ሸበልበረንታ ወረዳ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉ/ጽ/ቤት women Children and Social Affairs Office

  • Home
  • Ethiopia
  • Yeduha
  • ሸበልበረንታ ወረዳ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉ/ጽ/ቤት women Children and Social Affairs Office

ሸበልበረንታ ወረዳ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉ/ጽ/ቤት women Children and Social Affairs Office ይህ ተቋም የሴቶች ህፃናትና ሌሎች የህ/ሰብ ክፍሎች ሁለንተና?

ሸበል በረንታ ወረዳ       ማርች 8 አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ የካቲት 24/06/2015ዓ/ም በወረዳ ደረጃ ከቀበሌ ከወረዳ ከመጡ ሴቶና የወረዳ አመራሮች ጋር በመሆን ሞቅ ደመቅ ባለ መ...
03/03/2023

ሸበል በረንታ ወረዳ
ማርች 8
አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ የካቲት 24/06/2015ዓ/ም በወረዳ ደረጃ ከቀበሌ ከወረዳ ከመጡ ሴቶና የወረዳ አመራሮች ጋር በመሆን ሞቅ ደመቅ ባለ መልኩ ተከብሯል። በእለቱ ሴቶች በሀገራዊ የመልካም አስተዳደርና የልማት ግንባታ ዙሪያ ያላቸውን ጉልህ ሚንና አቅም ታሪክን በማጣቀስ ለበአሉ የምድረክ መክፈቻ ያደረጉት የወረዳችን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ባንተላይ ደምሰው ናቸው። የሸበልበረንታ ወረዳ ሴ/ህ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት ሀላፊም ሴቶች በአለም የሰላምና የልማት እውደት ውስጥ የሚያሳርፉት አሻራ ከሁሉም በላይ እንደሆነና ይህ ልፋታቸውና ድካማቸው ግን ዛሬም በሚገባው ልክ ቦታ እየተሰጠው ባለመሆኑ ወደፊትም ብዙ የምንሰራቸው ስራወች በመኖራቸው ዛሬም ጠንክረን በአንድነት ልንታግል ይገባል ብለዋል። በእለቱ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ሴት ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት በማበርከት በአሉ ተጠናቋል።

በሸበልበረንታ ወረዳ አግሪሰርቪስ ኢትዮጵያ ከደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በወረዳ ደረጃ በጎጅልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት ያካተተ የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና ...
01/03/2023

በሸበልበረንታ ወረዳ አግሪሰርቪስ ኢትዮጵያ ከደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በወረዳ ደረጃ በጎጅልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት ያካተተ የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና የካቲት 21/06/2015ዓ/ም ተሰጠ ።

ሴትነት የጥንካሬ ትምሳሌትነት ነው ።
30/03/2022

ሴትነት የጥንካሬ ትምሳሌትነት ነው ።

የሸበል በረንታ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8 ዛሬ መጋቢት 20/2014ዓ/ም በሸበል በረንታ ወረዳ የህዝብ መሰብሠቢያ አዳራሽ ከቀበሌና ከወረ...
29/03/2022

የሸበል በረንታ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8 ዛሬ መጋቢት 20/2014ዓ/ም በሸበል በረንታ ወረዳ የህዝብ መሰብሠቢያ አዳራሽ ከቀበሌና ከወረዳ ጥሪ ከተደረገላቸው ሴቶችና የክብር እንግዶች ጋር በደማቅ ሁኔታ ተከበረ ።

