በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ የመንግስት ኮሚዩንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wolkite
  • በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ የመንግስት ኮሚዩንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ የመንግስት ኮሚዩንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ለዜጎቻችን !!!

ግንቦት 26/2018 ዓ.ም===============የእነሞርና ኤነር ምረጫ ክልል 1 የ60 ምርጫ ጣቢያ የመራጮች ድምጽ ተጠቃሎ ወደ ምርጫ ክልሉ ገብቶ የቆጠራ ስራ ተጀምሯል።የእነሞርና ኤነር ም...
03/06/2026

ግንቦት 26/2018 ዓ.ም
===============
የእነሞርና ኤነር ምረጫ ክልል 1 የ60 ምርጫ ጣቢያ የመራጮች ድምጽ ተጠቃሎ ወደ ምርጫ ክልሉ ገብቶ የቆጠራ ስራ ተጀምሯል።

የእነሞርና ኤነር ምርጫ ክልል 1 ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኃይማኖት አለሙ በመግለጫቸው የምርጫ ክልሉ ሎጀስቲክ ዘርፍ አስተባባሪ የነበሩት ዳዊት ዳንኤል በስራ ላይ እያሉ በሞተር ሳይክል በደረሰባቸው አደጋ ምክንያት ህይወታቸው በማለፉ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።

ግንቦት 25/2018 ዓ.ም  🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏የእኖር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መብራቱ ተክሌ የምስጋና መልእክት አስተላለፉ።ዋና አስተዳዳሪው 7ተኛውን ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በወረዳው በሰላም መጠ...
02/06/2026

ግንቦት 25/2018 ዓ.ም
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏የእኖር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መብራቱ ተክሌ የምስጋና መልእክት አስተላለፉ።

ዋና አስተዳዳሪው 7ተኛውን ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በወረዳው በሰላም መጠናቀቁን አስመልክተው በተግባሩ ላይ ለተሳተፉ ባለድርሻ በሙሉ፣ለምርጫ አስፈጻሚዎች ፣ለጸጥታ አካላት፣ለታዛቢዎች፣ለተወካዮች እና ለመላው የወረዳው ህዝብ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

መራጩ ህዝብ የጠዋት ብርድና የቀን ጸሀይ ሳይበግረው ለረጅም ሰዓት በትዕግስት ተሰልፎ ወረፋ በመጠበቅና በመምረጥ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላሳየው ቁርጠኝነትና ጽናት የሚደነቅ መሆኑንም ገልጿል።

አቶ መብራቱ በዚሁ አጋጣሚ የምርጫ ክልሉ ሎጀስቲክ ዘርፍ አስተባባሪ የነበሩት ዳዊት ዳንኤል በስራ ላይ እያሉ በሞተር ሳይክል በደረሰባቸው አደጋ ምክንያት ህይወታቸው በማለፉ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።

ዋና አስተዳዳሪው ለሟች ቤተሰብ እና ለወዳጅ ዘመድ በሙሉ በራሳቸውና በወረዳው ህዝብ ስም መጽናናትን ተመኝቷል።ዘገባው የወረዳው መ/ኮ ነው።

ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በድጋሚ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅ...
01/06/2026

ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።

በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ከማለዳው ጀምሮ  መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ ናቸው።ግንቦት 24/2018(ወልቂጤ) በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ...
01/06/2026

በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ከማለዳው ጀምሮ መራጮች የሚፈልጉትን ፓርቲ በመምረጥ ላይ ናቸው።

ግንቦት 24/2018(ወልቂጤ) በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ተዘዋውረን በተመለከትናቸው የምርጫ ጣቢያዎች ከማለዳው 12:00 ሠዓት ጀምሮ መራጩ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ በቀጣዩ 5 ዓመታት እንዲመራው የሚፈልገውን ፓርቲ በመምረጥ ላይ ነው።

በምርጫ ክልሉ ጉንችሬ 01 እና ጉንችሬ 02 ምርጫ ጣቢያዎች አግኝተን ካነጋገርናቸው መራጮች መካከል በሰጡት አስተያየት በዛሬው ዕለት እየተካሄደ በሚገኘው ታሪካዊው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመራጭነት በመሳተፋቸው ዕድለኛ መሆናቸውን ገልፀውልናል።

