Mortena Jeru Werda Communication

Mortena Jeru Werda Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mortena Jeru Werda Communication, Government Organization, Moretena Jeru, north Shewa, Martinez, CA.

A leading role in the Queen's Communication Information Sector: Integrating our vision for the success of our mission by raising public awareness of basic police strategies and programs by raising public awareness of basic police strategies and programs

"በጎነትና አብሮነት ...ለኢትዮጵያ ከፍታ""ጥራት በመጨመር ተደራሽነትን በማስፋት የተናበበ ዕቅድ በማቀድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መፈጸም ይጠበቅብናል"አቶ ኤልያስ አበበ የሰሜን ሸዋ ዞን ብል...
06/24/2026

"በጎነትና አብሮነት ...ለኢትዮጵያ ከፍታ"

"ጥራት በመጨመር ተደራሽነትን በማስፋት የተናበበ ዕቅድ በማቀድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መፈጸም ይጠበቅብናል"

አቶ ኤልያስ አበበ የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ

ደብረ ብርሃን፦ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን "በጎነትና አብሮነት ...ለኢትዮጵያ ከፍታ"
በሚል መሪ ቃል የ2018/19 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።

የንቅናቄ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ አበበ
"ጥራት በመጨመር ተደራሽነትን በማስፋት የተናበበ ዕቅድ በማቀድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መፈጸም ይጠበቅብናል" ብለዋል።

በየደረጃው ከሚገኘው መዋቅር የተናበበ ሁሉም ሊፈጽመው የሚችል ዕቅድ በማቀድ አመራሩ ኃላፊነት ወስዶ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት አለበት ብለዋል አቶ ኤልያስ።

የተሠራው ተግባር እራሱ የሚመሰክር በጠንካራ ድጋፍና ክትትል በመምራት በውጤት መታጀብ እንዳሐበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅዱን የሰሜን ሸዋ ዞን ሴቶች ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ የሮምነሽ ጋሻውጠና አቅርበዋል

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዜጎች ግዴታ ያልታከለበት በውስጣቸው ከሚመነጭ ሰብዓዊ አመለካከት ተነሥተው ለሚኖሩበት ማኅበረሰብ ልማትና አካባቢ ደኅንነት ጊዜያቸውን፣ ገንዘባቸውን ፣ ጉልበታቸውን ፣ በጎ አመለካከታቸውን ተግባር ላይ የሚያውሉበት ቅዱስ ተግባር መሆኑን ኃላፊዋ አንስተዋል።

በጎ ፈቃድኝነት ሌሎችን ከመርዳት አኳያ በጎ ፈቃደኞቹ ከማኅበረሰባቸው የሚማሩበትና የሕይወት ክህሎት የሚቀስሙበት አኩሪ ተግባር ነው ብለዋል።

ቁርጠኝነት ፣ ፈቃደኝነት ፣ነጻ አገልግሎት ፣ሰብአዊነት ፣ ዓለምአቀፋዊነት ፣ የሌሎችን ባህላዊ ዕሴቶችን ማክበር እና ከሌሎች ለመማር ዝግጁ መሆን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሆዎች እንደሆኑ አንስተዋል።

ወጣቶችናወጣቶችና ሴቶች (ዜጎች) የልማት ፣ የሰላምና የዲሞክራሲ አቅጣጫዎችና ትግበራ ላይ የተሟላ ግንዛቤ በመያዝ የሕዝብና የሀገር ፍቅር ተላብሰው ባለው በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ጉዳይ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል ነው።

በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በማኀበራዊ ኑሮ ውስጥ የመረዳዳት ባህልን ለማዳበር ትልቅ ሚና ይጫወታል ፤ በማኅበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ
ተግባሩ ባለፉት ዓመታት በንቅናቄ ሰፊ ተሳትፎ በመደረጉ በቂ ልምድና ክህሎት መወሰዱን አንስተዋል።

ወይዘሮ የሮምንሽ ከ9 መቶ 85 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍል እና ከ6 መቶ 40 በላይ በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ለማዳን ይሠራል ያሉት ኃላፊዋ 2 መቶ 97 ሚሊዮን 1 መቶ ሺህ ችግኝ በ38 ሺህ 8 መቶ 5 ሄክታር መሬት ይተከላል ብለዋል።