25/03/2022
24/03/2022
24/03/2022

ማርች 8 (የሴቶች ቀን) ለምን ይከበራል?
****************

• ከ3 ሴቶች አንዷ በህይወት ዘመኗ ተደፍራለች (UN)
• በአለማችን ዕድሜቸው ከ15 እስከ 44 የሆኑ ሴቶች ከካንሰር፣ ከጦርነት፣ ከመኪና አደጋና የወባ በሽታ ይልቅ አስገድዶ የመደፈር ስጋት ያሳስባቸዋል (UN)
• 603 ሚሊዮን ሴቶች ጾታዊ ጥቃት ወንጀል ባልሆነባቸው አገራት ውስጥ ይኖራሉ (UN)
• በአሁኑ ወቅት በአለማችን 700 ሚሊዮን ያህል ሴቶች ዕድሜያቸው 18 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ሲሆን 250 ሚሊዮን ሴቶች ደግሞ ዕድሜያቸው 15 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ናቸው (UNICEF)
• በየአመቱ በአለም ላይ ከ600-800 ሺህ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውሮች ይካሄዳሉ፡፡ ከሚካሄደው የህገ ወጥ ሰዎች ዝውውር ከአምስት አራቱ ሴቶች ነው፡፡ (Trafficking.org)
• በየአመቱ 62 ሚሊዮን ሴቶች የትምህርት ዕድል አያገኙም (Makers)
• የአለማችን116 ሚሊዮን ሴት ተማሪዎች (25 በመቶ ያህሉን የሴት ተማሪዎችን ቁጥር ይዛል) አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አያጠናቅቁም፡፡
• በአለማች ለሴቶች የሚከፈለው ክፍያ ከወንዶች አንጻር ከ60-75 በመቶ ያነሰ ነው (PBS)
• 155 አገራት ሴቶችን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚገድብ ህጎች ሲኖራቸው 100 አገራት ደግሞ ሴቶች የሚሰሩትን የስራ አይነት ገድበዋል (The Guardian)
• በየደቂቃው አንድ እናት በወሊድ ምክንያት ትሞታለች (UN)
• በአለማች 200 ሚሊዮን ሴቶች በግዳጅ ይገረዛሉ (World Health Organization)

24/03/2022

ሴቶች የችግሮቻችን ሁሉ
መፍቻ ቁልፍ ናቸው ።
ለሁለንተናዊ እድገትን ካሰብን
ትኩረታችን እቁልፉ ላይ መሆን አለበት።

የሴቶች ቀንየምስራቅ ጎጃም ዞን ሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በዞን ደረጃ አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በአለም አቀፍ ደረጃ     ለ111ኛ ጊዜበአገር አቀፍ ደረጃ ለ46ኛ ጊዜ   ...
08/03/2022

የሴቶች ቀን
የምስራቅ ጎጃም ዞን ሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በዞን ደረጃ አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በአለም አቀፍ ደረጃ
ለ111ኛ ጊዜ
በአገር አቀፍ ደረጃ ለ46ኛ ጊዜ

በሚል መሪ ቃል ከሁሉም የምስ/ጎ/ዞን ወረዳወች ጥሪ ከተደረገላቸው ሴቶችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ዛሬ 29/06/2014 ዓ/ም በድምቀት እያከበረነው።

