Basketo ZoneLaska Zuriya Woreda Youths and Sport Department

Basketo ZoneLaska Zuriya Woreda Youths and Sport Department እኛ ወጣቶች የነገዋን የበለፀገች ኢትዮጵያ የመገንበት ታሪካዊ ኃላፊነት ያለብን ነን!!

ባህላችን የእኛ መለያችን ነው፤ባህላዊ አለባበሳችን የትውልድ መድመቂያችን ነው፤መሬቶቻችን የኢንቨስትመንት ትኩረታችን ነው፤ሾልኣ ካሻ የብሔረሰቡ የምስጋና በዓላችን ነዉ ፤ኑ ወደ ባስኬቶ ዞን ም...
08/12/2025

ባህላችን የእኛ መለያችን ነው፤
ባህላዊ አለባበሳችን የትውልድ መድመቂያችን ነው፤
መሬቶቻችን የኢንቨስትመንት ትኩረታችን ነው፤
ሾልኣ ካሻ የብሔረሰቡ የምስጋና በዓላችን ነዉ ፤
ኑ ወደ ባስኬቶ ዞን ምን አላችሁ ካላችሁ:- ለም፣ሰፊ ፣ ለሁሉም ሰብሎች ምቹ መሬት አለን
ስርሶና በአርሶ መንቲያ ፏፏተ፣ አርድሞሳ አዲታና ሶኚ ዋሻዎች፣ አቡነ አረጋዊ ፀበል፣ ሮኪ መልካአ ምድር፣ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖች የቱን ዘርዝሬ የቱን ልተው! የኦሮሞ ይገርማል! በሆቴል፣ በእርሻ፣ በማዕድን፣ በጥናትና ምርምር ሥራዎች ኢንቨስት ለማድረግ የምትፈልጉ ካላችሁ በፍቅር እና በብሔረሰቡ የእንግዳ ተቀባይነት ባይል እንቀበላለን።

በዛሬው ዕለት በላስካ ዙሪያ ወረዳ የበጋ   ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፍ አካል የሆነው የታዳጊዎች የእግር ኳስ የውስጥ ውድድር  መደረጉ ተገለፀ። ‎ ህዳር 28/3/ 2018 ዓ...
07/12/2025

በዛሬው ዕለት በላስካ ዙሪያ ወረዳ የበጋ ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፍ አካል የሆነው የታዳጊዎች የእግር ኳስ የውስጥ ውድድር መደረጉ ተገለፀ።

‎ ህዳር 28/3/ 2018 ዓ/ም ላስካ ዙሪያ ወረዳ የወጣቶችና ስፖርት ኮሚንኬሽን ላስካ

በዛሬው ዕለት ‎የበጋ ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፍ አካል የሆነው የታዳጊዎች የእግር ኳስ ጨዋታ መደረጉን የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ።

በዚህም ጋራ ብሩህ ተስፋ ከዶኮ መድን ጋር የወዳጅነት ጨዋታቸውን ደረጉት ስሆን ዶኮ መዲና ብሩህ ተስፋን 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

‎በውድድሩ ታዳጊ ተጨዋቾች እርስ በርስ ዓቅማቸውን የፈተሹበትና ፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነትን በተላበሰ መልኩ ብርቱ ፉክክር ያደረጉበት ጨዋታ መሆኑ ታይቷል።

ህዳር 28/3/ 2018 ዓ/ም
ላስካ

"የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ለሀገራዊ መተማመንና መተዋወቅ ጉልህ ሚና አለው" ወጣት ሳሙኤል ግርማበባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ሱባ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የበጋ በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዕቅድ ...
25/11/2025

"የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ለሀገራዊ መተማመንና መተዋወቅ ጉልህ ሚና አለው" ወጣት ሳሙኤል ግርማ

በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ሱባ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የበጋ በጎ ፍቃድ አገልግሎት ዕቅድ አካል የሆነው የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት አስተባባሪ አቶ ሳሙኤል ግርማ ዓለም በዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ፊቷን ወደ አንድ ተርታ እያቀናች መሆኑን ተናግረዋል።

አያይዘውም የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ መተማመን እና መታወቅን ለማፅናት ከፍተኛ ሚና መኖሩን ጠቁመዋል።

የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ በተለይ ወጣቱን ከቴክኖሎጂ ጋር ለማላመዲና ዘመኑን የሚመጥን መረጃን ወደ አንድ ቋት ለመሰብሰብ የታለመ መሆኑን የባስኬቶ ዞን የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የወጣት ዘርፍ ኃላፊ ወጣት ታምራት ደጄ ተናግረዋል።

ይህ ተግባር የበጋ ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ18ቱ የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ እንደሆኑ አክለው ጠቁመዋል።

ይህ ተግባር በዙሪያ ወረዳ ባሉ ሁሉም ቀበሌዎች ላይ በነቃ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

ህዳር 16/2018 ዓ.ም
ላስካ
የላስካ ዙሪያ ወረዳ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት

በዛሬው ቀን ጳጉሜ 2 በኅብር ተሳስረን በአንድነት ተዋደን በዶንኪ ሁለገብ ስታድዬም ከቀኑ 7:00 ላስካ ዙሪያ ወረዳ መምህራን VS ከከተማ መምህራን እንድሁም የዙሪያ ወረዳ አመራር VS ከከተ...
07/09/2025

በዛሬው ቀን ጳጉሜ 2 በኅብር ተሳስረን በአንድነት ተዋደን በዶንኪ ሁለገብ ስታድዬም ከቀኑ 7:00 ላስካ ዙሪያ ወረዳ መምህራን VS ከከተማ መምህራን እንድሁም የዙሪያ ወረዳ አመራር VS ከከተማ አመራር ጋር ከቀኑ 9:00 ላይ እጅግ በጣም ብርቱ ፉክክር የምታይበት ጫዎታ ስለምያደርጉ ኤርሶ የትም መሄድ አይጠበቆትም አብረን ዛሬ ጳጉሜ 2 የኅብር ቀንን በደስታ እናክብር!

‎ከላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት


ጳጉሜን-2 የኅብር ቀንኢትዮጵያ በብሔር፣ በሃይማኖት እና ባህል ኅብር ያጌጠች ውብ ሀገር ነች፡፡ ኅበሯ የጥንካሬዋ እና የውበቷ መገለጫ ነው፡፡ በዚህ ኅብሯም ዓለም የሚደነቅባቸውን ጀብዱዎች ፈ...
07/09/2025

ጳጉሜን-2 የኅብር ቀን

ኢትዮጵያ በብሔር፣ በሃይማኖት እና ባህል ኅብር ያጌጠች ውብ ሀገር ነች፡፡

ኅበሯ የጥንካሬዋ እና የውበቷ መገለጫ ነው፡፡

በዚህ ኅብሯም ዓለም የሚደነቅባቸውን ጀብዱዎች ፈጽማለች፡፡

ጳጉሜን ሁለት "ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ!" በሚል መሪ ቃል የኅብር ቀን ሆኖ ይውላል፡፡ በዕለቱ ኢትዮጵያውያን በኅበረት ያሳኳቸው ታላላቅ ድሎች ይታሰባሉ፡፡

ኢትየጵያውያ በዘመናት ሂደት በፅኑ መሰረት ላይ እየተገነቡ የመጡ የነባር የአብሮነት እሴቶች፣ የወል ታሪኮች እና ባህሎችበላቤት ነች፡፡

ይህን እሴቷን ተጠቅማም የትንሣኤዋ ማብሰሪያ የሆነውን የማንሰራራት ዘመን ጀምራለች፡፡

ትላንት በኅብረት ዓድዋ ላይ ታሪኳን በወርቅ ቀለም እንደጸፈችው ዛሬም በልጆቿ ኅብር እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን አሳክታለች፡፡