ምርጫ የሀገሪቱን ቀጣይ ጉዞ ወደተሻለ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግር መራጮቹ አንስተው የምርጫው ሂደት ነፃ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንደሆነም ነው ያስረዱት።

መንግስት የሚገነባው በህዝብ የምርጫ ካርድ በመሆኑ፣ ህዝቡ ይህንን ሰላማዊ እድል ተጠቅሞ የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አመላክተዋል።

Fm Wolkite 89.2 Radio

የኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ አዛዥ አቶ እርስቱ ይርዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በዕጩነት በተወዳሩበት በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ቀርበው...
01/06/2026

የኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ አዛዥ አቶ እርስቱ ይርዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በዕጩነት በተወዳሩበት በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ቀርበው ድምጽ ሰጥተዋል፡፡

ግንቦት24/2018ዓ.ም(ወልቂጤ)

የኢፌዲሪ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ አዛዥ አቶ እርስቱ ይርዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ በዕጩነት በተወዳሩበት በጉራጌ ዞን እነሞርና ኤነር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ቀርበው ድምጽ ሰጥተዋል።

ሀገሪቱ በየጊዜው ምርጫ እያካሄደች እንደምትገኝ በማውሳት ይህም በጊዜው እየተሻሻለ መምጣቱንና ሀገርን የማጽናት ተልዕኮ እንዳለው አንስተዋል።

ምርጫው ታሪካችንን የሚያድስ በመሆኑ መራጩ ህዝብ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል።

Fm Wolkite 89.2 Radio

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም================እኖር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እየመረጠ ይገኛል።
01/06/2026

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም
================እኖር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እየመረጠ ይገኛል።

በ7ተነ የገን ሽፗቸ የጉራጌ ሐልቅ በዞንዌ ብንም የሽፗቸ ጣቢያ በጋት ተረከበም ወሸብት ቀነሰም።
01/06/2026

በ7ተነ የገን ሽፗቸ የጉራጌ ሐልቅ በዞንዌ ብንም የሽፗቸ ጣቢያ በጋት ተረከበም ወሸብት ቀነሰም።

ግንቦት 22/2018 ዓ.ም===============በእኖር ኤነር ቁ 1 ምርጫ ክልል ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ ይገ...
30/05/2026

ግንቦት 22/2018 ዓ.ም
===============
በእኖር ኤነር ቁ 1 ምርጫ ክልል ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ ይገኛል፡፡

ለምርጫ የተመዘገቡ እጩዎች ልዩ መብቶች1. ለምርጫ የተመዘገቡ እጩዎች ከባድ ወንጀል ሲፈፅሙ እጅ ከፍንጅ ካልተያዙ በስተቀር ምርጫው እስከሚጠናቀቅ ድረስ በወንጀል ተጠርጥረው አይያዙም፡፡2. እ...
28/05/2026

ለምርጫ የተመዘገቡ እጩዎች ልዩ መብቶች

1. ለምርጫ የተመዘገቡ እጩዎች ከባድ ወንጀል ሲፈፅሙ እጅ ከፍንጅ ካልተያዙ በስተቀር ምርጫው እስከሚጠናቀቅ ድረስ በወንጀል ተጠርጥረው አይያዙም፡፡

2. እጅ ከፍንጅም ባይሆንም ዕጩዎች ሕገወጥ ድርጊት የፈፀሙ እንደሆነ ሕጋዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው የሚችለው፣ የምርጫው ውጤት በቦርዱ አማካኝነት በይፋ ለህዝብ ከተገለፀ በኋላ ብቻ ይሆናል፡፡

3 እጩው በምርጫ ካሸነፈ፣ አሸናፊው ሰው በምርጫ ወቅት በፈፀመው ወንጀል የሚጠየቀው በሚመለከተው ምክር ቤት የሕግ ከለላው ሲነሳ ብቻ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ትመርጣለች!

ግንቦት 24 ቀን "ኢትዮጵያ ትመርጣለች"ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮጵያ ትመርጣለች"
28/05/2026

ግንቦት 24 ቀን "ኢትዮጵያ ትመርጣለች"

ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮጵያ ትመርጣለች"

Address

Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ የመንግስት ኮሚዩንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ የመንግስት ኮሚዩንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት:

Share