ሴት
ሀገር ናት
ትዳር/ቤት ናት
እናት ናት
ሚስት ናት
እህት ነት
ክብር ለሴቶቻችን

05/03/2022

የካቲት 2014ዓ/ም የዕድውሃ
መግቢያ፡-
በወረዳችን የተለያዩ ጎጅልማዳዊ ድርጊቶች የፈጸማሉ እነዚህ ጎጅልማዳዊ ድርጊቶ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሆን ተብሎ ወይም ባለማወቅ ሲወርድ ሲዋረድ ከአያት ቅድመ አያት እንደመልካም ነገር እየተወራረሰ የመጣና ዛሬም ስልቱን እየቀያየረ እየተፈጸመ ያለ ተግባር ነው ፡፡ከነዚህም ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች መካከል ያለእድሜ ጋብቻ አስገድዶ መድፈር አድፋፊ ድግስ የህፃናት ጉልበት ብዝበዛ በቀል(ደም መልስ) በዋናነት የሚጠቀሱና ዛሬም ፈተና ሆነውብን ያሉና ያልተሻገርናቸው አስከፊ ክስተቶች ሆነው ቀጥለዋል፡፡ በመሆኑም በርካታ እህቶቻችን፣ ልጆቻችን ፣ ተማሪዎቻችንና ሁሉም የማህበረሰባችንን የኢኮኖሚ አቅም እያሽመደመዱ ንሮአችን ከድጥ ወደ ማጡ እንዲሆን ሲያደርጉ አንዳንዶቹ ጎጅልማዳዊ ድርጊቶች ደግሞ በፈለግንው ሰአትና ቦታ ተንቀሳቅሰን እንዳንሰራ እንዳንማር ከማድረጋቸውም በላይ ህይወታችንን እየቀጠፉ በንሮአችን ላይ ከባድ ስጋት ደቅነውብናል።
እንዲሁም በአሁኑ ሰዓት ሀገራችን ያለችበትን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ በሚደረገው ርብርብ ላይም በእንቅርት ላይ ጀሮ ደግፍ እንዲሉ ከባድ ተጽእኖ እያሳደሩብን ነው፡፡
ስለሆነም የክልላችን መንግስት በጦርነቱ የወደመውን ሀብት ለመተካት እና ወደ ነበረበት ለመመለስ የተለያዩ መሰረታዊ ጉዳዮች እንዳይፈጸሙ በአዋጅ አስቀምጧል ፡፡ስለዚህ ይህን የህልውና አደጋ ከግምት ውስጥ በማስገባትና ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች የሚያስከትሉትን የኢኮኖሚ የማህበራዊና የሞራል ድቀት በመገንዘብ ጎጅልማዳዊ ድርጊትን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ ከወረዳ እስከ ቀበሌ የተቋቋመውን ኮማንድ ፖስት በመደገፍና በማገዝ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ተዘጋጅቷል፡፡
የስልጠናው ዓላማ
በወረዳችን ውስጥ የሚስተዋሉትን ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች ለማስወገድ ይቻል ዘንድ እንዲሁም ማህበረሰቡ በጎጅልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ ያለውን የተዛባ አመለካከት መቀልበስና ከጎጅልማዳዊ ድርጊት ነፃ የሆነ ማህበረሰብ ለመፍጠር የሚያስችል ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው፡፡
የስልጠናው አስፈላጊነት
ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶች በተለይ በሴቶችና ህጻናት እንዲሁም በሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ላያ እያደረሱት ያለው የጤና፣የአካል፣የኢኮኖሚያ የስነ-ልቦና ድቀት አስከፊ በመሆኑያለእድሜ ጋብቻ ህጻናትን ያለ እድሜያቸው ሊሸከሙት ከማችሉት ለተመሰቃቀለ የህይወት አዙሪት የሚዳርግ በመሆኑ ጎጅልማዳዊ ድርጊት ከግዜ ወደ ጊዜ ይዘቱንና ስልቱን እየቀያየረ የመጣ አስከፊ ተግባር በመሆኑ በተለይ አሁን ካለንበት የህልውና ዘመቻ ጋር ፍጹም የተቃረነና ሌላ የህልውና ስጋት በመሆኑ በጎልድ ዙሪያ የማህበረሰቡ አስተሳሰብና አመለካከት ሊስተካከልና ወደ ተግባር ለቀየር ባለመቻሉ ይህ ሰነድ ተዘጋጅቶ ግናዛቤ መፍጠሩ አስፈላጊ ሆኗል፡፡
ልማዳዊ ድርጊት ምንነት
ልማዳዊ ድርጊት ማለት ከትውልድ ትውልድ እየተሸጋገረ የመጣ እረዥም ዕድሜ ያስቆጠረ እንደየ አካባቢው ሁኔታ በተለያየ አይነትና ደረጃ በህብረተሰቡ ውስጥ በልማድ እየተፈጸመ ያለ ትግባር ነው፡፡