‎በላስካ ዙሪያ ወረዳ የወጣቶች ክረምት በጎ ስራ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።‎‎ላስካ፦ጳጉሜ 1/2017ዓ.ም (ፓርቲ ሚዲያ)‎በላስካ  ዙሪያ ወረዳ ዶኮ አይማ ቀበሌ የክረምት ወጣቶች በጎ ስራ ተ...
06/09/2025

‎በላስካ ዙሪያ ወረዳ የወጣቶች ክረምት በጎ ስራ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

‎ላስካ፦ጳጉሜ 1/2017ዓ.ም (ፓርቲ ሚዲያ)
‎በላስካ ዙሪያ ወረዳ ዶኮ አይማ ቀበሌ የክረምት ወጣቶች በጎ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎የላስካ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ተፈራ ኃይሉ በጎነት በተፈጥሮ ብቻ የሚሰጥ ሳይሆን በሂደት መበልፀግ እና መዳበር የሚችል መልካም ስብዕና ነው ስሉ ገልፀዋል፡፡

‎አክለው 2017 ዓ.ም በያዝነው የክረምት ወጣቶች በጎ ስራ አገልግሎት የበርካቶችን እንግልትና ስቃይ ያስቀረ እንዲሁም የበርካቶችን ዕንባ ያበሰ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል።

‎የላስካ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ተወካይና የፓርቲ ጽ/ቤት የሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መርዕድ ወንዱ ወጣቶች ሁለንተናዊ ብልፅግናን በማረጋገጥ ረገድ ዘርፈ ብዙ ኩነቶችን እያከናወኑ እንደሆነ ጠቅሰው በዝህ በጎ ስራ ላይ የተሳተፉ አካላቶችን አመስግነዋል።

‎የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶች ጽ/ቤት ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታምራት ደጄ እንደ ዙሪያ ወረዳ እስካሁን ባለው ክረምት በጎ ስራ ብቻ 18 የተጠናቀቁ ቤቶችን ለአቅሜ ደካሞችና አረጋዊያን ቁልፍ ለማስረከብ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ጠቅሰዋል።

‎በጎነት ከትናንት እስከ ዛሬ ካሻገሩን መልካም እሴቶቻችን መካከል አንዱና ዛሬም አጠናክረን ለቀጣዩ ትውልድ ልናሻግረው የሚገባው እሴታችን እንደሆነ ተገልጿል፡፡

‎በመጨረሻም በዛሬው ዕለት ግንባታ የተፈፀመላቸው አረጋዊ ስለተደረገላቸው በጎ ተግባር አመስግነዋል።


‎ ጳጉሜ 1/2017ዓ.ም
‎ ላስካ

በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ እና በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ ወረዳ መካከል የሚካሄድ የእርቅ ሰላም ኮንፍራንስ በባስኬቶ ዞን እየተካሄደ ይገኛል።ጷጉሜ 1/2017 ዓ/ም‎"ሰላምን በሰላም ጊዜ...
06/09/2025

በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ እና በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ ወረዳ መካከል የሚካሄድ የእርቅ ሰላም ኮንፍራንስ በባስኬቶ ዞን እየተካሄደ ይገኛል።

ጷጉሜ 1/2017 ዓ/ም

‎"ሰላምን በሰላም ጊዜ እንሰራለን" በሚል መሪ ቃል ጷጉሜ 1 የጽናት ቀን በባስኬቶ ዞን በላስካ ዙሪያ ወረዳ ቡንባሳ_ባስኬቶ ቀበሌ በመከበር ላይ ይገኛል።

በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ እና በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ ወረዳ መካከል የሚካሄድ የእርቅ ሰላም ኮንፍራንስ "ሰላምን በሰላም ጊዜ እንሰራለን" በሚል መሪ ቃል ጷጉሜ 1 የጽናት ቀን ምክንያት በማድረግ በባስኬቶ ዞን በላስካ ዙሪያ ወረዳ ቡንባሳ_ባስኬቶ ቀበሌ በመከበር ላይ ይገኛል።

