CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wolkite
  • CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት

CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት "Integrity is doing the right thing, even when no one is watching. An auditor's job is to make sure everyone is watching."

4/7/2018 ዓ.ምአለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8)  ተከበረ።የሴቶች ቀን (ማርች 8)  በዓለም ለ115ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ " የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ...
14/03/2026

4/7/2018 ዓ.ም
አለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8) ተከበረ።

የሴቶች ቀን (ማርች 8) በዓለም ለ115ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ " የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ተከብሯል ።

ወ/ሮ ገነት ደምስ የመስሪያ ቤቱ የሴቶችና ህጻናት ጉዳዮች ተወካይ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን መከበር ሴቶች በተዛቡ አመለካከቶች የተነሳ የሚደርሱባቸውን ልዩ ልዩ ጥቃቶች በመታገል ፍትህ ፣ሰላም ፣ልማትና ሁሉ አቀፍ የሆነ እድገትና ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ያስቻለ ንቅናቄ እንደሆነ ገልፀዋል።
በሀገራችን ሴቶች የሚያገል የጭቆና ጊዜያቶች የተሻገርን ቢሆንም አሁንም ቢሆን ህግን ከማስከበር አንፃር ,የውሳኔ ሰጭነት ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም የነበሩ ሴቶች የሚደርስባቸውን ዘርፈ ብዙ ጥቃትና ችግሮች በመቋቋም አሁን ላይ የመጡ ለውጦች ማስቀጠልበቀጣይም ሁለንተናዊ ተሳትፏቸውን ለማሳደግ መረባረብ ይገባልም ሲሉ ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን ገልፀዋል።

በኦዲት ተግበር የስነ-ምግባር መርሆዎችን( ቅንነት፡አለማዳላት፡ ሚዛናዊነት፡ብቃት፡ሚስጥር ጠባቂነት፡ገለልተኝነትን) ማካተት  መደበኛ የአሰራር ደንቦችን መከተል ብቻ ሳይሆን ህዝባዊ አመኔታን ማ...
11/12/2025

በኦዲት ተግበር የስነ-ምግባር መርሆዎችን( ቅንነት፡አለማዳላት፡ ሚዛናዊነት፡ብቃት፡ሚስጥር ጠባቂነት፡ገለልተኝነትን) ማካተት መደበኛ የአሰራር ደንቦችን መከተል ብቻ ሳይሆን ህዝባዊ አመኔታን ማሳደግና የኦዲት ሙያ የማዝለቅ ቁልፍ መገለጫ ነዉ !

ዓለም አቀፍ የጸረ ጾታዊ ጥቃት እና   አለም አቀፍ የኤች አይ ቪ ቀን  የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  ዋና ኦዲተር መ/ቤት አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል፡፡...
10/12/2025

ዓለም አቀፍ የጸረ ጾታዊ ጥቃት እና አለም አቀፍ የኤች አይ ቪ ቀን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል፡፡

‎ ህዳር/ 2018

‎የዘንድሮው የጸረ -ጾታዊ ጥቃት ቀን “ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ” በሚል መሪ ቃል፣ እንዲሁም ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይ ቪ ምላሽ ዘላቂነት እናረጋግጥ በሚል መሪ ቃል መከበሩ ተመላክቷል፡፡
‎በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር አቶ መሀመድ አብድላ ጾታን መሠረት ያደረገ አካላዊ ፣ ወሲባዊ ፣ ስነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቃቶች በሀገራችን ከባድ ችግር እየፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል። ከ 50% በላይ የህዝባችን ቁጥር የሚይዙ ሴቶች ላይ ጥቃት ማድረስ የምንመኘው ልማት ለማምጣት ሴቶችን ከጥቃት መከላከል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
‎ የስረዓተ ዖታ እና የኤች አይ ቪ ጉዳይ በልማት ማካተት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የስራ ሂደት ተወካይ ወ/ሮ ገነት ደምስ በስርአተ ፆታና በኤች አይ ቪ ዙሪያ የተዘጋጁ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት  አመራርና ሰራተኞች  በስነ-ምግባር መርሆዎች ዙሪያ  ዉይይት አደረጉመኢዋኦ ህዳር 12/2018 ዓ.ም. ወልቂጤ፡ የማ/ኢ/ክ/መ/ዋና ኦዲተር   መ/ቤት  አመራርና ...
21/11/2025

የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት አመራርና ሰራተኞች በስነ-ምግባር መርሆዎች ዙሪያ ዉይይት አደረጉ
መኢዋኦ ህዳር 12/2018 ዓ.ም. ወልቂጤ፡ የማ/ኢ/ክ/መ/ዋና ኦዲተር መ/ቤት አመራርና ሰራተኞች የስራ ስነ-ምግባር አስመልክቶ ዉይይት ያደረጉ ሲሆን መድረኩን የሰዉ ሀብት ስራ አመራር ዳይሬክቶሬት ዳይረክተር ሀስና ሀሊል በንግግር ከፍተዋል፡፡
የዋና ኦዲተር መ/ቤት የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ተወካይና የል/ዕ/በ/ዝ/ክትትልና ግብረ-መልስ ዳይሬክቶሬት ዳይረክተር ተወካይ አቶ ሲሳይ ጥላሁን የመወያያ ሰነድ ካቀረቡ በኋላ ሰራተኞች ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄ አንስተዋል፡፡ከነዚህም መካከል የቀረበዉ ሰነድ አስፈላጊና ይዘቱም ከተቋም ባለፈ ለግል ህይወት የሚጠቅም ግንዛቤ የተገኘበት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡በተጨማሪም ለአንድ ተቋም አላማና ግብ መሳካት ብቻ ሳይሆን ለሰራተኞች አንድነትና በአንድነት ለጋራ ራዕይ መቆም ስነ-ምግባር እጅግ አስፈላጊ ስለመሆኑ ገልፀዉ ሰነዱና አቀራረቡ ሁሉም ሰራተኛራሱን እንደመስታወት ለመመልከት የሚያስችል በመሆኑ ለሁሉም ሰራተኞች ተመሳሳይ ስልጠና ቢሰጥ ሲሉ አስተያየታቸዉን አቅርበዋል፡፡
በመጨረሻም አቶ ሲሳይ ጥላሁንና ሀስና ሀሊል ከስልጠናዉ መልካም ዉጤት እንደሚገኝበት እምነታቸዉ መሆኑን ተናግረዉ መሰል ዕድል ለሁሉም ሰራኞች እንዲደርስ ከበላይ ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር ሊደገም እንደሚችል ጠቁመዉ ስብሰባዉ ተጠናቋል፡፡
ዘገባዉ የመ/ቤቱ ኮሙንኬሽንና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ነዉ፡፡

መስከረም 13/01/2018የማእከላዊ  ኢትዮጲያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና  የ2018 በጀት አመት እቅድ በወልቂጤ ከተማ  ገመገመ።የማእከላዊ  ኢትዮጲያ...
23/09/2025

መስከረም 13/01/2018
የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2018 በጀት አመት እቅድ በወልቂጤ ከተማ ገመገመ።

የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም የመ/ቤቱ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት በዛሬው ዕለት የተገመገመ ሲሆን ሰነዱ በመ/ቤቱ የልማት እቅድና በጀት ክትትል ግምገማና ግብረ መልስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ የሆኑት አቶ ሲሳይ ጥላሁን ቀርቦዋል፡፡ የቀረበዉን ሰነድ መነሻ በማድረግ በአፈጻጸም ወቅት የታዩ ደካማና ጠንካራ ጎኖች ፣ በዕቅድ ተይዘው ያልተከናወኑ ተግባራት እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮች ቀርበው ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

የማእከላዊ ኢትዮጰያ ክልል መንግስት ዋና ኦዲተር ክብርት ወ/ሮ ፈዲላ አደም መድረኩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በበጀት አመቱ ተቋሙ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን ገልጸዉ የህዝብና የመንግስት ሀብት በአግባቡ ስራ ላይ እንዲውል ለማድረግ ኦዲተሮች ለኦዲት ጥራት ትኩረት በመስጠት ሙያዊ ስነ-ምግባር ተከትለው በዲሲፕሊን እና በጥራት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

በመጨረሻም በቀረበው ሪፖርት ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከቤቱ ተነስተው ዋና ኦዲተሯ ክብርት ወ/ሮ ፈዲላ አደም እና ምክትል ዋና ኦዲተር የተከበሩ አቶ መሀመድ አብድላ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን መ/ቤቱ በተሻለ አፈፃፀም ላይ እንደሚገኝና እንደ ተቋም በጥንካሬ የተገለጹ ተግባራትን አጠናክሮ በመቀጠል እንዲሁም በጉድለት የተገመገሙ ችግሮችን ቀርፎ በቀጣይ በጀት አመት ሁሉም የመ/ቤቱ አመራሮችና ሠራተኞች የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ በቅንጅትና በቡድን መንፈስ መስራት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል፡፡

ዘገባው የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የኮሚኒኬሽንና ዳይሬክቶሬት ነው።

መሰከረም 05/1/2018 ዓ/ም(ወልቂጤ)ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ከሀገራችን አልፎ ለአፍሪካ ትንሳኤ መነሻ መሆኑ ተገለፀ።''እምርታ እና ማንሰራራት'' በሚል መሪ ቃል በታላቁ የ...
15/09/2025

መሰከረም 05/1/2018 ዓ/ም(ወልቂጤ)

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ከሀገራችን አልፎ ለአፍሪካ ትንሳኤ መነሻ መሆኑ ተገለፀ።

