Gurage Zone Government Communication Affairs Department

Gurage Zone Government Communication Affairs Department We work hard to build an informed society by providing hot and hard news, articles and documentary films!

የምርጫ ሂደቱ የኢትዮጵያን የዲሞክራሲ ጉዞ የሚያጠናክርና የሕዝብ ፍላጎት በሰላማዊ መንገድ የሚገለጽበት ነው፦አቶ ይግለጡ አብዛግንቦት 24/2018(ውልቂጤ)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልፅግና...
01/06/2026

የምርጫ ሂደቱ የኢትዮጵያን የዲሞክራሲ ጉዞ የሚያጠናክርና የሕዝብ ፍላጎት በሰላማዊ መንገድ የሚገለጽበት ነው፦አቶ ይግለጡ አብዛ

ግንቦት 24/2018(ውልቂጤ)

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ይግለጡ አብዛ እንዲሁም የእዣ ቁጥር 2 ምርጫ ክልል የፓርቲው የክልል ምክር ቤት እጩ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው ሕዝቡ የሚፈልገውን ፓርቲ በነጻ ፈቃዱ እየመረጠ ሲሆን፣ የምርጫው ሂደቱም በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ መንገድ እየተካሄደ ነው ብለዋል።

"ዛሬ አለመምረጥ ማለት ወደፊት በራስ ምርጫ ባልተወሰነ አስተዳደር መመራት ማለት ነው" ያሉት አቶ ይግለጡ፣ ሁሉም ዜጋ የዴሞክራሲ ግንባታን ለማጠናከር በምርጫው ላይ በንቃት ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባው ገልጸዋል።

የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ እና በእዣ ቁጥር 2 ምርጫ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የፓርላማ እጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ መሰረት አመርጋ በምርጫ ጣቢያቸው በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ወ/ሮ መሰረት በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ሕዝቡ በቀጣይ ኢትዮጵያን የሚመራ መንግሥት በነጻነትና በዲሞክራሲያዊ ሂደት እየመረጠ ሲሆን፣ በምርጫው የሚታየው ተሳትፎም የማህበረሰቡ የዲሞክራሲ ግንዛቤና ንቃተ ህሊና እያደገ መምጣቱን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል።

በምሁር አክሊል ወረዳ የእዣ ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ ገብረመድህን ቤዛ በምርጫ ክልሉ በሚገኙ 63 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ከጥዋቱ 12 ሰአት ጀምሮ ድምጽ እየተሰጠ መሆኑ ተናግሯል።

የምርጫ ሂደቱም ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው አሰራር መሰረት ፍጹም ሰላማዊ፣ድሞክራሲያዊ እና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ምርጫው በተያዘለት መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው፦  ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ******************የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰ...
01/06/2026

ምርጫው በተያዘለት መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው፦ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
******************

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም አጠቃላይ የድምፅ መስጠት ሂደቱ ዛሬ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ ከ50 ሺህ በላይ በሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል።

ይሁን እንጂ 695 በሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ሂደቱ በጥቂቱ ዘግይቶ መጀመሩን አብራርተዋል።

ለምርጫው ስኬታማነት ወሳኝ የሆነው የቁሳቁስ ስርጭት ትላንት ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁንም ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።

የምርጫውን ግልፅነትና ታማኝነት ለማረጋገጥ ገለልተኛ ታዛቢዎች በ39 ሺህ 723 የምርጫ ጣቢያዎች እየተከታተሉ እንደሆነ ነው ሰብሳቢዋ የጠቀሱት፡፡

41 ሺህ 978 በሚሆኑት ጣቢያዎች ላይ ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች ተገኝተው ሂደቱን በቅርበት እየታዘቡ እንደሚገኙም ገለጸዋል።

7ኛው ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በወልቂጤ ከተማ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት ፍፁም ሳላማዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ ነው። ግንቦት24/18(ወልቂጤ)የምርጫ ...
01/06/2026

7ኛው ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በወልቂጤ ከተማ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት ፍፁም ሳላማዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ ነው።

ግንቦት24/18(ወልቂጤ)የምርጫ ጣቢያዎች ከንጋቱ 12 ሰአት ጀምሮ ከፍት የተደረጉ ሲሆን እኛም በከተማው ለድምፅ መስጫ የተዘጋጁትን የምርጫ ጣቢያዎች ተዘዋውረን ለመመልከት ችለናል።

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለምርጫው ስኬታማነት ተቋማዊ እና የህግ ማዕቀፎችን በማሻሻል በርካታ ተግባራት ሲያከናውን መቆየቱ የሚታወስ ነው።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና ድጋፍ ማካሄድ የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የውይይት መድረክ ማከናወን የሚጠቀሱ ናቸው።