ልማዳዊ ድርጊት በሁለት (2 ) ይከፈላል
1.ጠቃሚ ልማዳዊ ድርጊት
2.ጎጅ ልማዳዊ ድርጊት
ጠቃሚ ልማዳዊ ድርጊት
ጠቃሚ ልማዳዊ ድርጊት ማለት ሳይንስን ወይም ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ ለህብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ባህላዊ እሴቶች መጎልበት መልካም ዋጋ ያላቸውን ልማዳዊ ድርጊቶች ጠቃሚ ልማዳዊ ድርጊቶች እንላቸውለን፡፡
ለምሣሌ፡- እቁብ ፣ እድር ፣ የደቦ ስራወች ወዘተ
ጎጅልማዳዊ ድርጊት
ጎጅ ልማዳዊ ድርጊት ማለት ሳይንሳን ወይም ህማኖታዊ መሰረት ሳይኖረው ለህብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ባህላዊ እሴቶች መጎልበት መልካም ዋጋ የሌላቸው እንዲሁ በዘልማድና ዘፈቀደ በማንኛውም ማህበረሰብ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ የመጣ እረዘም ያለ እድሜ ያስቆጠረና የተወሰነ ይህ/ሰብ ክፍልን ፍላጎት ለማስተናገድ /ለማስደስሰት/ ሲባል በሌሎች ላይ ኢኮኖሚያዊ ስነ -ልቦናዊና ማህበራዊ ጉዳትና ጫና የሚያስከትሉ ድርጊቶች ናቸው፡፡
የዚህ ድርጊት ውጤቱ የህብረተሰባችንን የኢኮኖሚ ፣ የጤና ፣የስነ-ልቦናና የአካል ደህንነት አደጋን ያስከትላል፡፡በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ መጥፎ ተግባር የሚፈጸመው በህ/ሰቡ ዘንድ ትክክልና ጠቃሚ ነው ተብሎ መሆኑ ነው።
ለምሳሌ፡-አድፋፊ ድግስ፦ ...............በእድ አምልኮ፦...........ያለእድሜ ጋብቻ….
የነፍስ ግድያ …...
ደም ብቀላ (ነፍስ ማጥፋት)፦
በወረዳችን በጣም በሚያሳዝንና በሚሰቀጥጥ ሁኔ ከአመት አመት የከፋ የመጣው አሳዛኝ ጎጅልማዳዊ ድርጊት የነፍስ ማጥፋት (ብቀላ) ነው ። በዚህ ዘግናኝ ተግባር ሴቶች ፣ ህፃናት ፣ ወንዶችና አዛውንቶችን በማያውቁት ባልተሳተፉበት የክፋት ጥግ መስዋት ሆነዋል ። ይህ ዘግናኝና ሰቅጣጭ ድርጊት ህፃናትን ያለቤተሰብ እናትና አባቶችን ያለ አጋር አሩጋውያንን ያለጧሪ የመከራ ማቅ አልብሶ የሰቀቀን ህይወት እንዲገፉ ያደርጋል።
የሰው ልጅ ግድያን በተመለከተ ሁለት አይነት መረጃ ነው ያለው
ከወረዳ ሰላምና ደህንነት ቢሮ በተገኘ መረጃ መሰረት በዚህ 6ወር ውስጥ የተፈፀመ መረጃ
ወ 23
ሴ 4
ድ 27 ሲሆን
ከወረዳ ፓሊስ ጽ/ቤት በተገኘ መረጃ መሰረት ደግሞ እስከዚህ ወር ድረስ በሰቅጣጭ ሁኔታ የተፈፀሙ የነፍስ ግድያወች
ወ 23
ሴ 2
ድ 25
ሲሆን በዚህ የግድያ ወንጀል ነፍሰጡር ሴቶች ከነልጆቻቸው የሰውልጅ ከሚያስበው በላይ ሰቅጣጭ በሆነ ፍፁም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ተጨፍጨፈዋል ። ይህን አሳፋሪ የግድያ ተግባር የፈፀሙ ገዳዮች ብዛትን ስንመለከትም ከሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት በተገኘ መረጃ
ወ 26
ሴ ዐ
ድ 26 ሲሆን በዚህ ወንጀል አንድ ወንጀለኛ ከአንድ በላይ ሰው እንደገደለ ሲገልፅ
ከፖሊስ ጽ/ቤት በተገኘ መረጃ ደግሞ
ወ 28
ሴ 0
ድ 28 መሆናቸውን ያሳያል ። በዚህ መረጃ መሰረት ደግሞ በአንድ የወንጀል ድርጌት ከአንድ በላይ ወንጀለኛ መሳተፉቸውን ።
በዚህ አሳዛኝ የነፍስ ግድያ ምክንያት ህፃናት ያለአሳዳጊ አሩጋውያን ያለቀባሪ ቀርተዋል ዘመድ አዝማድ ከአደገበት ቀየ ተሰደው ተፈናቅለው በተሰደዱበት ቦታም የሰቀቀንና የስጋት ህይወት ተጋርጦባቸው ለችግር ተጋልጠው የመከራ ህይወት ይመራሉ። ከወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት በተገኘው መረጃ መሰረት ከላይ በተፈፀሙት የነፍስ ማጥፋት ወንጀሎች ምክንያት ተፈናቅለው ለችግር የተጋለጡ ወገኖቻችንን መረጃ ስናይ


