09/05/2026
የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል በኮፒያ (KOPIA) ፕሮጀክት ድጋፍ፣ ለቀቤና ልዩ ወረዳ እና አበሽጌ ወረዳ አርሶ አደሮችና ባለሙያዎች በሽንኩርት ዘር አመራረት ቴክኖሎጂ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
የስልጠናው ዋና ዋና ነጥቦች፦
የሽንኩርት ዘር እና የኮረት አመራረት ዘዴዎች።
ከመሬት ዝግጅት እስከ ምርት አሰባሰብና ድህረ ምርት አያያዝ።
በአመራረት ሂደት ላይ ለሚገጥሙ ተግዳሮቶች ከወልቂጤ እና ከመልካሳ ምርምር ማዕከል ተመራማሪዎች ማብራሪያ ተሰቷል።
ይህ ስልጠና አርሶ አደሩ ጥራት ያለው የሽንኩርት ዘር በራሱ ማምረት እንዲችልና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ነው።