Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wereta
  • Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት በወረዳው ውስጥ የሚከናወኑ ሰላም ነክና ሀገራዊ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ጋር የተያያዙ መረጃዎች ይሰራጭበታል።

በፎገራ ወረዳ ለአገር መከላከያ ሠራዊት የተመለመሉ ወጣቶች፦በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ የአገር መከላከያ ሠራዊት ያወጣውን የቅጥር ማስታወቂያ አሟልተው ወደ ስልጠና ቦታ ለመሄድ በዝግጅት ...
14/08/2026

በፎገራ ወረዳ ለአገር መከላከያ ሠራዊት የተመለመሉ ወጣቶች፦

በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ የአገር መከላከያ ሠራዊት ያወጣውን የቅጥር ማስታወቂያ አሟልተው
ወደ ስልጠና ቦታ ለመሄድ በዝግጅት ላይ ያሉ ምልምል ወጣቶችን የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ደጀኔ ፣ የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ገብሬ ፣ ሌሎችም የስራ ኃላፊዎችና የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ወጣቶችን አበረታተዋል።

በፎገራ ወረዳ የጎርፍ አደጋ ለመከላከል የቅድመ ዝግጅት ስራና የቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ውይይት አካሂዷል።በደቡብ ጎንደር ዞን በፎገራ ወረዳ የጎርፍ አደጋ ለመከላከል የቅድመ ዝግጅት ስ...
11/08/2026

በፎገራ ወረዳ የጎርፍ አደጋ ለመከላከል የቅድመ ዝግጅት ስራና የቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ውይይት አካሂዷል።

በደቡብ ጎንደር ዞን በፎገራ ወረዳ የጎርፍ አደጋ ለመከላከል የቅድመ ዝግጅት ስራና የቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጠ ያለመ ውይይት ተካሂዷል።

ክረምቱን ተከትሎ የሚከሰተው የጎርፍ መጥለቅለቅ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመከላከል ኮሚቴው የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።

የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ገብሬ ወረዳው ሜዳማ እና በርብና ጉማራ ወንዝ መካከል የሚገኝ ለጎርፍ ተጋላጭ መሆኑን ጠቁመው የአደጋ መከላከል ዝግጅት ኮሚቴው ባቀደው እቀድ መሰረት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ፈጠራ ስራ መስራትና መረጃዎች በወቅቱ መስጠት ይገባል ፤የጎርፍ መጥለቅለቅ በሚከሰትባቸው ቀበሌዎች መደረግ ያለባቸውን ተግባራት በአፋጣኝ ለማከናወን መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ጎርፍን ለመከላከል በበጋ ወቅት የመከላከል ስራዎች መሰራታቸውን አቶ ጌታቸው ገልጸው የጎርፍ መጥለቅለቅ ለመከላከል የውሀ ማፋሰሻ ቦዮችን ማፋሰስ ፣ በዘጠኙ ቀበሌዎች አደጋ ቢከሰት የማረፊያ ቦታዎችን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፣የአስቸኳይ ጊዜ ቁሳቁስ ፣ምግብ ማመቻቸት እንደሚጠበቅና የተዋቀሩት ኮሚቴዎች በጋራ በመቀናጀት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በተያያዘ ከተረጅነት ወደ ምርታማነት በተነሱ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

የፎገራ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን

አስገድዶ የደፈረው ወጣት በፅኑ እስራት መቀጣቱን የፎገራ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት መርማሪ ዋና ሳጅን እዮብ አመራ እንዳሉት የግል ተበዳይ በፎገራ...
05/08/2026

አስገድዶ የደፈረው ወጣት በፅኑ እስራት መቀጣቱን የፎገራ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።

በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት መርማሪ ዋና ሳጅን እዮብ አመራ እንዳሉት የግል ተበዳይ በፎገራ ወረዳ አለምበር ዙሪያ ቀበሌ ነዋሪ የሆነች የ15 ዓመት እድሜ እና የ7ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ሰኔ 17/2018 ዓ.ም በጋዞ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የማጠቃለያ ፈተና ተፈትና ወደቤቷ ስትመለስ ተከሳሽ መኳንት አበበ ገዜ የተባለው የ18 ዓመት ወጣት የሃይል ድርጊት በመጠቀም በፎገራ ወረዳ ጫልማና ዲሙ ቀበሌ የተከሳሹ ቅርብ ቤተሰብ ቤት በመውሰድ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅሟል።