ድ ናቸው።
ይህ ድርጊት በጣም የሚያሳዝነው ችግሩ በሟችና በገዳይ ብቻ የሚያበቃ ድርጊት አለመሆኑ ነው ። እነዚህ ዘግናኝ ድርጊቶች ሲፈፀሙ በእግዛብሄር ጥበብና ቸርነት ከዚህ መአት ቆስለው ከሞት የተረፉ ቁስለኛችም የተመዘገቡ ሲሆን


ድ ። ናቸው ። ግን ወገኖቸ የዚህ ችግር ማብቂያው የት ነው ? ምን እስከምንሆን እየጠበቅን ነው ? ከንፈር እየመጠጥን በእንባ እየተራጨን የምንወዳቸውን ሰወች በገዛ እጃችን እየገደልን ስንቀብር እንኖር ይሆን ? ነው ከንፈር ከመምጠጥ የዘለለ ተግባራዊ እርምጃ በመውሰድ የሰው ልጅ ግድያን እናስቆም ?
በወረዳችን ውስጥ በጣም በአሳሳቢ ሁኔታ እየጨመረ የመጣው የሰው ልጅ ግድያ ምክንያቶቹ በርካታ ቢሆኑም ከፈጣሪ በታች ከሰው ልጅ ክቡርነትና ትልቅነት አንፃር ስናቸው እዚህ ግባ የሚባሉ አደሉም ። ነገር ግን ለሰው ልጅና ለሰውነት ያለን አስተሳሰብና አመለካከት ከአእምሮአችን እየተሟጠጠ በመምጣቱና ለረከሰ መንፈስ ተገዥ ሆነን የእንሰሳነትና የአውሬነት በሀሪ ተላብሰን እሰበሳችን ተናክሰን ለመጫረስ ተግተን ተገኝተናል። ይህ የአስተሳሰብ ፣ የስብዕናና የሰውነት ድርቅ የመታው ጨካኝና አረመኔ ትውልድ እንዲፈጠር ያደረገው ደግሞ ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ ሳይሆን የእናትና የአባት የአስተዳደግ ችግር ፣ የሀይማኖት አባቶች ትውልዱ ፈሪሃእግዛብሄርን ተላብሶ እንዲያድ ለማድረግ የሚጠበቅባቸውን ያህል ሀይማኖታው ግዳጃቸውን መወጣት አለመቻላቸው ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና መንግስት ችግሮች ሲከሰቱ ተሎ ብሎ በሽምግልናና በህግ ችግሮች እልባት እንዲያገኙ አለማድረግ እንዲሁም በሀገራችን የህግ መአቀፍ የተካቱ የነፍስ ግድያ ወንጀል መቅጫ ህጎች ለዘብተኛ መሆናቸው ጉዳውን እንዲከብድ አድርጎታል። ስለዚህ ከእኛ የሚጠበቀውን ማድረግ ባለመቻላችን ዛሬ የዘራንውን እንድናጭድ ተገደናል ።
ስለዚህ በቀጣይ ምን ብናደርግ
ይህን ትውልዳችንን ከገጠመው
የስብዕና ፣ የአመለካከትና
የአስተዋይነት ድርቅ ልናወጣው እንችላለን ?
የሰው ልጅ ግድያ መንስኤዎች
1.የንብረትና የመሬት ጠብ
2.በሴት የሚመጣ ጠብ
3. እራስን አጀግኖ ሌላውን አኮስሶ ማየት
4. ሰው መግደልን እንደጀግንነት ማየት
5. መግደልን እንደ አማራጭ መፍትሄ ማየት
6.የሀገር ሽማግሌዎች ችግርች ሲፈጠሩ ፈጥነው አለማስታረቅ
7. ማንኛውም ነገር ሁሉ ከሰው በታች መሆኑን አለመገንዘብ
8.ግድያን ማስቆም የሚችል ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ አለመኖር ከብዙ በጥቂቱ ለሰው ልጅ ግድያ መንስኤዎች ናቸው።
ያለእድሜ ጋብቻ