‎በመርሃ ግብሩ ላይ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳደር ኢንጂነር ፍሬው ፍሻሌው፣ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ በቀለ ኮርማ፣ የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የአስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ታደለ ጋያ፣ የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ ኢንጂነር ዘማች ካንሶ፣ የላስካ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አደም ግርማ፣ የሳላማጎ ወረዳ አስተዳደር አቶ ህጎ ቅጣቱ እና ሌሎች የዞንና የላስካ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች እየታደሙ ይገኛሉ።

ጳጉሜ 2/13 /2017 ዓ.ም ዕለተ እሁድ የህብር ቀንን ምክንያት በማድርግ በላስካ ዙሪያ ወረዳና   ከላስካ ከተማ አስተዳደር የእግር ኳስ ወድድሮች ይካሄዳል። ከቀኑ 7:00 ላይ የላስካ ዙሪ...
05/09/2025

ጳጉሜ 2/13 /2017 ዓ.ም ዕለተ እሁድ የህብር ቀንን ምክንያት በማድርግ በላስካ ዙሪያ ወረዳና ከላስካ ከተማ አስተዳደር የእግር ኳስ ወድድሮች ይካሄዳል።
ከቀኑ 7:00 ላይ የላስካ ዙሪያ ወረዳ መምህራን ከላስካ አስተዳደር መምህራን ጋር የሚደርግ ስሆን ከቀኑ 9:00 ላይ ደግሞ የላስካ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች ከላስካ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር ይደርጋል።
ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ በመሆኑ በዕለቱ የተለያዩ የበጎ አድርጎት ሰጪ ወጣቶች የተለያዩ የበጎ ተግባራት ሥራዎችን ያከናውናል። ድጋፍ ለሚሹት አካላት ድጋፋቸውን በማድረግ ዕለቱ እንደሚከበር የገለፁት የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ኤፌሶን ዳንዳኦ ገልፀዋል።
በዞናችን የስፖርት ዘርፉ እጅግ አኳሪ ተግባር እያመጣ ያለ በመሆኑ መላው ህዝቡ በአንደም የህብር ቀኑን በማክበር በሌላው በከሉ የስፖርት አፍቃራን ቤተሰቦች ነጋዴዎች የመንግስት ሠራተኛች ወድ ተማሪዎች በአጠቃላይ መላው ህብረተሰቡ በዶንኪ ሁሌ ገብ ስቴዲየም መልካም ስነምግባር በመላበስ እንድትገኑና ለሁለቱ ቡድኖች መልካም ዕድል እንድሆንላቸው ተመኝተዋል።

ወይዘሮ ፀሀይ ወርቁ መታሰቢያ በጎ አድራጎት ድርጅት ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አረጋውያንና አቅሜደካሞች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አካሄደ ።‎‎ላስካ፦ነሐሴ 27/2017ዓ.ም(ላስካ ኮሙኒኬሽን)...
02/09/2025

ወይዘሮ ፀሀይ ወርቁ መታሰቢያ በጎ አድራጎት ድርጅት ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አረጋውያንና አቅሜደካሞች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አካሄደ ።

‎ላስካ፦ነሐሴ 27/2017ዓ.ም(ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎ወ/ሮ ፀሐይ ወርቁ መታሰቢያ በጎ አድራጎት ድርጅት ከላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከዙሪያ ወረዳ እና ከላስካ ከተማ አስተዳደር ለተወጣጡ አረጋዊያንና አቅሜ ደካሞች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አካሂዷል።

‎በፕሮግራሙ የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር አንለይ ወንድይፍራው፣ የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤፌሶን ዳንዳኦ እና ተጋባዣ እንግዶች ተገኝተዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር አንለይ ወንድይፍራው በከተማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ ያለውን የበጎነት አገልግሎት በዝህ ደረጃ አድጎ ማየት እጅግ በጣም አስደሳች መሆኑን ገልፀዋል።