ይህ በመሆኑ ሃገሪቷ እያካሄደች ባለው ጠቅላላ ምርጫ ከዚህ በፊት ከነበረው ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን እንዳስቻለው መገንዘብ ይቻላል።

በወልቂጤ ከተማ እየተደረገ ያለው የድምፅ አሰጣጥ ሂደትም የዚሁ ማረጋገጫ ነው።

በወልቂጤ ምርጫ ክልል ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ፣ኢዜማ እና ጎጎት በአጠቃላይ 5 የፖለቲካ ፓርቲዎች ለህዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት እየተወዳደሩ ይገኛል።

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱም እጅግ ሰላማዊ ያለማንም ጣልቃ ገብነት ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን በየምርጫ ጣቢያዎች ተዘዋውረን ያነጋገርናቸው መራጮች አረጋግጠውልናል።

ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት 6 ጊዜ ሃገር አቀፍ ምርጫዎችን አካሄዳለች የዘንድሮ 7ኛው ምርጫ ግን የዲሞክራሲ መሠረት የተጣለበት ካለፊት ምርጫዎች ሁሉ የተሻለ ስለመሆኑ መራጮቹ ይገልጻሉ።

በዕለቱ በመገኘት ድምፃቸውን የለማንም አስገዳጅነት ለሚፈልጉት የፖለቲካ ፓርቲ መስጠት በመቻላቸው መደሰታቸውን ነው የጠቀሱት።

የከተማው ነዋሪዎች ያለ መታከት ረጃጅም ሰልፎችን በመያዝ ድምፅ እየሰጡ መሆናቸው የቀጣይ የሃገሪቷ እጣ ፈንታ የሚወሰነው በያዙት ካርድ እና በሚሰጡት ድምፅ ብቻ እንደሆነ መረዳት ይቻላል።

Fm Wolkite 89.2 Radio

የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በአዲስ አበባ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን እየጎበኙ ነውግንቦት 24፣ 2018 (ወልቂጤ) የምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በአዲስ አበባ የሚገ...
01/06/2026

የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በአዲስ አበባ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን እየጎበኙ ነው

ግንቦት 24፣ 2018 (ወልቂጤ) የምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎችን እየጎበኙ ነው፡፡

የታዛቢ ቡድኑ መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን አከፋፈት እና አጠቃላይ የምርጫውን ሒደት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

መሪዋ የመጀመሪያ ምልከታቸውን ያደረጉት በምርጫ ክልል 17፣ ወረዳ 3 በሚገኘው የሻላ ፓርክ ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 1 ላይ ሲሆን÷ በዚህም የምርጫ ቁሳቁሶች መሟላታቸውን፣ የጣቢያውን አከፋፈት ሕጋዊ ሥነ ሥርዓት እና የድምፅ አሰጣጥ ጅማሮን በቅርበት ታዝበዋል።

የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን እየተካሄደ የሚገኘውን የድምፅ አሰጣጥ ሒደት፣ የመራጮችን ተሳትፎ፣ የምርጫ ጣቢያዎችን ለአካል ጉዳተኞችና ለአረጋውያን ምቹ መሆን እንዲሁም አጠቃላይ የጸጥታና የምርጫ ድባቡን በቅርበት መከታተሉን እንደሚቀጥል የኢጋድ መረጃ ያመላክታል።

#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያእየመረጠችነው #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል

በጉራጌ ዞን በጉመር ቁጥር 2 ምርጫ ክልል የጉመር ወረዳ  ነዋሪዎች ከማለዳው ጀምረው ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛል።ግንቦት 24/2018(ወልቂጤ)ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ መምረጡን አጠናክሮ መቀጠሉን ...
01/06/2026

በጉራጌ ዞን በጉመር ቁጥር 2 ምርጫ ክልል የጉመር ወረዳ ነዋሪዎች ከማለዳው ጀምረው ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛል።

ግንቦት 24/2018(ወልቂጤ)

ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ መምረጡን አጠናክሮ መቀጠሉን ተዘዋውረን ባየንባቸው ቦታዎች ማረጋገጥ ችለናል።

የኢፌድሪ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር  አቶ ኤልያስ ሽኩር  የፌደራል መንግስት ግዢ አገልግሎት ዳይሬክተር ወ/ሮ ነጂባ አክመል እንዲሁም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የኢኮኖሚ...
01/06/2026

