የቤ/ጉ/ክ/መ/የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ምክር ቤት ጽ/ቤት

  • Home
  • Jordan
  • Wadi as Sir
  • የቤ/ጉ/ክ/መ/የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ምክር ቤት ጽ/ቤት

የቤ/ጉ/ክ/መ/የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ምክር ቤት ጽ/ቤት To give support and coordinate the people

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ሊግ ከክልሉ ወጣቶች፣ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመተባበር በሆሞሻ ወረዳ ቱመት ቀበሌ ችግኝ ተተከለ *****(አሶሳ፣ ሀምሌ ...
05/08/2022

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ሊግ ከክልሉ ወጣቶች፣ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመተባበር በሆሞሻ ወረዳ ቱመት ቀበሌ ችግኝ ተተከለ

*****
(አሶሳ፣ ሀምሌ 29/11/2014 ዓ.ም) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ሊግ ከክልሉ ወጣቶች፣ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመቀናጀት በአሶሳ ዞን ሆሞሻ ወረዳ ቱመት ቀበሌ በመገኘት የአረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጠዋል።

ፕሮግራሙን ወ/ሮ ከልቱም ባበክር የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት ኋላፊ እና ወ/ሮ አበራሽ ደጃስ የክልሉ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ም/ኃላፊ ተገኝተው አስጀምረዋል።

ወ/ሮ ዘይነባ ባበክር የሆሞሻ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት ኋላፊ እንደገለፁት በወረዳው በተደረገው ንቅናቄ የወረዳውና የቱመት ቀበሌ ከልጅ እስካዎቂ በነቂስ በመውጣት በዛሬው ቀን ብቻ 4 ሺህ 5 መቶ ችግኝ መትከል መቻሉን ገልፀዋል ።

በያዝነው የክረምት ወቅት እንደ አሶሳ ዞን ዘጠኝ ወረዳዎችና አሶሳ ከተማ አስተዳደር 10 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፤ ከችግኝ ተከላ ባሻገር ደም መለገስ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶችን ማደስ፣ ለትምህርት የደረሱ ህፃናት ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ እና የቦንድ ግዥም መፈፀም እንዳለበት አሳስበዋል።

ወ/ሮ አበራሽ ደጃስ የክልሉ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ም /ኋላፊ በችግኝ ተከላ ወቅት ተገኝተው መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት የዚህ ክረምት በጎ ፍቃድ ስራ አረንጓዴ አሻራ ከማስቀመጥ ባሻገር ሰላም ከሌለ የመጀመሪያ የችግር ገፈት ቀማሾች ሴቶቼና ህፃናት ስለሆኑ ሴቶች ለሰላም ዘብ በመቆም አጋርነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
መረጃው፦የክልሉ ብልጽግና ፖርቲ ጽ/ቤት

01/08/2022
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አሶሳ ከተማ ገቡ**************************(አሶሳ፣ ሐምሌ 24/2014 ዓ.ም) በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመል...
31/07/2022

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ አሶሳ ከተማ ገቡ
**************************

(አሶሳ፣ ሐምሌ 24/2014 ዓ.ም) በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራር ልዑክ ሶሳሳ ከተማ ገባ።

ልዑኩ አሶሳ ህዳሴ አየር ማረፊያ ሲደርስ በክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እና በከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ልዑኩ በክልሉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የሚሳተፍ ሲሆን፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ ምርቃት ላይ የሚታደም ይሆናል።
መረጃው፦የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዩች ጽ/ቤት

ታላቅ ህዝብ ታላቅ የሚያደርገውን ታሪክ ስሰራ ትንንሽ ሀሳቦች  በራሳቸው ይከስማሉ !!
31/07/2022

ታላቅ ህዝብ ታላቅ የሚያደርገውን
ታሪክ ስሰራ ትንንሽ ሀሳቦች በራሳቸው
ይከስማሉ !!

