17/06/2026
በሪያድ የኢትዮጵያ ዓለሞ አቀፍ ትምህርት ቤት የገቢ ማሰባሰብ ዙሪያ የውይይት ተካሄደ
=======≡==========================
(ሪያድ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም) በሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ ከተማ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት በቅርቡ በጨረታ ለተረከበው 10,000 ካሬ ሜትር አዲስ የትምህርት ቤት ቦታ ለእድሳትና ለማስፋፊያ ግንባታ የገቢ ማሰባስብ ዙሪያ የኮሙኒቲው የማህበራት አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
መድረኩን የመሩት በሪያድ የኢፌዲሪ ኤምባሲ የሚሲዮኑ ምክትል መሪ ክቡር አምባሳደር አወል ወግሪስ ባሰተላለፉት መለዕክት "ት/ቤት መገንባት ዘመናዊ ዕውቀትን የታጠቀ ትውልድና ሀገርን መገንባት ማለት በመሆኑ ይህ አዲስ የምንገነባው ት/ቤት ዘመኑን ያፈራውን ቴክኖሎጂን በመጠቀም መገንባት እንዳለበት፣ በአላህ ፈቃድ የጀመርነውን ተግባር መጨረስ ስለምጠበቅብን ቃላችንን አክብረን ለስኬቱ በማብቃት ሁሌም ሀገሩን እና ማህበረሰቡን ደጋፊ የሆነው የሪያድ ነዋሪ ለትምህርት ቤቱ ግንባታ ገቢ ማስባስብ መረባረብ ይጠበቃል" ብለዋል።
በመድረኩ ላይ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሰብሳቢ አቶ ሱለይማን መሀመድ፣ የት/ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ አበበ ጫላ፣ ሪያድ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ማህበራት እና የአደረጃጀት አመራሮች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል።
የት/ቤቱ ርዕሰ መምህርም የት/ቤቱን አመሠራረትና እስካሁን የተጓዘበትን ረጅም ጉዞ በስፋት በማብራራት፣ የፊታችን ዐርብ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (19/6/2026) በሪያድ እና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን በነቂስ ወጥቶ ገቢ ማሰባሰቢያው ላይ እንዲሳተፍ ከመድረኩ ጥሪ አስተላልፈዋል::
በመጨረሻም መድረኩ ላይ የተሳተፉት የልማት ማህበራት የሥራ ኃላፊዋችና ታዋቂ ግልሰቦች ለትምህርት ቤቱ ዕድሳትና ማስፋፊያ የሚጠብቅባቸውን እንደሚያደረጉ ቃል ገብተዋል።
MFAEthiopia Amharic የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia
Ethiopian Diaspora Service
FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)