Gubalafto woreda culture and tourism office

Gubalafto woreda culture and tourism office promote tourist destinations

እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት እና ትንሳዔ  በዓል አደርሳችሁ ፣ አደርሰን !!   ➾ የትንሳኤ በዓል ጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሰው ...
11/04/2026

እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት እና ትንሳዔ በዓል አደርሳችሁ ፣ አደርሰን !!

➾ የትንሳኤ በዓል ጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሰው ልጆች ደህንነት ሲል ያጋጠመውን መከራ፣ ይቅር ባይነት፣ ስቃይና ግርፋት በፅናት ተቋቁሞና ሞትን አሸንፎ የዲያብሎስን ቀንበር ሰብሮ የሰውን ልጅ ወደ ብርሃን ያሻገረበት የፅናት፣ የአሸናፊነትና የነፃነት በዓል ተምሳሌት ነው

➾ ትንሳዔ ኢየሱስ ክርስቶስ በሰሙነ ህማማት የተቀበላቸውን ግርፋት፣እርዛት፣ችንካር እና የእሾህ አክሊሊል በትዕግስት አልፎ በሰው ልጆች ሁሉ የሚታየውን ቀቢጸ ተስፋነት አስወግዶ የተስፋ ጮራ የዘራ ታላቅ የምስራች በዓል ነው ።

➾ የመረዳዳት፣የመደጋገፍና የመተባበር ባሕልና እሴት ባለቤት ሲሆን በዓሉን ሲከብር በሃይማኖቱ አስተምህሮ መሠረት የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ በአብሮነትና በመደጋገፍ የምናከብርው በዓል ነው ።

በመጨረሻም በዓሉ ከፍታን እና ርህራሄን የምናሳይበት፣እርስ በርስ የምንረዳዳበት፣ያለው ከሌለው ተባብሮ የሚያልፍበት በዓል እንዲሆን ከልብ እንመኛለን ።

" ባህላችን ለዘላቂ ሠላማችን "

የጉባላፍቶ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ፅ/ቤት

18/03/2026
‎የአብሮነት እና የመረዳዳት ወር በሆነው የረመዳን ወር የነበረውን መልካምነት አጠናክሮ በማስቀጠል ለሀገር ሁለንተናዊ ሰላምና ልማት መትጋት ይገባል። ‎የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ መንገሻ...
18/03/2026

‎የአብሮነት እና የመረዳዳት ወር በሆነው የረመዳን ወር የነበረውን መልካምነት አጠናክሮ በማስቀጠል ለሀገር ሁለንተናዊ ሰላምና ልማት መትጋት ይገባል።
‎የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)

‎ወልድያ፦ መጋቢት 8 /2018 ዓ.ም (ጉባላፍቶ ኮሙኒኬሽን)

‎በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ የረመዳንን ፆም ምክንያት በማድረግ የኢፍጣር መርሃ ግብር ተካሂዷል።

‎የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) የኢፍጧር መርሃ-ግብር የኢትዮጵያን የመቻቻል እና የእንግዳ ተቀባይነት እሴት የሚዘክር በመሆኑ በህዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነት እና ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ የሚያጎለብት በመሆኑ ሁሉም በአቅሙ መረዳዳቱን እንዲቀጥል መልክት አስተላልፈዋል።

‎የፕሮግራሙ ተሳታፊዎችም ለተደረገው የኢፍጧር ፕሮግራም ምስጋና አቅርበዋል።

‎በፕሮግራሙ የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የወረዳ አመራሮች እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

‎አንድነት ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት እና ክብር መሰረት መሆኑን የአድዋ ድል ማሳያ ነው። ‎ወልድያ፦ የካቲት 23/2018 ዓ/ም (ጉባላፍቶ ኮሙኒኬሽን)‎በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ 130...
02/03/2026

‎አንድነት ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት እና ክብር መሰረት መሆኑን የአድዋ ድል ማሳያ ነው።