በ3 መቶ 55 ትምህርት ቤቶች ለ8 ሺህ 8 መቶ 49 ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ይሰጣል ፣ 39 ሺህ 3 መቶ 39 ደርዘን ደብተር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ተማሪዎች ይሰራጫል ፣ 9 መቶ 72 የአረጋዊያን ቤት ይጠግናል ፣ 2 ሺህ 1 መቶ 17 ዩኒት ደም ይለግሳል ነው ያሉት ኃላፊዋ።

በመድረኩ ላይ የዞኑ ኮር አመራሮችና የየመምሪያ ኃላፊዎች የቡድን መሪዎችና አጋርና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።
ምንጭ ሰሸዞመኮ

“ውጤታማ የሆነ ተግባቦት በማካሄድ እና የህግ የበላይነትን በማስከበር በጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶችን ላይ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል  የበኩሉን ሊወጣ ይገባል።አቶ ብዙሐን አሰፋ ሞረትና ጅሩ ወረዳ ዋ...
06/23/2026

“ውጤታማ የሆነ ተግባቦት በማካሄድ እና የህግ የበላይነትን በማስከበር በጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶችን ላይ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የበኩሉን ሊወጣ ይገባል።አቶ ብዙሐን አሰፋ ሞረትና ጅሩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ

‎የሞረትና ጅሩ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ከዩኒሴፍ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በጎጅ ልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ኮሚቴ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ካሂዷል።

‎ሞረትና ጅሩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ እንደተናገሩት ጎጅ ልማዳዊ ድርጊትን ለመከላከል ባለ ድርሻ አካላት ውጤታማ የሆነ ተግባቦት በማካሄድ እና የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁሉም የኮሚቴ አባላት የድርሻውን ከተወጣ ሙሉ በሙሉ ማስቆም ባይቻልም ለመቀነስ የድርሻው ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

‎በ2018 በጀት ዓመት በ6 ወሩ በተሠራው የጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች መከላከል ስራ ድርጊቱ እየቀነስ ቢመጣም አሁንም በማኅበረሰቡ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን ገልፀዋል።

‎ሞረትና ጅሩ ወረዳ ም/አስተዳዳሪምና የገንዘብ ጽ/ቤት አቶ ተመስገን ዲና በበኩላቸው ልማዳዊ ድርጊትን ከማህበረሰባችን ላይ ለመቅረፍ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ ማህበረሰቡ ላይ ጥልቅ የግንዛቤ ፈጠራ በመስራት የቅድመ መከላከል ስራ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

‎በወረዳው ውስጥ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ የጎጅ ልማዳዊ ድርጊት ጥቃቶችን ለመቀነስ እስካሁን የተደረጉ በተለይም በፕሮጀክቱ አማካኝነት የግንዛቤ ፈጠራ ፣ የህግ የማስከበር ፣ የማህበረሰብ ንቅናቄ እና የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር እየተሻሻለ ቢመጣም በርካታ ጉድለቶች አሉበት ብለዋል። በቀጣይ ከፕሮጀክቱ ጋር በትብብር በመሆን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመታገል ማህበራዊ ንቅናቄዎችን እና የህግ የማስከበር ተግባራት አስተማሪ እንዲሆኑ አቅዶ መስራት እንደሚገባም አቶ ተመስገን አሳስበዋል ።
‎ በወረዳው ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በኩል በጎጅ ልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ኮሚቴ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በዝርዝር ቀርቦ ሰፊ ወይይት ተካሂዶበታል።

‎የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ማስወገድ የአንድ ተቋም ስራ ሳይሆን የሁሉም ተቋማት እና ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች የጋራ በትብብርና በቅንጅትን ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
‎ለተጎጂዎች የማህበራዊ፣ የህጋዊ እና የስነ-ልቦና ድጋፍ አገልግሎቶችን በማስፋፋት በወጣቶች እና በሃይማኖት ተቋማት ተሳትፎ ላይ የተጠናከረ ስራ መስራት እንደሚገባም ቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል።
‎በመድረኩ ሞረትና ጅሩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ፣የሞረትና ጅሩ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ደስታ ሀይሉን ጨምሮ የአብይኮሚቴው አባላትና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በሞረትና ጅሩ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት  101 ኛ አየር ወለድ 4ኛ አድዋ  ከ እነዋሪ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች  ጋር  የወዳጅነተ የእግር ኳስ  ጨዋታ አካሂደው  2 ...
06/23/2026

