Central Ethiopia Water,Irrigation and Mine Bureau

Central Ethiopia  Water,Irrigation and Mine  Bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia Water,Irrigation and Mine Bureau, Government Organization, Wolkite.

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ተመድቦ የለምቡዳ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ተጀመረ ። ሰኔ 08/2018ዓ.ም(ወልቂጤ)ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ የሌሞ አካባቢ ፕሮ...
15/06/2026

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ተመድቦ የለምቡዳ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ተጀመረ ።

ሰኔ 08/2018ዓ.ም(ወልቂጤ)
ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ የሌሞ አካባቢ ፕሮግራም በሌሞ ወረዳ የሶስት ቀበሌያት ህብረተሰብን ተጠቃሚ የሚያደርግ የከርሰ ምድር ንፁህ የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ አስጀመረ ።

ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ የሌሞ አካባቢ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ አበባአየሁ ጩማ እንደገለጹት የተጀመረው ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ግንባታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ከ20 ሺህ በላይ የአከባቢውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ግንባታው ተጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅም ከ60 ሚሊየን በላይ ገንዘብ ተመድቦ ወደ ስራ መገባቱንና ፕሮጀክቱም በሶስት ዓመት ውስጥ ተጠናቆ ለሕዝብና ለመንግስት ርክብክብ እንደሚደረግ ገልፀው ለስራው መሳካትም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጀምሮ እስከ አካባቢው ነዋሪዎች ከጎናቸው እንዲሆኑ ጠይቀዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙላቱ ጡሞሮ ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ ስራውን በተያዘለት የጊዜ ገደብ በጥራት እንዲያጠናቅቅ ቢሮው የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቀው ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ ሶስቱን ቀበሌያት ተጠቃሚ ለማድረግ የከርሰ ምድር ንፁህ የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ በማስጀመሩ አመስግነዋል ።

የሌሞ ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ ታደለ ደምሴ እንደተናገሩት ለምቡዳ ላይ የተጀመረው የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ ሲጠናቀቅ የለምቡዳ፣የማስቢራንና የጎራ ጡሜን ህብረተሰብ ተጠቃሚ እንደሚያደርግና የወረዳውን አማካይ የመጠጥ ውሃ ሽፋንም ከ7 እስከ 10 በመቶ እንደሚያሳድግ ገለጸው ፕሮጀክቱ ከሶስት ዓመት ቀድሞ እንዲጠናቀቅም የአከባቢው ማህበረሰብን ጨምሮ የወረዳው መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ያደርጋል ብለዋል።

በማስጀመሪያ ስነ ሥርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ማዕድን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙላቱ ጡሞሮ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኢንቨስትመንት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሼቦ ኡሊሶ፣የሌሞ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎች የቀበሌ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የወረዳው መንግስት ኮምኒኬሽን ዘግቧል ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስጀመሩሰኔ 8፣ 2018 ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በ...
15/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስጀመሩ

ሰኔ 8፣ 2018 ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በይፋ አስጀምረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት÷ የዚህን ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምረናል።

በተያዘው ዓመት 8 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ መቀመጡን ገልጸው ÷ በዚህም 65 ቢሊየን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ዜጎች ‎ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ አቅርበዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ማዘመን ያስችላል :- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሰኔ 8/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳ...
15/06/2026

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ማዘመን ያስችላል :- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሰኔ 8/2018)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወልቂጤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )እንደገለጹት ልዩ ልዩ ተቋማትን ያካተተው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን ያስችላል።

በክልሉ በተለያዩ ከተሞች ግንባታቸው የተጠናቀቁ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች ለምረቃ ይበቃሉ ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በክልሉ 2018 በጀት ዓመት ከመጠናቀቁ በፊት ከ15 እስከ 17 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

በወልቂጤ ከተማ በዛሬው እለት የተመረቀው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ እንዲጀምር ድጋፍ ላደረጉ አካላት ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንዳሉት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከወረቀት ንክኪ እና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አሰራር መዘርጋት ያስችላል።

