29/10/2025
ቀን 19/02/2018 ዓ/ም
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የስልጠና ኦረንተሽን መስጠቱ ተገለፀ ።
አድስ አበባ ጥቅምት 18/2018 ዓ/ም
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለሁሉም የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች የስልጠና ኦረንተሽን መስጠቱ ተገልጿል።
ለሁሉም ክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች የተሰጠውን ስልጠና ቀደም ስል ለፌደራል ለአድስ አበባና ድረዳዋ ፖሊስ አባሎችና አመራሮች መሰጠቱን አስታውሰው በስልጠናው ግንዛቤ ውጤታማ ስራ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል ።
የተሰጠው የስልጠና ኦረንተሽን በሀገራዊ ጄኦ-ስትራቴጂያዊ ቁመና ላይ መሠረት ያደረገ በመሆኑ ቀጣይ እስከ ወረዳዎችና ከተማ አስ/ር መዋቅሮች በሚሰጠው ስልጠና ሁሉም የፖሊስ አመራሮችና መኮንኖች እንድሁም የፖሊስ አባሎች እንደሚሳተፉ ነው የተገለፀው።
የስልጠና ኦሬንተሽን የተሰጠው በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት ስሆን ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ስልጠናው ሀገራዊ አህጉራዊና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በማጠን ፖሊሳዊ ተልዕኮን ለመፈፀም የሚያስችል አቅም ለመፍጠር እንደሚያግዝ ነው የገለፁት።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስተዳደር እና ልማት ጠቅላይ መምሪያ ኃላፊ ም/ኮሚሽነር ጀነራል ነብዩ ዳኜ የስልጠናውን መርሃግብር በማብራራት የሰለጠነ የሰው ኃይል ያለበት የፖሊስ ተቋም ፖሊሳዊ አገ/ትን በብቃት በመስጠት ብሔራዊ ጥቅም የማስጠበቅ ግዳጁን መወጣት ይችላል ስሉ አብራርተዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋናው መ/ቤት ስሆን
ዘገባው የኮንታ ዞን ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።
ጥቅምት 19/2018 ዓ/ም