በሞረትና ጅሩ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት 101 ኛ አየር ወለድ 4ኛ አድዋ ከ እነዋሪ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ጋር የወዳጅነተ የእግር ኳስ ጨዋታ አካሂደው 2 አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል።

በ3ሽህ 700 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ጅሩ ንግድና አግሮ ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር አባላት የዱቄት ፋብሪካ ለመገንባት ቦታ በመረከብ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ  በተገኙበ...
06/23/2026

በ3ሽህ 700 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ጅሩ ንግድና አግሮ ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር አባላት የዱቄት ፋብሪካ ለመገንባት ቦታ በመረከብ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ በተገኙበት የመሠረት የድንጋይ ተቀመጠ

‎እነዋሪ ፤ሰኔ 16/2018 ዓ.ም(ሞ.ጅ.ወ.መ.ኮ) በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በሞረትና ጅሩ ወረዳ በማንጉዶ ቀበሌ በ3ሽህ 700ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፍ ጅሩ ንግድና አግሮ ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር አባላት የዱቄት ፋብሪካ ለመገንባት የወረዳው ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና የአክሲወኑ ባለቤቶች የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል።
‎ይህ ፋብሪካዎች የጅሩ ንግድና አግሮ ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህር እንዱ ሲሆን የዱቄት ፋብሪካና እና የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን ፕሮሰስ የሚያደርጉ ግዙፍ ፋብሪካዎችን ጭምር የሚያካትት ሲሆን በ3700 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚገነባ እንደሆነም ተጠቁሟል።
‎ይህ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በዚህ አካባቢ መገንባቱ በአካባቢያችን ያለውን የስንዴ ምርትና አቅርቦት በቀላሉ ማህበረሰቡ እንዲጠቀምና የሚገነባው የዱቄት ፋብሪካና የምግብ ኮምፕሌክስ የመሰረት ድንጋይ መቀመጥ መቻሉ ለአካባቢው ትልቅ ገጸ በረከት ነው። በዚህም በጣም ተደስተናል ሲሉ በመርሐግብሩ የተገኙ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
‎የሞረትና ጅሩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ በመርሐ ግብሩ ተገኝተው እንደተናገሩት የአምራች ኢንዱስትሪው የሚያተኩርባቸው የወረዳችንን የሰብል ልማትና እንስሳት ሀብት ልማታችንን መሰረት ባደረገ መልኩ እሴት ጨምረን ሁለንተናዊ የአ/አደሮቻችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደ መንግስትም እንደ ፓርቲም በልዩ ኢንሸቲቭ እየተከናወነ እንደሆነ ጠቁመዋል። አክለውም ለፕሮጀክቱ ግንባታ ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበለት ሲሆን ግንባታው ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባ ከ134 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዚያዊ የስራ እድል እንደሚፈጥር አብራርተዋል።
‎በመርሐ ግብሩ የሞረትና ጅሩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ ፣ የሞረትና ጅሩ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቃለማሁ ሐይሌ፣የወረዳው ምክትል አሰተዳዳሪና የገንዘብ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ዲና፣ የሞረትና ጅሩ ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨሶትመንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባሻው በላይሁንን ጨምሮ የወረዳ አመራሮች ፣የአክሲዮኑ ባለቤቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

06/23/2026
የሞረትና ጅሩ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ስር የወጣቶች  የበጋ ስልጠናና ውድድር ሲካሄድ የነበረው ፋጻሜ አገኘ። እነዋሪ ሰኔ 15/10/2018 ዓ/ም የ/ሞ/ጅ/ወ/መ/ኮ/ጽ/ቤት በሰ...
06/22/2026