ያለእድሜ ጋብቻን ለማስቀረት በርካታ ጥረቶች ቢደረጉም ከመቀነስ ይልቅ ቅርፁን እየቀያየረ ቁጥሩ እያሳሰበ መቷል። ለመነሻ ያህል በሚያሳዝን ሁኔታ በዚህ አመት እስከዚች ቀን ድረስ ከ11 ቀበሌዎች ብቻ በተሰበሰበ መረጃ መሰረት ያለእድሜ ጋብቻ ሊፈፀምባቸው ትምንምን የተበላባቸው ህፃናት
ወ = 33 ሴ = 111 ድ = 144 ናቸው
በቀበሌ ደረጃ ለማየት ያህል
1.ቃርማ ........... ወ 6 ሴ 12 ድ 18
2.የጁ ................ወ 4 ሴ 3 ድ 7
3.ሌዲ ............... ወ 2 ሴ 10 ድ 12
4. መርገጭ........... ወ 0 ሴ 2 ድ 2
5. አብረቁይ .......... ወ 1 ሴ 9 ድ 10
6.ወይንየ............... ወ 7 ሴ 10 ድ 17
7. ወቦ...................ወ 7 ሴ 27 ድ 34
8. ገዳያሱ..............ወ o ሴ 4 ድ 4
9. አንሸብ...............ወ 2 ሴ 12 ድ 14
10. ገብሲት............ወ 2 ሴ 11 ድ 13
11.ቦንያ................ ወ 7 ሴ 10 ድ 17
ጠለፍ ፦
ጠለፋን በተመለከተም በአመቱ አሳፋሪ ክስተቶችን እያሳለፍን ያለንበት ሁኔታ በመኖሩ ልንሻገርንው ያልቻልው ተግባር በመሆኑ እናቶቻችንና እህቶቻች በፈለጉት ጊዜ በነፃነት ተንቀሳቅሰው እንዳይሠሩና እንዳይማሩ በማድረግ ሁኔ የስጋት ህይወት እንዲገፉ ተፈርዶባቸዋል። በዚህ አመትም
- በቃርማ ቀበሌ ወ 0 ሴ 1 ድ 1 አስተናግደናልሁን ።
የህጻናት ጉልበት ብዝበዛ፣
በተለያየ ችግር ምክንት ወላጆቻውን ያጡና ከወላጆቻቸው ጋር የሚኖሩ በርካታ ህፃናት ጉልበታቸው በተለያየ መንገድ ይበዘበዛል ከአቅማቸው በላይ ስራ እንዲሰሩ ይገደዳሉ ።ይህ ተግባር አሁንም በስፋት የሚፈፀም ችግር በመሆኑ ትኩረት የሚያሻ ተግባር ነው ።
ሰው ሲሞት ፊት መንጨት፣
ሌላው አሳዛኝ ጎጅ ልማዳዊ ድርጊት ደግሞ አስገድዶ መድፈር ነው ።
ይህ አሳፋሪ ተግባርም በወረዳችን ውስጥ አሳሳቢ እየሆነ መቷል ። በመሆኑም በዘንድሮው አመት
ወ 0
ሴ 1 አባስልማ ቀበሌ
ድ 1
አስገድዶ መደፈር መፈፀሙን ያሉን መረጃዎች ያመለክታሉ ።
በአጠቃላይ የጎጅ ልማዳዊ ድርጊት መንስኤዎች ፦
የጎጅ ልማዳዊ ድርጊት መንስኤዎች በአብዘሃኛው የበጎነት ሽፈን የተሰጣቸው ቢሆንም እውነተኛ መንስኤዎቹ ኋላቀርነትበህብረተሰባችን ዘንድ የተንሰራፋው የወንዶች የበላይነት
