Ethiopian Embassy in Riyadh / የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ሪያድ

Ethiopian Embassy in Riyadh / የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ሪያድ This is the official Facebook handle of the Ethiopian Embassy in Riyadh, Saudi Arabia
(4)

This is the official page of the Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in the Kingdom of Saudi Arabia.

በሪያድ የኢትዮጵያ ዓለሞ አቀፍ ትምህርት ቤት የገቢ ማሰባሰብ ዙሪያ የውይይት ተካሄደ=======≡==========================(ሪያድ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም) በሳዑዲ ዓረቢያ ...
17/06/2026

በሪያድ የኢትዮጵያ ዓለሞ አቀፍ ትምህርት ቤት የገቢ ማሰባሰብ ዙሪያ የውይይት ተካሄደ
=======≡==========================
(ሪያድ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም) በሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ ከተማ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት በቅርቡ በጨረታ ለተረከበው 10,000 ካሬ ሜትር አዲስ የትምህርት ቤት ቦታ ለእድሳትና ለማስፋፊያ ግንባታ የገቢ ማሰባስብ ዙሪያ የኮሙኒቲው የማህበራት አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

መድረኩን የመሩት በሪያድ የኢፌዲሪ ኤምባሲ የሚሲዮኑ ምክትል መሪ ክቡር አምባሳደር አወል ወግሪስ ባሰተላለፉት መለዕክት "ት/ቤት መገንባት ዘመናዊ ዕውቀትን የታጠቀ ትውልድና ሀገርን መገንባት ማለት በመሆኑ ይህ አዲስ የምንገነባው ት/ቤት ዘመኑን ያፈራውን ቴክኖሎጂን በመጠቀም መገንባት እንዳለበት፣ በአላህ ፈቃድ የጀመርነውን ተግባር መጨረስ ስለምጠበቅብን ቃላችንን አክብረን ለስኬቱ በማብቃት ሁሌም ሀገሩን እና ማህበረሰቡን ደጋፊ የሆነው የሪያድ ነዋሪ ለትምህርት ቤቱ ግንባታ ገቢ ማስባስብ መረባረብ ይጠበቃል" ብለዋል።

በመድረኩ ላይ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሰብሳቢ አቶ ሱለይማን መሀመድ፣ የት/ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ አበበ ጫላ፣ ሪያድ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ማህበራት እና የአደረጃጀት አመራሮች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ተሳትፈዋል።

የት/ቤቱ ርዕሰ መምህርም የት/ቤቱን አመሠራረትና እስካሁን የተጓዘበትን ረጅም ጉዞ በስፋት በማብራራት፣ የፊታችን ዐርብ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (19/6/2026) በሪያድ እና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን በነቂስ ወጥቶ ገቢ ማሰባሰቢያው ላይ እንዲሳተፍ ከመድረኩ ጥሪ አስተላልፈዋል::

በመጨረሻም መድረኩ ላይ የተሳተፉት የልማት ማህበራት የሥራ ኃላፊዋችና ታዋቂ ግልሰቦች ለትምህርት ቤቱ ዕድሳትና ማስፋፊያ የሚጠብቅባቸውን እንደሚያደረጉ ቃል ገብተዋል።

MFAEthiopia Amharic የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia
Ethiopian Diaspora Service
FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)

ማስታወቂያወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ ኮፒ በመስጠት ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ ረቡዕ በቀን (17/06/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ...
16/06/2026

ማስታወቂያ
ወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ ኮፒ በመስጠት ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ ረቡዕ በቀን (17/06/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 1:00 (7:00 AM) ሰዓት መለዝ አከባቢ በሚገኘው የአሻራ መስጫ ማዕከል ቀደም ብላችሁ በቦታው በመገኘት በስማ/አሻራ መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ቦታው📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA?g_st=ic