የከተማዋን ገጽታ በመቀየር ረገድ የሚኖራቸው አበርክቶ ከፍተኛ ስለመሆኑም ዋና አስተዳዳሪው ጠቁመዋል።

ከተማዋን በአጭር ጊዜ ውስጥ መለወጥ የሚያስችል ስርዓት በመዘርጋት ተወዳዳሪነቷን ለማላቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አቶ ላጫ አብራርተዋል።

የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር በበኩላቸው ከተማዋ የአንድነት እና የታታሪ ህዝቦች መገኛ ነች ብለዋል።

የንግድና የኢኮኖሚ ጥንካሬ ማሳያ ከተማ ስለመሆኗም ከንቲባው አስረድተዋል።

ከለውጡ መንግስት ወዲህ የብልጽግና ተምሳሌት ከተማ ነች ያሉት ከንቲባው በከተማዋ የመሰረተ ልማት ስራዎች እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ስኬታማ ያደርገዋል ብለዋል።

የክልሉ መንግስት ኮምኒኬሽን

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም ማጠቃለያ ክልል አቀፍ የአመራር መድረክ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ‼ 👉 የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማ...
14/06/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም ማጠቃለያ ክልል አቀፍ የአመራር መድረክ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ‼

👉 የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ይገባል !!

👉 ክልሉ ሲመሰረት የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት በመደረጉ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ እንድንሆን ረድቶናል።

👉 የጋራ ትርክት ለመገንባት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው።

👉 ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የነበረው የቅድመ ዝግጅት ስራ ስኬታማ ነበር።

👉 የልማት እና የምርጫ ስራችን ተመጋጋቢ ሆነው ነበር።

👉 በምርጫው የህዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ መነቃቃት የታየበት ነበር።

👉 በክልሉ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ለቅድመ ዝግጅት ስራ አጋዥ ሆኗል።
👉 በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት ተሰርቷል።
በወቅታዊ የግብርና ልማት ስራ ላይ የጋራ ጥረት ማድረግ ይገባል።

👉 የግሪን ኢኔሼቲቭ እና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው።

👉 በክልሉ በፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ እና በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የተጀመሩ ስራዎች መጠናከር አለባቸው።

👉 ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ እየተካሔደ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።

👉 የስራ እድል ፈጠራ ካለው ጠቀሜታ አንጻር በዘርፉ የወጣቶችን ተጠቃሚነት እውን ማድረግ ይገባል።

👉 ለኑሮ ማረጋጋት ታልመው የተቋቋሙት የሰንበት ገበያዎችን ቀጣይነት ማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ያሻል።

👉 በከተማ እና በገጠር ኮሪደር ልማት ስራ ላይ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር ተገቢ ነው።

14/06/2026
በሁሉም ዘርፎች በሚከናወኑ ተግባራት ተደማሪ ድሎች ለማስመዝገብ መስራት ይገባል:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሰኔ 7/2018)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ...
14/06/2026

በሁሉም ዘርፎች በሚከናወኑ ተግባራት ተደማሪ ድሎች ለማስመዝገብ መስራት ይገባል:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሰኔ 7/2018)
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም ማጠቃለያ ክልል አቀፍ የአመራር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሔደ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በሁሉም ዘርፍ ተደማሪ ድሎችን ለማስመዝገብ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

የቤተሰብ ብልጽግናን ማረጋገጥ ልዩ ልዩ አቅሞችን በማስተባበር የክልሉን ብሎም የሀገሪቱን ልማት ቀጣይነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ መላው ህዝብ እና አመራሩ ላደረጉት የላቀ ድጋፍ ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።

ምርጫው ሰላማዊ፣ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሀዊ እንዲሆን ህብረተሰቡ የላቀ ጥረት ማድረጉን ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ ኢትዮጵያ መርጣለች፣ አሸንፋለች ሲሉም አብራርተዋል።

የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ቀጣይነት ማረጋገጥ ተገቢ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳደሩ በሁሉም መስክ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ መትጋት ይጠበቃል ብለዋል።

የህዝቡን መሰረታዊ ፍላጎት ለማሟላት ያለ እረፍት በመስራት ይገባል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።

በስራ ሂደት የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በጽናት በማለፍ የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ አብይ ጉዳይ በማድረግ መስራት እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

ያለንበት ዘመን እረፍት የሚሰጥ አይደለም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ለዚህም የአመራሩን ቁርጠኝነት ይጠይቃል ብለዋል።

ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሔድ ጥቂት ቀናት ሲቀሩ እና ከምርጫ በኋላ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ለመዳፈር ጥረት ያደረጉ ኃይሎች እንደነበሩ ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውሰዋል።
ነገር ግን የነዚህ አካላት ሴራ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ድል መደረጉን ጠቅሰዋል።

ፈጥኖ ወደ መደበኛ ስራ ላይ ማተኮር ይጠበቃል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው አስታውቀዋል።

የክልሉ መንግስት ኮምኒኬሽን

የሳምንቱ  #ዋና ዋና ሁነቶች በዋን ዋሽ ፕሮግራም የሚገነቡ ነባርና አዲስ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ውሀ ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ...
14/06/2026

የሳምንቱ #ዋና ዋና ሁነቶች
በዋን ዋሽ ፕሮግራም የሚገነቡ ነባርና አዲስ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ውሀ ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ አስታወቁ ።

የክልሉ ውሀ ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ በክልሉ በዋን-ዋሽ ፌዝ-2 ፕሮግራም በታቀፉ ወረዳዎችና ከተማዎች ውስጥ በማጠናቀቂያ ጊዜ ውስጥ የሚገነቡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በቀሪ ጊዜያት ማጠናቀቅ እንዲቻል የቢሮው የስራ ሃላፊዎችና የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ተገምግሟል ።

በዋን ዋሽ ፌዝ-2 ፕሮግራም በታቀፉ ወረዳዎችና ከተሞች ግንባታቸው የተጓተቱ ነባርና አዳዲስ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ቢሮው በየወሩ የሚገመገም ልዩ ዕቅድ በማዘጋጀት የተግባር ውጤታማነት ለማስመዝገብ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል ።

በአፈጻፀም ትግበራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን ተገቢው ክትትል በማድረግ በጊዜ የለንም መንፈስ መንቀሳቀስ እንደሚገባ የገለፁት አቶ ዳዊት በተቋራጮች በኩል የሚቀርቡ የነዳጅ ጥያቄዎችን ፣ የማቺንግ ፈንድ ግዴታን እና ተያያዥ ችግሮች በየመዋቅሩ አመራሩ በባለቤትነት በመውሰድ በፍጥነትና በቅንጅት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሀ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እና ምሁር አክሊል ወረዳ በዋን-ዋሽ ፕሮግራም ለሚያስገነባቸው የሶስት የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የስራ ቦታ/ሳይት ርክክብ አካሄዷል ።

ቢሮው በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በኮምበል አነስተኛ ከተማ ስራ እንዲሁም በምሁር አክሊል ወረዳ በጨቦና አበጅ ቀበሌዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ መስመር ዝርጋታና የቦኖ ግንባታ ስራ ማካሄጃ ቦት/ሳይት ለተቋራጮች ማስረከቡን በቢሮው የዋን ዋሽ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ መለሰ ጩፋሞ ገልፀዋል ።

በዋን ዋሽ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ኮንበል አነስተኛ ከተማ አንድ ባለ 100 ሜ/ኩ የንፁህ መጠጥ ውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር እና ባለ 50ሜ/ኩ ጋን (wet-well) ግንባታ ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰገንባት የቦታ ርክክብ መካሄዱን አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ በምሁር አክሊል ወረዳ ጨቦ ቀበሌ አምስት የውሃ ቦኖዎችን የመገንባትና የ4.1 ኪሎ ሜትር እንዲሁም በአበጅ ቀበሌ የ4 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የውሃ ቧንቧ መስመር ዝርጋታ ስራ እንደሚከናወን አቶ መለሰ ገልጸዋል።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ አስተባባሪነት የከተማ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለማቋቋም በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ ።