‎የህይወት ተግዳሮቷ በበዛበት በዚህ ዘመን ከራሳቸው ደስታ ይልቅ ለሌሎች ደስታ የሚተጉ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ልበረታቱ ይገባል ብለዋል።

‎የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤፌሶን ዳንዳኦ ወ/ሮ ፀሐይ ወርቁ መታሰቢያ በጎ አድራጎት ድርጅት በዙሪያ ወረዳችን በርካታ የበጎ አድራጎት ስራዎችን እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።

‎አክለው በጎነት ሰማያዊ ክብርን የሚያጎናፅፍና የህልናን እርካታ የሚያስገኝ መሆኑን ጠቁመው ፀሐይ ወርቁ መታሰቢያ በጎ አድራጎት ድርጅት ካሉ ድርጅቶች አንዱ እንደሆነ ገልፀዋል።

‎የድርጂቱ አስተባባሪ ወ/ሮ እታፌራሁ ትዕዛዙ በ2014ዓ.ም የተጀመረው የእናታችን ወ/ሮ ፀሐይ ወርቁ መታሰቢያ በጎ አድራጎት ድርጅት ለተከታታይ ዓመታት አቅሜ ደካሞችን ፣ አረጋዊያን እና ተማሪዎችን እየረዳን ቆይተናል ስሉ ገልፀዋል።

‎አክለው ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ መሆኑን ገልፀው ከተረፈን ሳይሆን ካለን በማካፈል ነው በዝህ ተግባር ላይ መሳተፍ የቻልነው ብለዋል።

‎በዛሬው ዕለት ከ110 በላይ የሚሆኑ አረጋዊያንና አቅሜ ደካሞችን ነው በማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ላይ የተሳተፉት።

‎በመታሰቢያ ድርጅቱ በቋሚነት 40 አረጋዊያን እና አቅሜ ደካሞችን እንዲሁም 25 ተማሪዎችን በመያዝ ነው ለአራት ዓመታት የዘለቀው።

‎በድርጅቱ ቋሚ ለሆኑ አረጋዊያን በዛሬው ዕለት ከማዕድ ማጋራቱ ባሻገር ለእያንዳዳቸው 1000(አንድ ሺህ ብር) ለአርባ አረጋዊያን እና ለ25 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ ችለዋል።

‎ድርጅቱ በቀጣይ አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ልዩ የማዕድ ማጋራት በድጋሜ እንደማካሂድ ወ/ሮ እታፈራሁ ገልፀዋል።

‎በመጨረሻም ድርጂቱ የአረጋውያን ማዕከል ህንፃ ግንባታ ለማስጀመር በዝግጅት ላይ እንዳሉ ተጠቁሟል።

‎ ነሐሴ 27/2017ዓ.ም
‎ ላስካ

የላስካ ዙሪያ ወረዳ የክረምት ወጣቶች በጎ ፈቃድ የትኩረት መስክ የሆነው የእግር ኳስ ውድድር በቀን 25/12/2017 ዓ/ም በዶንኪ ሁለ ገብ ስታድዬም ሁለት ጨዎታዎች መደረጉ  ተገለፀ።‎‎(ነ...
31/08/2025

የላስካ ዙሪያ ወረዳ የክረምት ወጣቶች በጎ ፈቃድ የትኩረት መስክ የሆነው የእግር ኳስ ውድድር በቀን 25/12/2017 ዓ/ም በዶንኪ ሁለ ገብ ስታድዬም ሁለት ጨዎታዎች መደረጉ ተገለፀ።

‎(ነሐሴ፦ 25/12/2017 ዓ.ም ላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚንከሽን ላስካ)

