North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ

  • Home
  • Ethiopia
  • Woldia
  • North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ

North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ, Government Organization, North wollo, Woldia.

በቆቦ  ከተማ ለተደራጁ ለአስራ ሶስት ማህበራት 312 አባላት  የቤት መስሪያ ቦታ  መሰጠቱ ተገለፀ ።ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም  በእርክብክቡ ቦታ የቆቦ ከተማ አስተዳደር  ዋና ከንቲባ አቶ ...
22/04/2026

በቆቦ ከተማ ለተደራጁ ለአስራ ሶስት ማህበራት 312 አባላት የቤት መስሪያ ቦታ መሰጠቱ ተገለፀ ።

ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም በእርክብክቡ ቦታ የቆቦ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ አቶ ሀይለአብ ወንድሙ፣ የብልጽግና ፓርቲ ን/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበበ ይመር፣ የቆቦ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፓለቲካ ዘርፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን አምሃ ጨምሮ ለሎች አስተባባሪና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

መንግስት ከምንጊዜውም በላይ ዘጎች የከተማ መሬት ተጠቃሚ እንድሆን በልዩ ትኩረት እየሰራ እንዳለ የቆቦ ከተማ ዋና ከንቲባ አቶ ሀይለአብ ወንድሙ ተናገሩ።

ከተማችን የጀመረችውን ልማት አጠናክሮ ለማስቀጠል፣ ሰላሟን ለማስጠበቅ ማህበረሰቡ ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት ክቡር ከንቲባው መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዚህ መሠረት ለሀገር ትልቅ ውለታ የከፈሉ የቀድሞ ሰራዊት አባላቶችና ለሌሎች አሰራ ሁለት ማህበራት ለ312 ግለሰቦች ቤት መስሪያ ቦታ እርክብክብ ተደርጎላቸዋል።

መንግስት ለዜጎች ባመቻቸው ፖሊሲና ስትራቴጂ መሰረት ተደራጅተው ለቆጠቡ አሰራ ሶስት ማህበር ከይገበኛል ነፃ የሆነ መሬት በስማቸው መተላለፉ ትልቅ ስኬት እንደሆነ የቆቦ ከተማ መሬት ጽ/ቤት ኃላፊ አዲሱ ወዳጆ ዶ/ር ተናግሯል።

በማህበር ለተደራጁ አካላት በከተማ መሬትን እንዲያገኙ በተደነገገው መሠረት በዛሬው ዕለት የእርክብክብ ስራው ተፈጽሟል ያሉት አዲሱ ወዳጆ ዶ/ር ለቀጣዩም ተጠናክሮ የሚቀጥል ተግባር ነውም ብለዋል።

በመጨረሻም የማህበሩ አባላቶችም እጅግ በጣም ደስተኛ መሆናቸውን ገልጾ ለተመቻቸው ምቹ ዕድልና ስኬት መንግስትንና ባለድር አካላትን አመስግነዋል።

ዘገባው የሰሜን ወሎ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

16/04/2026

የሰሜን ወሎ ዞን ህዝብ ቅሬታ ሰሚ ጽ/ቤት የበጀት አመቱን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ገመገመ።

ሚያዝያ 8/2018ዓ.ም ወልዲያ

የሰሜን ወሎ ዞን ህዝብ ቅሬታ ሰሚ ጽ/ቤት በበጀት አመቱ በእቅድ የተያዙ ተግባራትን የገመገመ ሲሆን በዘጠኝ ወራት ውስጥ በግልና በቡድን አቤቱታ ላቀረቡ 239 የህብረተሰብ ክፍሎች ምላሽ መስጠቱን አሳውቋል።

ጽ/ቤቱ በበጀት አመቱ በማህበረሰብ አቀፍ ተጠያቂነት አሃዝ ካርድ በተመረጡ ቀበሌዎች ላይ ህብረተሰቡ የመረጣቸውን ተቋማት ፍተሻ የማድረግና በህብረተሰቡ የተለዩትን ችግሮች የሚፈቱበትን አግባብ በማስቀመጥ እየሰራ መቆየቱን ከግምገማው መረዳት የተቻለ ሲሆን በመንግስት ተቋማትም የአገልግሎት አሰጣጥ ፍተሻ በማድረግ የቅሬታ ምንጮችን ለማድረቅ በሚያስችል መልኩ ለ42ተቋማት በተዘጋጀ ቼክሊስት ፍተሻ መደረጉን ማረጋገጥ ተችሏል

በሰሜን ወሎ ዞን በቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር የሚገነባው የአንድ ማዕከል/መሶብ/አገልግሎት መስጫ ማዕከል ግንባታ ዲዛይን ይህን ይመስላል ለተፈፃሚነቱ በእውቀት ፣ በጉልበትና በገንዘብ ድጋ...
14/04/2026

በሰሜን ወሎ ዞን በቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር የሚገነባው የአንድ ማዕከል/መሶብ/አገልግሎት መስጫ ማዕከል ግንባታ ዲዛይን ይህን ይመስላል ለተፈፃሚነቱ በእውቀት ፣ በጉልበትና በገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ይጠበቃል

በኢትዮጵያ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24/2018ዓ.ም መካሔድ እንዳለበት የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ካሳወቀ በኋላ ከየካቲት 28 ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ በማድረግ እስከ መጋቢት 24 ድረስ 36...
04/04/2026

በኢትዮጵያ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ግንቦት 24/2018ዓ.ም መካሔድ እንዳለበት የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ካሳወቀ በኋላ ከየካቲት 28 ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ በማድረግ እስከ መጋቢት 24 ድረስ 36.9ሚሊየን ዜጎች የምርጫ ካርድ ማውጣታቸውን ምርጫ ቦርድ አሳውቋል በቀሪ ቀናትም ምዘገባው ተጠናክሮ የሚቀጠል ይሆናል።

10/03/2026
10/03/2026
07/03/2026
07/03/2026

Address

North Wollo
Woldia

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share