አስተሳሰብ ባህላዊ ተፅእኖ ሃይማኖታዊ ተፅዕኖ ሴቶች የወንዶች የኢኮኖሚ ጥገኛ መሆን የጠበቀ የህግ ማዐረቀፍ አለመኖር የጉዳዩን አሳሳቢነት አለመረዳት ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን በዚህ ዘርፍ የተደረጉ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ጎጅልማዳዊ ድርጊት የሚያስከትለው ጉዳት በአጠቃላ ጎጅልማዳዊ ድርጊት የማህበረሰባችንን ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ፖለቲካዊና ባህላዊ ድቀትንና መመሰቃቀልን በመፍጠር አስከፊ የህይወት ውጣውረድ እንድንመራ እንገደዳለን ጎጅልማዳዊ ድርጊትን ለማስወገድ ወይም ለመቀነስ መሰራት ያለባቸው ጉዳዮች መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በጎጅልማዳዊ ድርጊት ላይ በቅንጅት መስራት ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያለውን ጎጅልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ኮሚቴ ፋንክሽናል ማድረግ ማጠናከር በትምህርት ቤቶች ያሉ የተለያዩ ክበባትን በመጠቀም በጎልድ ዙሪያ የማህ/ሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ የህግ አካላት በትክክል የተደነገጉ ድንጋጌወችን በተግባር ላይ እንዲውሉ ማድረግ የንቅናቄ መድረኮችን በመፍጠር የህ/ሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ እድሮች በጎጅልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ ያላቸውን አመለካከት በማስተካከል የህግና የውስጠደንብ መአቀፎችን መሰረት በማድረግ ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ ማድረግ የሀይማኖት አባቶች ከማስመሰል አሰራር በመውጣት ኮስታራ እርምጃ እንዲወስዱ ማድረግ አስፈላጊ ነው።
የመወያያ (ነጥቦች )ሃሳቦች
- የሰው ልጅ ግድያ በጣም በሚያሳስብ ሁኔታ ወድ የሰው ልጅ ህይወትን ሲቀጥፍ ማየትና እያነቡ መሸኘት የለት ተለት ክስተት ሆኗል ምን ይሻላል
- ህፃናት ፣ ሴቶችና ተማሪዎች በማያውቁት በማይገባቸው ጉዳ የደም መመለሻ እየሆኑ እየረገፉ ነው ለምን ?
- ጎጅልማዳዊ ድርጊትን እንዴትት ታውታላችሁ
-ያለእድሜ ጋብቻ መልኩን እየቀያየረ በጣም እየተወሳሰበና እያደገ መቷል ምን ይሻላል
-አድፋፊ ድግስ በጣም አሳሳቢ በሆነ ደረጃ እየተፈጸመ ነው ምን ይሻላል
-እድሮች በማህበረሰባችን ማህበረዊ ክዋኔዎች ላይ ያላቸው ሚና የጎላ ነው በጎጅ ልማዳዊ ድርጊትና በነፍስ ግድያ ላይ ምን አይነት ሚና ይጫዎቱ ?
-መልካም እሴቶቻችንን ለማጎልበት ከማህበረሰቡ፣ ከመንግስትና ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች ምን ይጠበቃል ?
-በጎጅልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ የቀጣይ አቅጣጫዎቻችን ምን መሆን አለባቸው?