BEEKSISA
Lammiiwwan gara biyyaa galuuf koppii liiseepaasee keessan kennattanii eeggachaa jirtan, Guyyaa borii Roobii (17/06/2026) ganama sa'aatii 1:00 AM (7:00 AM) irratti wiirtuu ashaaraa qubaa naannoo Malaz jedhamutti waqtiin dhufuun ashaaraa qubaa kennuu akka dandeessan isin beeksifna.
Iddoon:📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA

15/06/2026
15/06/2026
15/06/2026
ማስታወቂያወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ ኮፒ በመስጠት ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ ሰኞ በቀን (15/06/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ ...
14/06/2026

ማስታወቂያ
ወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ ኮፒ በመስጠት ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ ሰኞ በቀን (15/06/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 1:00 (7:00 AM) ሰዓት መለዝ አከባቢ በሚገኘው የአሻራ መስጫ ማዕከል ቀደም ብላችሁ በቦታው በመገኘት በስማ/አሻራ መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ቦታው📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA?g_st=ic

BEEKSISA
Lammiiwwan gara biyyaa galuuf koppii liiseepaasee keessan kennattanii eeggachaa jirtan, Guyyaa borii Wiiyxata/Isniina (15/06/2026) ganama sa'aatii 1:00 AM (7:00 AM) irratti wiirtuu ashaaraa qubaa naannoo Malaz jedhamutti waqtiin dhufuun ashaaraa qubaa kennuu akka dandeessan isin beeksifna.
Iddoon:📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA

14/06/2026

በሪያድ የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት አዲስ የማስተማሪያ ትምህርት ቤት እድሳት እና ማስፋፍያ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ወላጆች፣ ዳያስፖራው ማህበረሰብ እና መላው የሪያድ ነዋሪ የሆናችሁ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የራሳችሁን አሻራ እንዲታኖሩ በቀን፡ ዓርብ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (June 19, 2026) በክብር ተጋብዛችኋል።
ቦታ፡ *አልህዝም ቀሲር በሰማት
ሰዓት ፡ *ከ 8፡00 p.m ጀምሮ

https://maps.app.goo.gl/Vn9qWhD1bHDiRdi49

📌ማስታወቂያ📌    *******ፓስፖርት ለማሳደስ አመልክታችሁ ታድሶ የመጣላችሁ ዜጐቻችን፣ ቀጥሎ በተቀመጠው የስም ዝርዝር ውስጥ ስማችሁን በማየት እና ተራ ቁጥራችሁን በመያዝ ዘወትር በስራ ሰ...
14/06/2026

📌ማስታወቂያ📌
*******
ፓስፖርት ለማሳደስ አመልክታችሁ ታድሶ የመጣላችሁ ዜጐቻችን፣ ቀጥሎ በተቀመጠው የስም ዝርዝር ውስጥ ስማችሁን በማየት እና ተራ ቁጥራችሁን በመያዝ ዘወትር በስራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 10 በአካል በመቅረብ ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን ኤምባሲው ያሳውቃል።
ማሳሰቢያ፡-
አመልካቾች ፓስፖርት ለመውሰድ ስትመጡ ለማሳደስ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ፣ አሮጌውን ፓስፖርት፣ በጠፋ ያመለከታችሁ ከሆነ የተሞላውን ፎርም እንዲሁም ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ላይ ከስማችሁ ትይዩ የተመለከተውን የኮድ ቁጥር መዝግባችሁ ይዛችሁ መምጣት ይኖርባችኋል።

📌Beeksisa 📌
*******
Lammiileen keenya paaspoortii haaraan isinii haaromsamee dhufe hundi sa'aatii hojiitti Mooraa Imbaasichaatti dhufuun waajjira lakkoofsa 10 dhihaatuun paaspoortii keessan fudhachuu akka dandeessan Imbaasiin Ethiopia Riyaaditti argamu isin beeksisa.
Hubachiisa:
Paaspoortii keessan fudhachuuf yeroo dhuftan lakkoofsa koodii gabatee armaan gadii irratti maqaa keessan cinatti mul’atu fiddanii dhufuu qabdu.