የኢፌድሪ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ሽኩር የፌደራል መንግስት ግዢ አገልግሎት ዳይሬክተር ወ/ሮ ነጂባ አክመል እንዲሁም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ልክነሽ ስርገማ እና የቀድሞ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በእነሞርና ኤነር ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ሚቄ 01 ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም(ወልቂጤ )የኢፌድሪ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ሽኩር የፌደራል መንግስት ግዢ አገልግሎት ዳይሬክተር ወ/ሮ ነጂባ አክመል እንዲሁም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ልክነሽ ስርገማ እና የቀድሞ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በእነሞርና ኤነር ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ሚቄ 01 ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

Fm Wolkite 89.2 Radio

ህዝቡ ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ በመምረጥ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እድገት እንዲዳብር የበኩሉን መወጣት እንዳለበት የጎጎት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ መሀመድ አብራር ገለፁ። ግንቦት24/18(ወልቂጤ) ለህ...
01/06/2026

ህዝቡ ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ በመምረጥ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እድገት እንዲዳብር የበኩሉን መወጣት እንዳለበት የጎጎት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ መሀመድ አብራር ገለፁ።

ግንቦት24/18(ወልቂጤ)

ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየተወዳደሩ የሚገኙት የጎጎት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ መሀመድ አብራር እየተካሄደ የሚገኘው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በወልቂጤ ምርጫ ጣቢያዎች ሰላማዊ መሆኑን ገልፀዋል።

በምርጫ ክልልሉ ካርድ የወሰዱ የህብረተሰብ ክፍሎች በምርጫው በነቂስ መሳተፋቸው በምርጫ መንግስት የመመሥረት ልምዱ እንዲዳብር ያደርጋል ብለዋል።

ህዝቡ ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ በመምረጥ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እድገት እንዲዳብር የበኩሉን መወጣት እንዳለበት አቶ መሀመድ ተናግረዋል።

አንድ ድምፅ ያለውን ዋጋ በመረዳት ሕዝቡ ነፃነቱንና መብቱን በመጠቀም ድምፁን መስጠት እንዳለበትም ገልፀዋል።

በ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ጎጎት ፓርቲ በአራት ክልሎች እየተሳተፈ እንደሚገኝም አቶ መሃመድ አስረድተዋል።

ዲሞክራሲያዊ መብታችንን ተጠቅመን ለቀጣይ አምስት አመታት የሚያስተዳድረንን መንግሥት በድምጻችን በመወከላችን ደስተኞች ነን ሲሉ በጉራጌ ዞን የእምድብርና ቸሀ ምርጫ ክልል ምርጫ ጣቢያዎች  መራ...
01/06/2026

ዲሞክራሲያዊ መብታችንን ተጠቅመን ለቀጣይ አምስት አመታት የሚያስተዳድረንን መንግሥት በድምጻችን በመወከላችን ደስተኞች ነን ሲሉ በጉራጌ ዞን የእምድብርና ቸሀ ምርጫ ክልል ምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ገልጸዋል።

ግንቦት24/18(ወልቂጤ)

በምርጫ ክልሉ ከምርጫ ጣቢያዎች ድምጻቸውን ሰጥተው ሲመለሱ አግኝተን ያነጋገርናቸው በጉራጌ ዞን ቸሀ ወረዳ የእምድብር ከተማ ነዋሪዎች ሀገርን የሚያስተዳድር መንግሥት ለመምረጥ የምርጫ ካርድ ወስደው እለቱን በጉጉት ሲጠባበቁ እንደነረ ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም በወሰዱት የምርጫ ካርድ የሚያስተዳድራቸውን መንግስት በድምጻቸው ለመወከል በምርጫ መሳተፋቸውን ተናግረዋል።

በወሰዱት ካርድ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ለሀገር እና ለሕዝብ ይጠቅማል ያሉትን መንግስት በመምረጥ ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል፡፡

ምርጫው ነጻ፣ ሰላማዊና ገለልተኛ በሆነ መልኩ ያለምንም ችግር እየተካሔደ መሆኑም ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል። .

Fm Wolkite 89.2 Radio

‎​የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በሀዲያ ዞን ሶሮ 01 የምርጫ ክልል በጊምቢቹ ከተማ አስተዳደር 01 ምርጫ ጣቢያ  በመገኘት  ድምፃቸውን ሰጥተዋል።‎
01/06/2026

‎​የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በሀዲያ ዞን ሶሮ 01 የምርጫ ክልል በጊምቢቹ ከተማ አስተዳደር 01 ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ኮንተብ 01 ምርጫ ክልል ዱና ጌመዶ የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጡ‎‎በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተ...
01/06/2026

አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ኮንተብ 01 ምርጫ ክልል ዱና ጌመዶ የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጡ

‎በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል፤ በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ኮንተብ 01 ምርጫ ክልል ዱና ጌመዶ የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።(ደሬቴድ)



Address

Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage Zone Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gurage Zone Government Communication Affairs Department:

Share