የጎጅልማዳዊ ድርጊትን ለማስወገድ በወረዳና በቀበሌ ደረጃ የተቋቋሙ ሁለት አይነት የጎጅልማዳዊ አስወጋጅ ኮሚቴወች ሲሆን አወቃቀር በተመለከተ
የጎጅልማዳዊ ድርጊት አብይ ኮሚቴ በወረዳ ደረጃ
1.ዋና አስተዳዳሪ ኃላፊ -------- ሰብሳቢ
2.ሴ/ህ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት ኃላፊ-----ም/ሰብሳቢ
3..ባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ -------- ፀሃፊ
4.ድርጅት ጉዳይ ጽ/ቤት--------------- አባል
5.ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ------------------ አባል
6.አስ/ጽ/ቤት ኃላፊ-------------------- አባል
7.ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ------------------ አባል
8.ገ/ፕላን ጽ/ቤት ኃላፊ---------------- አባል
9.ቅ/ት ጽ/ቤት ሀላሪ ኃላፊ------------- አባል
10.ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ----------------- አባል
11.ሴቶች ማህበር ኃላፊ--------------- አባል
12.ወጣት ማህበር ኃላፊ-------------- አባል
13.ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ኃላፊ--- አባል
14.እስልምና ቤተ እምነት ኃላፊ-------- አባል
15.ግብርና ጽ/ቤ ኃላፊ----------------- አባል
16.አብቁተ ጽ/ቤት ኃላፊ--------------- አባል
17.ኮምንኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ----------- አባል
እንዲሁም የጎጅ ልማዳዊ ድርጊት አስወጋጅ ቴክኒክ ኮሚቴ አወቃቀር
በቀበሌ ደረጃ
1.የቀበሌ አስተዳዳሪ ኃላፊ ------- ሰብሳቢ
2.የቀበሌ ሴቶች ጉዳይ --------ም/ሰብሳቢ
3.ስራ አስካጅ ------------------------- ፀሃፊ
4.ሴቶች የልማት ቡድን ሰብሳቢ------ አባል
5.የቀበሌ ሴቶች ማህበር ---------- አባል
6.አስ/ጽ/ቤት ኃላፊ------------------- አባል
7.የቀበሌ ወጣቶች ማህበር ---------- አባል
8.ሃያማኖትተወካይ-------------------አባል
9..የእድር ተወካይ …………....... አባል
10. የት/ት ቤት ር/መምህር……... አባል
11.የግብርና ተጠሪ--................ አባል
12.የሀገር ሽማግሌ….............. አባል
13. የቀበሌ ፖሊስ……………. አባል
14. ሌሎች የቀበሌ ሙያተኞች-- አባል

04/03/2022

የሸበል በረንታ ወረዳ ሴ/ህ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት እና ከአግሪሰርቪስ ኢትዮጵያ ጽ/ቤት ጋር በጎጅልማዳዊ ድርጊት ዙሪያ የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና ላይ በተከበሩ አቶ ታዴ ከቀረበው ግጥም በጥቂቱ

04/03/2022

Let us prevent harmful cultural action with Shebel Berenta District Women's and Social Affairs Office

Address

Yeduha

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሸበልበረንታ ወረዳ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉ/ጽ/ቤት women Children and Social Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share