''እምርታ እና ማንሰራራት'' በሚል መሪ ቃል በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ ዙሪያ የተዘጋጀ የፖናል ውይይት መድረክ የወልቂጤ ክላስተር ክልል ማእከል በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማእድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን መኔዶ የመወያያ ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት የግድቡ መጠናቀቅ ለመላው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ታላቅ ድል በመሆኑ በሀገር ውስጥ እና በመላው አለም ባሉ ዜጎቻችን የሚከበር ነው።
በሁሉም እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ የኢትዮጵያ ህዝብ የተሳተፈበት ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መጠናናቅ ‎ኢትዮጵያ በአለም ላይ ከፍታዋን ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ያሳየ ነው ተብሏል።
እኛ ኢትዮጵያዊ በህብረት የማንችለው የለም !!!!!!!!!

02/13/2017 የማእከላዊ  ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለአዳዲስ ኦዲተሮች የሚሰጠው የሁለተኛ ቀን ስልጠናእንደቀጠለ ይገኛል።
07/09/2025

02/13/2017
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለአዳዲስ ኦዲተሮች የሚሰጠው የሁለተኛ ቀን ስልጠናእንደቀጠለ ይገኛል።

የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለአዲስ ኦዲተሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ጀመረማኢዋኦ  ጳጉሜ  01/2017 ቡታጅራ፡የማ/ኢ/ክ/መ/ዋና ኦዲተር መ/ቤት በፋይናንሻልና ክዋኔ ኦዲት ዘርፎ...
06/09/2025

የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለአዲስ ኦዲተሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ጀመረ
ማኢዋኦ ጳጉሜ 01/2017 ቡታጅራ፡የማ/ኢ/ክ/መ/ዋና ኦዲተር መ/ቤት በፋይናንሻልና ክዋኔ ኦዲት ዘርፎች ለአዲስ ኦዲተሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ዛሬ የጀመረ ሲሆን መድረኩን በንግግር የከፈቱት የመ/ቤቱ ም/ዋና ኦዲተር አቶ መሀመድ አብደላ ጥራት ያለዉ የኦዲት ስራ ለመከወን የኦዲተሮች አቅም ማሳደግ አስፈላጊ ስለሆነ ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን ጠቁመዉ ተሳታፊዎች ከስልጠና ባሻገር በማንበብና ተግባራዊ ልምምድ በማድረግ ራሳችሁን ማብቃት ይገባል ብለዋል፡፡ለሶስት ተከታታ ቀናት የሚቆይ ስልጠና በመቀጠል ላይ ይገኛል፡፡
ዘገባዉ የመ/ቤቱ ኮሙንኬሽንና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክቶሬ

17/11/2017 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ተኛ  አመት የስራ ዘመን 4ተኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ መካሄዱ ይታወቃል በጉባኤው የ2017 በጀት አ...
25/07/2025

17/11/2017
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ተኛ አመት የስራ ዘመን 4ተኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ መካሄዱ ይታወቃል በጉባኤው የ2017 በጀት አመት የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት፣ የስራና የበጀት እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።
ዋና ኦዲተር ክብርት ወ/ሮ ፈዲላ አደም ሪፖርቱ ባቀረቡበት ወቅት በሠጡት አስተያየት አንዳንድ ኦዲት ተደራጊ መስሪያ ቤቶች ኦዲት ለመደረግ ፈቃደኛ አለመሆን፣ ተገቢውን ማስረጃና መረጃ ለኦዲተሮ አለማቅረብ፣ለኦዲት ተቋም ግብረ መልስ አለመስጠት በተደጋጋሚ የሚገኙ የኦዲት ግኝቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ከመስራት አንፃር ክፍተቶች መኖራቸውንና ተጠያቂነት ሊሰፍን እንደሚገባ ጠቁመዋል ።
ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በበኩላቸው የውስጥ ኦዲት ማጠናከር ፣ የኢንስፔክሽን ስራዎች መስራት እንደሚገባና የተገኙ የኦዲት ግኝቶች ከማስመለስ ጋር መስተዳድሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም የምክር ቤቱ አባል የተሰሩ የኦዲት ስራዎች በይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ በመግለፅ የቀረበው ሪፖርትና እቅድ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል ።
መረጃው የክልሉ ዋና ኦዲተር መንግስት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

16/11/2017 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ተኛ  አመት የስራ ዘመን 4ተኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ መካሄድ  ተጀመረ ።በጉባኤው የ2017 በጀት ...
23/07/2025

16/11/2017
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ተኛ አመት የስራ ዘመን 4ተኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ መካሄድ ተጀመረ ።
በጉባኤው የ2017 በጀት አመት የአስፈጻሚ አካላት ፣የጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት እና ሌሎችም ጉዳዮች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግ ተመላክቷል ።

Address

Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share