‎ወልድያ፦ የካቲት 23/2018 ዓ/ም (ጉባላፍቶ ኮሙኒኬሽን)

‎በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ 130ኛው የአድዋ ድል በዓል "ከአኩሪ ታሪክ ወደብሩህ አድማስ" መሪ ሀሳብ ከወረዳው ጠቅላላ አመራር እና ሰራተኞች ጋር በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።

‎የጉባላፍቶ ወረዳ ም/ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ በየነ የተጀመሩ ልማቶችን ለማስቀጠልና ሰላምን በዘላቂነት ለማረጋገጥ አድዋን ከመዘከር ባለፈ ዘመኑ የሚጠይቀውን አርበኝነት መላበስ እንደሚያስፈልግ መልእክት አስተላልፈዋል።

‎ለዓሉ በጉባላፍቶ ወረዳ የጁገነት የባህል ቡድን እና አማተር ከያኒያን የተለያዩ ኪነጥበብ ስራዎችን አቅርበዋል። ለፓናል ውይይት መነሻ ሰነድ የወረዳው መንግስት ኮሙኒኬሽን ሀላፊ አቶ አያሌው አስፋው ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

ጥር 17/05/ 2018 ዓ.ም 17ኛው የሰሜን ወሎ ዞን የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል ከወልድያ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር  በደማቅ ሁኔታ ባካሄደው የባህል ፌስቲቫል የጉባላፍቶ ወረዳ የሀመልማ...
27/01/2026

ጥር 17/05/ 2018 ዓ.ም 17ኛው የሰሜን ወሎ ዞን የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል ከወልድያ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በደማቅ ሁኔታ ባካሄደው የባህል ፌስቲቫል የጉባላፍቶ ወረዳ የሀመልማል የቲያትር ቡድን በዞን ደረጃ 1ኛ ደረጃ በመያዝ በዳኞች ተገምግሞ መምረጥ ችሏል።

ለኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች  በሙሉ➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽የ2018 የኪነ ጥበብ ውድድር  ሊጠናቀቅ 5 ቀን ቀርቷታል አያምልጠዎ➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽የጉባላፍቶ ...
04/12/2025

ለኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች በሙሉ
➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽

የ2018 የኪነ ጥበብ ውድድር ሊጠናቀቅ 5 ቀን ቀርቷታል አያምልጠዎ
➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽➽

የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት የኪነ -ጥበባት ውድድር ለማካሄድ የመወዳደሪያ መስፈርቶችን መሠረት በማድረግ ማስታወቂያዎችን በተለያዩ ቦታዎች የለጠፍን ሲሆን ምዝገባው የሚጠናቀቀው ህዳር 30/03/2018 መወዳደር የምትፈልጉ ጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 ድርስ በመምጣት ስራዎቻቸውን እንድታስገቡ ጥሪውን ያስተላልፋል ።

" ኪነ ጥበብ ለልማት "

የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት

እንደሀገር ጎልተው የሚታዩ ስኬቶቻችን የህብረታችን ውጤቶች መሆናቸውን በመረዳት ህብረብሔራዊነታችን ማጠናከር ያስፈልጋል።‎‎ወልድያ፦ ህዳር 11/2018 ዓ/ም (ጉባላፍቶ ኮሙኒኬሽን)‎‎በሰሜን ...
20/11/2025

እንደሀገር ጎልተው የሚታዩ ስኬቶቻችን የህብረታችን ውጤቶች መሆናቸውን በመረዳት ህብረብሔራዊነታችን ማጠናከር ያስፈልጋል።

‎ወልድያ፦ ህዳር 11/2018 ዓ/ም (ጉባላፍቶ ኮሙኒኬሽን)

‎በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል።

‎ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ መነሻ ሰነድ ያቀረቡት የጉባላፍቶ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ሀላፊ ኮማንደር ስለሽ ጉግሳ እንደሀገር ጎልተው የሚታዩ ስኬቶቻችን የህብረታችን ውጤቶች መሆናቸውን መሆናቸውን በመረዳት ህብረብሔራዊነታችን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።