የውይይት መድረኩን ያስጀመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣንን ለማቋቋም እየተሰራ ያለውን ሂደት ለማሳወቅ፣ የሚቋቋመው የፌዴራል ተቆጣጣሪ ባለስልጣን አዋጅ ላይ ማብራሪያ ለመስጠት እንዲሁም ባለስልጣኑ ሊጠቀምባቸው በሚችለው መሠረታዊ የቁጥጥር መሣሪያዎች ላይ ስልጠናና ግንዛቤ ለመፍጠር መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል ።

ተቆጣጣሪው ባለስልጣን የውሃውን አገልግሎት አሰጣጥ የሚሻሙ አካላቶችን ወደ ህግ ማዕቀፍ በማስገባት ቁጥጥር ላይ የተመሰረተ አሰራር እንዲኖር ያስችላል ያሉት ክቡር አምባሳደር የውሃ ሀብታችንም ያለአግባብ እንዳይባክን ያግዛል ብለዋል።

ክቡር አምባሳደር አክለውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ በቀጣይ ከሚሰሩ በርካታ ስራዎች መካከል ከውሃ በሚገኘው ገቢ የሀገራችንን ኢኮኖሚ ማሻሻል እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአማካሪዎች የሚቀርበውን ሰነድ በማዳበር ለሚመለከተው አካል ማቅረብና ወደ ትግበራ እንዲገባ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ስድስት ወረዳዎችና አንድ ልዩ ወረዳ በኮ-ዋሽ ፕሮግራም የተጀመሩ የውሀ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጂን ፕሮጀክቶችን በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ውሀ ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ አስታውቋል ።

በቢሮው የኮ-ዋሽ ፕሮግራም ከፍተኛ ባለሙያዎች በየም ዞን ፎፋ ወረዳ፣ በጉራጌ ዞን አበሽጌና ጌታ ወረዳዎች በኮ-ዋሽ ፕሮግራም እየተገነቡ የሚገኙ የውሀ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጂን ፕሮጀክቶች ፊዚካል እና ፋይናንሻል አፈፃፀማቸውን አስመልክቶ ድጋፋዊ ክትትል አድርገዋል ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሀ ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ የኮ-ዋሽ ፕሮግራም የፕሮግራሙ መሀንዲስ ተመስገን ብዙአየሁ እንደገለፁት በክልሉ በኮ-ዋሽ ፕሮግራም እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት እንዳይቆሙና በዲዛይናቸው መሰረት እንዲጠናቀቁ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

13/06/2026
የኢነርጂ ዘርፍ የሚጨበጥ የተስፋ ጉዞ ኢትዮጵያ በታዳሽ የኃይል ምንጮች ያላት እምቅ አቅም የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሽግግር እውን ለማድረግ ትልቅ ምሰሶ ነው። በውሃ፣ በፀሐይ፣ በንፋስ እና በጂኦተ...
13/06/2026

የኢነርጂ ዘርፍ የሚጨበጥ የተስፋ ጉዞ

ኢትዮጵያ በታዳሽ የኃይል ምንጮች ያላት እምቅ አቅም የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሽግግር እውን ለማድረግ ትልቅ ምሰሶ ነው።

በውሃ፣ በፀሐይ፣ በንፋስ እና በጂኦተርማል ሀብቶች የታደለችው ኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦቷን በማዘመን የዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለቀጣናዊ ትስስር ቁልፍ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።