‎ የላስካ ዙሪያ ወረዳ የክረምት ወጣቶች በጎ ፈቃድ የትኩረት መስክ የሆነው የእግር ኳስ ውድድር በቀን 25/12/2017 ዓ/ም በዶንኪ ሁለ ገብ ስታድዬም ሁለት ጨዎታዎች መደረጉን የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ።

‎በዝህም ባዬ ድቻ ከጋራ ብሩህ ተስፋ ጋር ባደረጉት ጫዎታ በጋራ ብሩህ ተስፋ 2ለ1 በሆነ ውጤት ጭዎታው በጋራ አሸናፍነት የተጠናቀቀ ስሆን በሁለተኛው ጫዎታ ጤና ንቦች ከጤና ቆርክዎች ጋር ያደረጉት ጫዎታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቅ ተችልዋል፡፡
‎ይህ የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገለግሎት የትኩረት መስክ አካል የሆነው ስፖርታዊ ውድድር ተጠናክሮ እንደምቀጥልና ለውጥ በምያመጣና ስፖርተኖችን ለቀጣዬ ውድድር አቅም የምፈጠር መሆኑን የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ኤፍሶን ዳንዳኦ ተናግሯል፡፡

‎በሁለቱም ጫዎታዎች ቡድኖች ፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነትን በተላበሰ እና በጥሩ ስብዕነና እስከ ጫዎታው ፍፃሜ ድረስ ያሳዩት ስነ-ምግባር እጅግ በጣም የምያስመሰግን መሆኑን የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የስፖርት ዘርፍ ኃላፍ የሆነው አቶ ግዛቸው ግድንባቦ ተናግሯል፡፡


‎ ነሐሴ 25/12/2017ዓ.ም
‎ ላስካ


የክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡‎‎የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት በቀን 25/12/2017 ዓ/ም በዶንኪ ሁለገቢ ስታድዮም ተገኝቶ ተጨ...
31/08/2025

የክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

‎የላስካ ዙሪያ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት በቀን 25/12/2017 ዓ/ም በዶንኪ ሁለገቢ ስታድዮም ተገኝቶ ተጨዋቾች ወደ ሜዳ ከመግባታቸው በፍት አጠቃላይ ለተጨዋቾችና ደጋፊዎች የስብዕና ግንባታ መስጠቱን አስታወቀ፡፡

‎የስብዕና ግባታ ስልጠናው በጽ/ቤቱ ወጣት ዘርፍ ኃላፍ በሆነው በወጣት ታምራት ደጄ የተሰጠ ስሆን ተጨዋቾች ፈፁም የስፖርት ጨዋነትን በመላበስ ከምንም አይነት አሉታዊ ባህርዎች በመላቀቅ ህልሞቻቸው ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው መሠረታዊ የሆኑ የምክር ሀሳቦች ቀርበዋል፡፡

‎ስፖርተኞች ከመጥፎ ስሜት ራሳቸውን በመቆጠብ ያለሙትን ህልማቸውን አጠናክረው በመያዝ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ውስጥ ጉለልህ ሚና መጫወት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

‎በዋናነት የሥልጠናው ማዕከላዊ ሀሳብ ችግሮቻችንን በመነጋገር መፍታት! የምል ስሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ የተሰጠው ሥልጠና በወጣቶች ውስጣዊ የአዕምሮ ማዕከል ላይ አዎንታዊ ለውጥ እንደምያመጣ ነው ወጣት ታምራት የተናገረው፡፡

Adres

Basketo
Łask

Telefon

+251920868197

Strona Internetowa

Ostrzeżenia

Bądź na bieżąco i daj nam wysłać e-mail, gdy Basketo ZoneLaska Zuriya Woreda Youths and Sport Department umieści wiadomości i promocje. Twój adres e-mail nie zostanie wykorzystany do żadnego innego celu i możesz zrezygnować z subskrypcji w dowolnym momencie.

Skontaktuj Się Z Ta Organizacja

Wyślij wiadomość do Basketo ZoneLaska Zuriya Woreda Youths and Sport Department:

Udostępnij

Kategoria