‎የጉባላፍቶ ወረዳ ም/ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ትብለጥ በላይነህ የበዓሉ መከበር በሀገራችን ህገ-መንግስትና ህገ-መንግስታዊ ስርዓት ዙሪያ ህብረተሰቡ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረዉ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርና ህብረብሄራዊነትን ለማጎልበት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።

‎የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት አስተባባሪነት የወረዳው ባህል ቡድን እና አማተር ክበባት በጋራ የብሄር ብሄረሰቦች አብሮነት ውጤት ላይ መሰረት ያደረገ አጭር ተውኔት ቀርቧል።

የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት የአለም የቱሪዝም ቀንን  "ቱሪዝም ለዘላቂ ለውጥ " በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጁቶች በፓናል ውይይት ፣በስነፅሁፍ ፣ በቲያትር ፣ በሙዚቃ  ተክብሮ ...
23/10/2025

የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት የአለም የቱሪዝም ቀንን "ቱሪዝም ለዘላቂ ለውጥ " በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጁቶች በፓናል ውይይት ፣በስነፅሁፍ ፣ በቲያትር ፣ በሙዚቃ ተክብሮ ውሏል

ቱሪዝም ከኢኮኖሚ ዘርፎች አንዱ እና ዋናኛው ለወጣቶችና ለሴቶች የሰራ ዕድል መፍጠሪያ ተቋም ሲሆን የቱሪዝም መስህቦችን ማልማት፣ ማስተዋወቅና መጠበቅ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ድርሻ ነው

በፓናል ‎ውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በወረዳ ደረጃ የሚገኙ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎችን ማልማትና ማስተዋወቅ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ቢሰራ ብለዋል። በተለይም ዋሌ ኢየሱስ ፣አኖቫ ማርያም ፣ደቦት ተክለሀይማኖት የዋሻ ውስጥ ቤተክርስቲያን፣ ጉባርጃ ገነተ ልኡል ማርያም ቤተ ክርስትያን እና እዜት ቅድስት አርሴማ ገዳም የመሳሰሉት ሲሆኑ እነዚህን የቱሪዝም መስህቦች ማልማት፣ ማስተዋወቅና መጠበቅ እንደሚገባ አበክረው ተናግረዋል።

እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 አደረሳችሁ!የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ ቤት  ለወረዳችን ማህበረሰብ እና  ለኢትዮጵያውያን በሙሉ!እንኳን ለ2018፣ዓም በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤ አዲሱ...
10/09/2025

እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 አደረሳችሁ!
የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ ቤት ለወረዳችን ማህበረሰብ እና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ!
እንኳን ለ2018፣ዓም በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤
አዲሱ አመት ‘የፍቅር፣ የሰላም፣ የስኬት፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

➽ በአዲስ ዓመት አዲስ ተስፋ!
➽ እንቁጣጣሽ!

# የጉባላፍቶ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት

በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ጳጉሜን -2 የኅብር ቀን  “ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል። ‎‎በመድረኩ የጉባላፍቶ ወረዳ የጁገነት የባህ...
07/09/2025

በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ጳጉሜን -2 የኅብር ቀን “ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል።

‎በመድረኩ የጉባላፍቶ ወረዳ የጁገነት የባህል ቡድን እና አማተር ከያኒያን የብዝኃነታችን ውበት እና አቅም የሚያሳዩ የተለያዩ የኪነጥበብ ስራዎች አርበዋል።

‎ሚዲያ እና ኪነጥበብ ብዝሀነትን ጠብቆ በማቆየት እና ለሀገር ሁለንተናዊ እድገት የሚኖራቸውን ፋይዳ በሚመለከት የወረዳው መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አያሌው አስፋው አቅርበው ውይይት ተካሂዷል።

‎ # ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ!

Address

Woldia

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gubalafto woreda culture and tourism office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share