ኢነርጂ የኢንዱስትሪ መስፋፋት፣ የግብርና ምርታማነት እና የአገልግሎት ዘርፍ ዕድገት ቁልፍ ግብዓት ነው።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት "የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከል" ለመሆን በምታደርገው ጥረት የኢነርጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ የሀገሪቱን የሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል።

የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝ እና ተደራሽ ማድረግ፣ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና የግብርና ተቋማት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት አንኳር ጉዳይ ነው።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እየተወሰዱ ካሉ እርምጃዎች ጋር አብሮ የሚሄደው የኢትዮጵያ የኢነርጂ ልማት ስትራቴጂ፣ በዋናነት በአረንጓዴ ኃይል ላይ የተመሰረተ ነው።

የሀገሪቱ የኢነርጂ ምንጭ በውሃ ኃይል ብቻ ሳይወሰን በፀሐይና በንፋስ ኃይል እንዲታገዝ የሚደረገው ጥረት የላቀ ውጤት እያመጣ ይገኛል።

ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ የኢነርጂ ዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ሲሆን፤ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ትኩረት ተሰጥቷል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት መብቃት ለኢነርጂ ዘርፉ ቀጣይ ስኬት ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥሯል።

የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃት የዘርፉን ተስፋ የሚጨበጥ አድርገውታል።

በግንባታ ላይ የሚገኘው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በኢነርጂ ልማት ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር የጀመረችውን ጉዞ ከዳር የማድረስ ቁመና ላይ መገኘቷን ያሳያል።

በዘንድሮ በጀት ዓመት በኢነርጂ ልማትና አስተዳደር ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ኢትዮጵያ በዘርፉ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሷን ያመላክታሉ።

የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት መደገፍና የዜጎችን የኢነርጂ ፍላጎት የተሟላ እንዲሆን ለማድረግ የሚሰራው የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ተሻሽሏል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ዘጠኝ ወራት አጠቃላይ ከተለያዩ የኃይል ምንጮች የመነጨ የኤሌክትሪክ ኃይል ከነበረበት 7,910 ሜ.ዋ ወደ 9,580 ሜ.ዋ ለማሳደግ ታቅዶ ነበር።

በዚህም 1,669 ሜ.ዋ በማመንጨት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ወደ 9,579 ማደግ ችሏል፡፡
ከሚመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዘው ከውሃ ኃይል የመነጨ ኤሌክትሪክ ነው።

ከውሃ የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ከነበረበት 7,451 ሜ.ዋ ወደ 9,051 ሜ.ዋ ለማሳደግ ታቅዶ በዘጠኝ ወራት 1,599 ሜ.ዋ በማመንጨት ወደ 9,050 ሜ.ዋ እንዲያድግ ተደርጓል።

በተመሳሳይ ከንፋስ ኃይል፣ ከፀሐይ እና ከጂኦተርማል የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ይገኛል።

በዘጠኝ ወራት ብቻ 45 ሜ.ዋ ከንፋስ ኃይል ማመንጨት የተቻለ ሲሆን፤ ከጸሀይ ኃይል ደግሞ 6.5 ሜ.ዋ በማመንጨት ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደትን መደገፍ ተችሏል።

የኤሌክትሪክ ኃይል ከማመንጨት ስራው ጎን ለጎንም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዝግጁነትን የማሳደግ ተግባር መከናወኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት አቅም እየተገነባ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።

በአጠቃላይ በኢነርጂ ዘርፍ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግ እና ቀጣናዊ ትስስርን የማጎልበት እንቅስቃሴ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል።

በቀጣይም የዘርፉን አቅም በማጎልበት የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ፣ የከተማና ገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን እንዲሁም በኢነርጂ የቀጣናውን ሀገራት ይበልጥ ለማስተሳሰር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል።

የከተማ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለማቋቋም በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።ሰኔ 05/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመ...
12/06/2026

የከተማ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለማቋቋም በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።

ሰኔ 05/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ)
በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ አስተባባሪነት የከተማ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለማቋቋም በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።