የሞረትና ጅሩ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ስር የወጣቶች የበጋ ስልጠናና ውድድር ሲካሄድ የነበረው ፋጻሜ አገኘ።
እነዋሪ ሰኔ 15/10/2018 ዓ/ም የ/ሞ/ጅ/ወ/መ/ኮ/ጽ/ቤት በሰሜን ሸዋ ዞን በሞረትና ጅሩ ወረዳ በጅሁር ንዑስ ከተማ በባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት በስፖርት ሂደት ስር የወጣቶች የበጋ ስልጠናና ውድድር ሲካሄድ የነበረው የእግር ኳስ ጨዋታ ለዋንጫ የቀረቡት ቡድኖች 27ኛ ሻለቃ ጉና እግር ኳስ ቡድን vsየጅሁር ከተማ ቅርጭም ኳስ ቡድን ጨዋታ አስገራሚ ፉክክር የታየበት ቢሆንም ጨዋታው 27ኛ ሻለቃ ጉና የእግር ኳስ ክለብ ጨዋታውን በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል።

በሞረትና ጅሩ ወረዳ የግብዓት አስተባባሪ ኮሚቴ የ2018/19 የግብርና ግብዓት አቅርቦት አፈፃፀም እና ከአሁን በፊት የነበሩ  የብድር አመላለስ ዙሪያ  የግምገማ መድረክ ተካሄደ‎​‎​በሰሜን ...
06/22/2026

በሞረትና ጅሩ ወረዳ የግብዓት አስተባባሪ ኮሚቴ የ2018/19 የግብርና ግብዓት አቅርቦት አፈፃፀም እና ከአሁን በፊት የነበሩ የብድር አመላለስ ዙሪያ የግምገማ መድረክ ተካሄደ
‎​
‎​በሰሜን ሸዋ ዞን ዞን የሞረትና ጅሩ ወረዳ የግብርና ጽ/ቤት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያለመ የ2018/19 የምርት ዘመን የግብዓት አቅርቦትና ስርጭት አፈፃፀምን ግምገማ

‎​በመድረኩ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ ፣አቶ ተመስገን ዲና የሞረትና ጅሩ ወረዳ ም/አስተዳዳሪ የገንዘብ ጽ/ቤት ኃላፊ የግብርና ጽ/ቤት አመራሮች ባለሙያዎች፣ የህብረት ሥራ ማህበራት ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

‎የውይይቱ አላማ ከአሁን በፊት ለአርሶ አደሩ በብድር የተሰጠ የግብዓት አመላለስና አሁን ለምርት ዘመኑ እየገባ ያለውን ግብዓትና በስርጭት ሂደቱን የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት በቀጣይ ዓመት ለሚከናወኑ ተግባራት አቅጣጫ በማስቀመጥ ላይ ትኩረቱን አድርጓል።

‎​በመድረኩ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ እንደተናገሩት የ2018/19 የምርት ዘመን የግብዓት አቅርቦት አፈፃፀም የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል የታዩብንን ክፍተቶች ደግሞ በማስተካከል ለቀጣዩ ቀሪ ጊዜያት እንደ ትልቅ ልምድ ልንጠቀምባቸው ይገባል ብለዋል።

‎አክለውም አቶ ብዙሐን አርሶ አደሩ ያለምንም እንግልት ግብዓቶችን በወቅቱ እንዲያገኝና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ በየደረጃው ያለን አመራሮች በቁርጠኝነትና በቅንጅት መስራት ይኖርብናል ሲሉ አሳስበዋል።

‎ወረዳ ም/አስተዳዳሪ የገንዘብ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ዲና በበኩላቸው በ2018/19 የምርት ዘመን የታየው የግባት ስርጭት አፈፃፀም አበረታች እንደሆነ እና አቅርቦቱ ባለፈ ስርጭቱ ፍትሃዊ እንዲሆን ማድረግ ይገባል ብለዋል።

‎አክለውም አቶ ተመስገን ከአሁን በፊት ለአርሶ አደሩ ግብዓት ይሰጥ እንደነበረና የተሰጠው ብድር ደግሞ በአግባቡ ባለመመለሱ በየ ዓመቱ ከወረዳው በጀት ላይ ክልሉ እየቆረጠ እንደሆነና ይህንን ችግር ለመቅረፍ እና ግብዓቱ ለአርሶ አደሩ በጊዜው እንዲደርስ ከህብረት ስራ ማህበራት እና አጋር መ/ቤቶች ጋር ያለውን ግንኙነት ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል ።

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ መሆንን ምክንያት በማድረግ ከብልፅግና ፓርቲ የቀረበ የምስጋና መልዕክት፤እጅግ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያን፣ የተከበራችሁ የፖለቲካ ማኅበረሰብ አባ...
06/21/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ መሆንን ምክንያት በማድረግ ከብልፅግና ፓርቲ የቀረበ የምስጋና መልዕክት፤