የክልሉ የ2015 በጀት ከ6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኖ በምክር ቤቱ ጸደቀ********************(አሶሳ፣ ሐምሌ 23/2014 ዓ.ም) የክልሉ ምክር ቤት ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል...
30/07/2022

የክልሉ የ2015 በጀት ከ6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኖ በምክር ቤቱ ጸደቀ
********************

(አሶሳ፣ ሐምሌ 23/2014 ዓ.ም) የክልሉ ምክር ቤት ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለ2015 በጀት ዓመት የሚውል ከ6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ አድርጎ አጸደቀ፡፡

በቀረበው የበጀት ረቂቅ ላይ የተወያየው ምክር ቤቱ የ2015 አጠቃላይ የክልሉ በጀት 6 ቢሊዮን 710 ሚሊዮን 502 ሺህ 301 ብር አድርጎ አጽድቋል፡፡

የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዚያድ አብዱላሂ፣ ለበጀት ዓመቱ እንዲውል ከተያዘው በጀት ውስጥ 2 ቢሊዮን 516 ሚሊዮን 465 ሺህ 382 ብር በክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢ የሚሸፈን ነው ብለዋል፡፡

ከበጀቱ ወስጥ 3 ቢሊዮን 690 ሚሊዮን 152 ሺህ 267 የሚሆነው ከፌዴራል መንግስት በድጎማ፣ ቀሪው ደግሞ ከተለያዩ ተቋማት የውስጥ ገቢ፣ ከዘላቂ ልማት ግቦች ማሳኪያ እንዲሁም ከውጪ ከሚገኝ ዕርዳታ መሆኑን የቢሮ ኃላፊው አብራርተዋል፡፡

በምክር ቤቱ ከጸደቀው አጠቃላይ በጀት ውስጥ 256 ሚሊዮን 200 ሺህ ብር የሚሆነው ለዘላቂ ልማት ግቦች ማሳኪያ የሚውል መሆኑም ገልጸዋል፡፡
ክልሉ ያለውን ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት በመጠቀም ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የምክር ቤቱ አባላት ለበጀት ዓመቱ ስራ ላይ እንዲውል የጸደቀው በጀት፣ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ለታለመለት ዓላማ እንዲውል አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የበጀት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ተገቢ ያልሆነ የበጀት ብክነትን መከላከል እንደሚገባም አሳስበዋል።

በተጨማሪም በክልሉ በጸጥታ ችግር ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም፣ የተጎዱ መሠረተ ልማቶችን መልሶ ለማልማትና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎችን ለማስቀጠል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡

በክልሉ የሚካሄደው የመልሶ ማቋቋም ሥራ ከፍተኛ በጀት የሚጠይቅ በመሆኑ የገቢ መሠብሠቢያ አማራጮችን በማስፋት በዕቅድ ከተያዘው በላይ ገቢ መሰብሰብ እንደሚጠበቅም የምክር ቤት አባላቱ አሳስበዋል፡፡
መረጃው ፦የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዩች ጽ/ቤት

የዛሬ አረንጓዴ አሻራችን ጥረት ለነገ ህብስተ-መናችን በረከት ነው!!
21/07/2022

የዛሬ አረንጓዴ አሻራችን ጥረት
ለነገ ህብስተ-መናችን በረከት ነው!!

11/07/2022

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ1ቢሊየን ብር በላይ ተሰበሰበ
ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ ከሐምሌ 1/2013 እስከ ሰኔ 30/2014 ዓ.ም 1ቢሊየን 186ሚሊዮን 297 ሺህ 461ብር ተሰብስቧል፡፡
ድጋፉ የተሰበሰበው ከሀገር ውስጥ ቦንድ ሽያጭና ስጦታ፣ከዲያስፖራ ቦንድ ሽያጭና ስጦታ፣በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ስጦታ አካውንት ገቢ፣ ከፒን ሺያጭ ገቢና ከ8100 አጭር የሞባይል ስልክ መልዕክት አገልግሎት ነው፡፡
የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት 2003 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2014 ዓ.ም ድረስ ከሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ከሚገኙ የዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላት እንዲሁም ከልዩ ልዩ ገቢዎች በአጠቃላይ 16 ቢሊዮን 915ሚሊዮን 312ሺህ 137 ብር መሰብሰቡም ታውቋል፡፡

Address

Wadi As Sir

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቤ/ጉ/ክ/መ/የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ምክር ቤት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share