የውይይት መድረኩን ያስጀመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣንን ለማቋቋም እየተሰራ ያለውን ሂደት ለማሳወቅ፣ የሚቋቋመው የፌዴራል ተቆጣጣሪ ባለስልጣን አዋጅ ላይ ማብራሪያ ለመስጠት እንዲሁም ባለስልጣኑ ሊጠቀምባቸው በሚችለው መሠረታዊ የቁጥጥር መሣሪያዎች ላይ ስልጠናና ግንዛቤ ለመፍጠር የሚያስችል መድረክ ነው ብለዋል።

ተቆጣጣሪው ባለስልጣን የውሃውን አገልግሎት አሰጣጥ የሚሻሙ አካላቶችን ወደ ህግ ማዕቀፍ በማስገባት ቁጥጥር ላይ የተመሰረተ አሰራር እንዲኖር ያስችላል ያሉት ክቡር አምባሳደር የውሃ ሀብታችንም ያለአግባብ እንዳይባክን ያግዛል ብለዋል።

ክቡር አምባሳደር አክለውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ በቀጣይ ከሚሰሩ በርካታ ስራዎች መካከል ከውሃ በሚገኘው ገቢ የሀገራችንን ኢኮኖሚ ማሻሻል እንደሚገባ ጠቁመው፤ በአማካሪዎች የሚቀርበውን ሰነድ በማዳበር ለሚመለከተው አካል ማቅረብና ወደ ትግበራ እንዲገባ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ክቡር አምባሳደር ለአዋጁ ዝግጅት አስተዋፅኦ ያደረኩ አካላትን ጨምሮ የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉትን የአለም ባንክንና ዩኒሴፍን አመስግነዋል።

እንደተቋም አገር አቀፍና ገለልተኛ ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለማቋቋም በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ እንደነበር የጠቆሙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃ ተቋማት ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ኃላፊ አቶ ኃይማኖት በለጠ ሰነዱን በውይይት ከማዳበር ጀምሮ ተቋማዊ የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ከፍትህ ሚኒስቴር እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻዎች ጋር ውይይት እንደተደረገበትም አስታውሰዋል።

አዋጁ በዋናነት ፍቃድ አሰጣጥ እና ተገዢነት /Licensing & Compliance/ አንደኛው ሲሆን ለአገልግሎት ሰጪዎች የሚወጡ መስፈርቶች፣ የንብረት አስተዳደር፣ ያልተመዘገበ ወይም የሚባክን ውሃ እና የውሃ ጥራት ቁጥጥር ላይ ያለመ፤ ሁለተኛው ደንበኛ ተኮር መሣሪያዎች /Customer-Centered Tools/ ሲሆን የደንበኞችን ጥቅም ማስጠበቅ፣ የደንበኞች ቻርተር ተገዢነት እና የውሃ ቆጣሪ ደንቦች ላይ የሚያተኩር እንዲሁም ሶስተኛው አፈፃፀም እና መልካም አስተዳደር /Performance and Governance/ የብሔራዊ አፈፃፀም መለኪያ መመሪያዎች እና የቦርድ አባላት እንዲሁም የዋና ሥራ አስፈፃሚዎች የሥነ-ምግባር ደንብን ያካተተ ነው።

ተቆጣጣሪ ባለስልጣኑን ለማቋቋም የሚያስችሉ ሰነዶች በግለሰብ አማካሪዎች /Individual Consultant/ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።

በመድረኩ የቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ ጨምሮ የክልሎች የውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊዎች፣ የከተሞች ውሃና ፍሻሽ አገልግሎት ድርጅት ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ ከተሞች መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽ ፌዴሬሽን የስራ ኃላፊዎች፣ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚመለከታቸው ስራ አስፈፃሚዎችና ባለሞያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ባለሞያዎች እየተሳተፉ ሲሆን መድረኩ ለተከታታይ ሶስት ቀናት ይቀጥላል።

ው/ኢ/ሚ

Address

Wolkite

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Water,Irrigation and Mine Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share