እጅግ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያን፣ የተከበራችሁ የፖለቲካ ማኅበረሰብ አባላትና የምርጫው ባለድርሻ አካላት፤

ዛሬ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲን በተግባር ያሳዩበት፣ ታሪካቸውን በደማቁ የጻፉበት እና አፍሪካ ስለ ራሷ በራሷ መወሰን እንደምትችል ለአለም ያበሰሩበት ታላቅ ምዕራፍ መመዝገቡ ይፋ ተደርጓል! በታሪካዊው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ሕዝባችን ትናንትን በማከም እና ነገን በፅኑ መሠረት ላይ በመተለም፣ የኢትዮጵያን ከፍታ እውን ለማድረግ ፋና ወጊ ለሆነው ለብልፅግና ፓርቲ ዳግም ታላቅ ኃላፊነትና አደራ ሰጥቷል። ብልፅግና ፓርቲ ይህንን ታላቅ ሕዝባዊ አደራ የተቀበለው በስኬቱ ሳይኩራራ፣ ጉድለቶቹን እያረመ ሕዝብን በቅንነት ለማገልገልና ቃልን በተግባር ለማረጋገጥ ባለው ፅኑ እምነት ነው። ለዚህ ታላቅ ክብር መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሰጠንን የዴሞክራሲ ውል በታላቅ ትሕትና እና በከፍተኛ አክብሮት እንቀበላለን።

ይህ የምስጋና መልዕክት እኛን ለመረጡን ዜጎች ብቻ የቀረበ አይደለም፤ ይልቁንም ያሻቸውን አማራጭ በመምረጥ መብታቸውን የተጠቀሙ፣ በካርዳቸው ድምፅ በመንፈግም ቢሆን ሂደቱ ሕጋዊና ሰላማዊ እንዲሆን የበኩላቸውን የተወጡ ዜጎችን ሁሉ ያጠቃልላል። ምክንያቱም የእያንዳንዱ ዜጋ ተሳትፎ የሀገራችን ዴሞክራሲ እውነተኛ አሸናፊ እንዲሆን አድርጓል።

በዚህ ምርጫ ሂደት ውስጥ በግልጽ መለየት ያለበት መሠረታዊ እውነት አለ፡- የብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ መንግሥት የመመሥረት መብት ማግኘቱ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና የማረጋገጥ ራዕይ ሰንቆ ውጤታማ ጉዞ እያደረገ እንዳለ ፓርቲ እንደ ትልቅ እድል የሚወሰድ ሲሆን፤ የምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሓዊና ተዓማኒ ሆኖ መጠናቀቅ ግን የውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ እና የመላው ሕዝቧ ስትራቴጂያዊ አሸናፊነት ማረጋገጫ ነው!

ይህ ምርጫ እንደ ከዚህ ቀደሙ የተለመደ የፖለቲካ ውድድር ወይም ወቅታዊ ኩነት አልነበረም። ይህ ምርጫ የውስጥና የውጭ የሴራ መረቦችን የበጣጠሰ፣ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በተግባር ያደመቀ፣ የዴሞክራሲ ተቋሞቻችንን ብስለት ያጎለበተ ታላቅ የታሪክ እመርታ ነው። ኢትዮጵያ በማንኛውም ውጫዊ ጫና ሳትበገር፣ ሙሉ በሙሉ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ ክንውን ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል።

ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መሳተፋቸው የሕዝባችንን የፖለቲካ ንቃት የሚያሳይ ሲሆን፣ የሕዝብን ድምፅና ሉዓላዊ ፈቃድ ማክበር የመንግሥትና የማንኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ቀዳሚ ተግባር መሆኑ በተግባር ተረጋግጧል። በምርጫው የኢትዮጵያ ጠላቶች ሀገርን ለማወክ የሸረቡት ተንኮልና መፍጨርጨር በሕዝባችን ብስለት ሙሉ በሙሉ እንዲመክን ተደርጓል።

የዚህ ታሪካዊ ስኬትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት መረጋገጥ ያለ ባለድርሻ አካላት ተጋድሎ ሊታሰብ አይችልም። በመሆኑም ፓርቲያችን ብልፅግና ለምርጫው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን ያቀርባል፡፡