በሪያድ የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ት/ቤት የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የምረቃ መርሃ ግብር ተካሄደ =============(ሪያድ፣ ሰኔ 05 ቀን 2018 ዓ.ም) በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ ...
14/06/2026

በሪያድ የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ት/ቤት የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የምረቃ መርሃ ግብር ተካሄደ
=============
(ሪያድ፣ ሰኔ 05 ቀን 2018 ዓ.ም) በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በድምቀት አካሄዷል።

በመርኃ ግብሩ ላይ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት በሪያድ የኢዴዲሪ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ ክቡር አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ ለተመራቂዎቹ "እንኳን ለዚህ ታላቅ ቀን አደረሳችሁ" በማለት ንግግራቸውን የጀመሩ ሲሆን፣ ተማሪዎቹ በቀጣይ የትምህርትና የሕይወት ጉዟቸው የሚጠበቅባቸውን ከፍተኛ ኃላፊነቶች በትጋትና በቁርጠኝነት እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

አክለውም መንግስታችን ሀገርን የሚገነባው የተማረ ማህበረሰብ መሆኑን በሚገባ በመገንዘብ ለትምህርት ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት፣ በተለያዩ የፖሊሲ እና የልማት ስትራቴጂዎች ውስጥ ትምህርትን እንደ ቀዳሚ አጀንዳ በመያዝ እየተገበረ መሆኑን በመግለጽ፣ በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤትም ይህንኑ የሀገራዊ ትምህርት ልማት አንድ አካል በመሆን እያገለገለ የሚገኝ ተቋም መሆኑን አንስተዋል።

በተጨማሪም ትምህርት ቤቱ ከመንግሥት ለ25 ዓመት በሊዝ ያገኘውን አዲስ የትምህርት ቤት ሕንፃ ለማደስና ለማስፋፋት በኤምባሲያችን፣ በት/ቤቱ አመራር እና በኮሚኒቲው የተጀመሩት የእስካሁኑ አበረታች እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን በመግለጽ፣ ከዚህ በፊት ከነበረው ምቹ የመማር ማስተማር ከባቢን ለመፍጠር ወላጆች፣ ቀድሞ ተማሪዎችና ዳያስፖራው ማህበረሰብ የራሱን አሻራ እንዲያኖር ጥሪ አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም በ2018 ዓ.ም ያስመዘገቡትን የትምህርት ውጤትና አፈጻጸም መሠረት በማድረግ ለተመራቂዎቹ የዋንጫ፣ የሰርቲፊኬት እና የምስክር ወረቀት ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኤምባሲው ዲፕሎማቶች፣ የሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ማህበር ሰብሳቢ አቶ ሱለይማን መሀመድ፣ የትምህርት ቤቱ አመራር ቦርድ አባላት፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ወላጆች፣ ተመራቂ ተማሪዎች ተገኝተዋል። MFAEthiopia Amharic የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ Ethiopian Diaspora Service

12/06/2026

. 📌ማስታወቂያ📌 *********************
ተጨማሪም መረጃዎችን በቆንስላ ጽ/ቤቱ ማኅበራዊ ሚዲያ ገፆች ላይ በሚከተሉት ማስፈንጠሪያ (Link) በኩል ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን:-
Telegram ( የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ) :- https://t.me/jedcon
Twitter (በትዊተር ይከተሉን):- https://x.com/EthiopianJeddah?s=20@

Address

Abu Bakr Al Karkhi, Al Safarat
Riyadh
11693

Opening Hours

Monday 8:30am - 3pm
Tuesday 8:30am - 3pm
Wednesday 8:30am - 3pm
Thursday 8:30am - 3pm
Sunday 8:30am - 3pm

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Embassy in Riyadh / የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ሪያድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share