06/24/2026
"በጎነትና አብሮነት ...ለኢትዮጵያ ከፍታ"
"ጥራት በመጨመር ተደራሽነትን በማስፋት የተናበበ ዕቅድ በማቀድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መፈጸም ይጠበቅብናል"
አቶ ኤልያስ አበበ የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
ደብረ ብርሃን፦ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን "በጎነትና አብሮነት ...ለኢትዮጵያ ከፍታ"
በሚል መሪ ቃል የ2018/19 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።
የንቅናቄ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ አበበ
"ጥራት በመጨመር ተደራሽነትን በማስፋት የተናበበ ዕቅድ በማቀድ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መፈጸም ይጠበቅብናል" ብለዋል።
በየደረጃው ከሚገኘው መዋቅር የተናበበ ሁሉም ሊፈጽመው የሚችል ዕቅድ በማቀድ አመራሩ ኃላፊነት ወስዶ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት አለበት ብለዋል አቶ ኤልያስ።
የተሠራው ተግባር እራሱ የሚመሰክር በጠንካራ ድጋፍና ክትትል በመምራት በውጤት መታጀብ እንዳሐበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅዱን የሰሜን ሸዋ ዞን ሴቶች ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ የሮምነሽ ጋሻውጠና አቅርበዋል
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዜጎች ግዴታ ያልታከለበት በውስጣቸው ከሚመነጭ ሰብዓዊ አመለካከት ተነሥተው ለሚኖሩበት ማኅበረሰብ ልማትና አካባቢ ደኅንነት ጊዜያቸውን፣ ገንዘባቸውን ፣ ጉልበታቸውን ፣ በጎ አመለካከታቸውን ተግባር ላይ የሚያውሉበት ቅዱስ ተግባር መሆኑን ኃላፊዋ አንስተዋል።
በጎ ፈቃድኝነት ሌሎችን ከመርዳት አኳያ በጎ ፈቃደኞቹ ከማኅበረሰባቸው የሚማሩበትና የሕይወት ክህሎት የሚቀስሙበት አኩሪ ተግባር ነው ብለዋል።
ቁርጠኝነት ፣ ፈቃደኝነት ፣ነጻ አገልግሎት ፣ሰብአዊነት ፣ ዓለምአቀፋዊነት ፣ የሌሎችን ባህላዊ ዕሴቶችን ማክበር እና ከሌሎች ለመማር ዝግጁ መሆን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሆዎች እንደሆኑ አንስተዋል።
ወጣቶችናወጣቶችና ሴቶች (ዜጎች) የልማት ፣ የሰላምና የዲሞክራሲ አቅጣጫዎችና ትግበራ ላይ የተሟላ ግንዛቤ በመያዝ የሕዝብና የሀገር ፍቅር ተላብሰው ባለው በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ጉዳይ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል ነው።
በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በማኀበራዊ ኑሮ ውስጥ የመረዳዳት ባህልን ለማዳበር ትልቅ ሚና ይጫወታል ፤ በማኅበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ
ተግባሩ ባለፉት ዓመታት በንቅናቄ ሰፊ ተሳትፎ በመደረጉ በቂ ልምድና ክህሎት መወሰዱን አንስተዋል።
ወይዘሮ የሮምንሽ ከ9 መቶ 85 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍል እና ከ6 መቶ 40 በላይ በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ለማዳን ይሠራል ያሉት ኃላፊዋ 2 መቶ 97 ሚሊዮን 1 መቶ ሺህ ችግኝ በ38 ሺህ 8 መቶ 5 ሄክታር መሬት ይተከላል ብለዋል።
በ3 መቶ 55 ትምህርት ቤቶች ለ8 ሺህ 8 መቶ 49 ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ይሰጣል ፣ 39 ሺህ 3 መቶ 39 ደርዘን ደብተር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ተማሪዎች ይሰራጫል ፣ 9 መቶ 72 የአረጋዊያን ቤት ይጠግናል ፣ 2 ሺህ 1 መቶ 17 ዩኒት ደም ይለግሳል ነው ያሉት ኃላፊዋ።
በመድረኩ ላይ የዞኑ ኮር አመራሮችና የየመምሪያ ኃላፊዎች የቡድን መሪዎችና አጋርና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።
ምንጭ ሰሸዞመኮ