በተለይም የኢትዮጵያ ሕዝብ የአገር ህልውናንና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለውን የማይናወጥ ወገንተኝነት በተግባር ባሳየበት በዚህ ታሪካዊ የምርጫ ሂደት፣ በተለይም በምርጫው ዕለት ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ እግር ጥሎት ሳይሆን ራዕይ መርቶት፣ ብርድና ድካምን በሀገራዊ ፍቅር እያሸነፈ፣ እስከ ሚቀጥለው ቀን ሌሊት 10 ሰዓት ድረስ ለሙሉ 24 ሰዓታት ያለመሰልቸት በታላቅ ትዕግሥትና ዲሲፕሊን ተሰልፎ

በመጪው የክረምት ወቅት ለሚደረገው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በወረዳው እየተደረገ ያለው የችግኝ ቅድመ ዝግጅት እና ቸግኞቹ ያሉበት ቁመና ተጎበኘ‎‎ሰኔ 14/2018 (ሞረትና ጅሩ ወረዳ  ...
06/21/2026

በመጪው የክረምት ወቅት ለሚደረገው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በወረዳው እየተደረገ ያለው የችግኝ ቅድመ ዝግጅት እና ቸግኞቹ ያሉበት ቁመና ተጎበኘ

‎ሰኔ 14/2018 (ሞረትና ጅሩ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)።።
‎በወረዳ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተደረገው ቅድመ ዝግጅት በጅሁር ችግኝ ጣቢያ በመገኘት ተጎብኝቷል።

‎የ8ተኛዉ አረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር ቅድመ ዝግጅት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል እንደሚመናነወን ተጠቁሟል

‎በጉብኝቱ ወቅት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብዙሐን አሰፋ አ እንደገለጹት፤ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ ይካሄዳል። ይህንን ለማሳካትም በወረዳ ደረጃ ከፍተኛ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶካሱ አበበ በበኩላቸው፤ የችግኝ ተከላው የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ ለምግብነት የሚውሉ እፅዋትንም ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።

‎አቶ ካሱ አከለውም በ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በወረዳው በአጠቃላይ ከ10.5 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል።

‎ተከላው የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያላቸውን የመኖ ዕፅዋት እና የውበት ችግኞችን ያካተተ መሆኑንም ገልጸዋል ።

ከምርጫ ማግስት ህብረተሰቡ ሰላምን በማጽናት፤ ልማትን ለማስቀጠል በትጋት መስራት ይገባል" ተባለ‎‎እነዋሪ፤ሰኔ 14/2018ዓ.ም(ሞጅወኮመ) በሰሜን ሸዋ ዞን የሞረት ጅሩ  ወረዳ ብልጽግና ፓር...
06/21/2026

ከምርጫ ማግስት ህብረተሰቡ ሰላምን በማጽናት፤ ልማትን ለማስቀጠል በትጋት መስራት ይገባል" ተባለ

‎እነዋሪ፤ሰኔ 14/2018ዓ.ም(ሞጅወኮመ) በሰሜን ሸዋ ዞን የሞረት ጅሩ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ "ከምርጫ ድል ማግስት፤ጠንካራ መንግስት"በሚል መሪ ቃል የሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁንና በቀጣይ አቅጣጫ ስራዎች ዙሪያ በወረዳወ በተያለዩ ቀበሌ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።
‎ማህበረሰቡ ከምርጫ ማግስት ህብረተሰቡ ሰላምን በማጽናት፤ልማትን ለማስቀጠል በትጋት ሊሰሩ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎ሰላም ለሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ የቀበሌው ነዋሪዎች ለአካባቢያቸው ሰላም መጠበቅ ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ በውይይቱ ተገልጿል።

‎ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም የተጠናቀቀው የወረዳው ህዝብ ሰላም ሰላምና ልማት ፈላጊና መንግስት የሚመሠረተው በምርጫ መሆኑን ካለፈው ልምዱና ህግ አክባሪነቱ የመነጨ መሆኑም ተጠቁሟል።
‎በውይይቱ የቀበሌው ደጋፊ አመራሮች፥ የቀበሌ አመራሮች ንዲሁምም የፀጥታ አመራሮች ተገኝተዋል።

Address

Moretena Jeru, North Shewa
Martinez, CA
251116880051

Telephone

+251116880051

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mortena Jeru Werda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share