የተበዳይ ቤተሰቦች ልጅቱን እያፈላለጉ መሆኑን መረጃ የደረሰው ተከሳሽ ሰኔ 18/2018 ዓ.ም እጁን ለህግ ሰጥቷል። የፎገራ ወረዳ ፖሊስም በሰውና በሰነድ ማስረጃ ጉዳዩን አጣርቶ ለፎገራ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ አስተላልፎ ዐቃቤ ሕግም መዝገቡን ለፍርድ ቤት አቅርቦ ክሱን ከተመለከተ በኋላ ተከሳሹ በቀረበበት ክስ ላይ መከላከል ባለመቻሉ ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል ብለዋል።

እንደ ዋና ሳጅን እዮብ ማብራሪያ ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን የክስ መዝገብ መርምሮ ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል በሚል በ8 ዓመት ከ4 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉን አብራርተዋል።

በመጨረሻም ሌሎች መሰል አጥፊዎች ከዚህ አይነት ድርጊት እንዲቆጠቡ ያሳሰቡት ዋና ሳጅን እዮብ በህፃናትና ሴቶች ላይ የሚፈፀሙ መሰል ድርጊቶችን ማህበረሰቡ ቀድሞ መከላከል ይገባል ተፈፅሞ ሲገኝም ለህግ አካል መጠቆም እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ፡፡

ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ወጣቶች ሀገራቸውን እና ማህበረሰባቸውን እንዲያውቁ እና የሀገር ፍቅር ስሜት በውስጣቸው እንዲሰርጽ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው፡፡ፕሮግራሙ ወጣቶች ...
29/07/2026

ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ወጣቶች ሀገራቸውን እና ማህበረሰባቸውን እንዲያውቁ እና የሀገር ፍቅር ስሜት በውስጣቸው እንዲሰርጽ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው፡፡

ፕሮግራሙ ወጣቶች የኢትዮጵያን እሴቶችን እና መርሆችን በውል ተገንዝበው በዘር፣ በጎሳ፣ በሃይማኖት እና በሌሎችም ማንነቶች ላይ መሠረት አድርጎ ያለውን መከፋፈል እና ጥርጣሬ የሚያስወግድ ብሎም የወጣቶችን የሀገር እና የሕዝብ ፍቅር የሚያሳድግ ነው፡፡

ሀገራዊ ፕሮግራሙ ወጣቱን ከሕዝብ ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ከሕዝቡ ዘንድ ያለውን ተጨባጭ እውነታ እንዲያውቁት በማድረግ
⚡️ ለሰላም፣
⚡️ ለሀገር ግንባታ እና
⚡️ ለልማት ከፍተኛ ድርሻ እንዲያበረክቱ ዕድል የሚሰጥ ነው፡፡

ሰላም ለኢትዮጵያ!

በፎገራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለዋል። .የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በፎገራ ወረዳ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግዛቸው መንገው የ...
23/07/2026

በፎገራ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም አማራጭ ተቀብለዋል። .
የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በፎገራ ወረዳ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግዛቸው መንገው የሚመሩ ታጣቂዎች እጃቸውን በሰላም የሰጡ ሲሆን የህዝባችን ስቃይና እንግልት በመረዳት እና ኢትዬጵያን ለማፈራረስ ከሚሰሩ የታሪካዊ ጠላቶቻችንን ጋር በጋራ አንሰራም ብለዋል።
ታጣቂዎቹም በቀጣይ በጦርነት የባከነውን ጊዜ በልማት ለማካካስ ከመንግስት ጎን በመሆን ህዝባቸውን ለመካስ ቀን ከሌት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ሀምሌ 16/2018 አ.ም
ፎገራ ኮሙዩኒኬሽን

የሰላም አስከባሪዎች የሃገር ሰላምና ደህንነትን በማስጠበቅ የሃገር አለኝታዎች መሆናቸውን የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አስታወቀ።በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በወረዳው የሚገኘ...
15/07/2026

የሰላም አስከባሪዎች የሃገር ሰላምና ደህንነትን በማስጠበቅ የሃገር አለኝታዎች መሆናቸውን የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አስታወቀ።

በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በወረዳው የሚገኘውን የሰላም አስከባሪ ሃይል በቀጣይ ህግን ከማስከበር አኳያ ያለውን ዝግጁነት በማጠናከር በስነ ልቦና ዝግጁ እንዲሆን ለማበረታታት በማለም የደቡብ ጎንደር ዞን እና የወረዳው የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የአገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው አካላት በመገኘት የሰላም አስከባሪ ሃይልን አበረታተዋል።

የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ጌታቸው ገብሬ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት የሰላም አስከባሪ ሃይል የህግ የበላይነትን በማስከበርና በማስጠበቅ በኩል ከፍተኛ ሚና ሲወጣ የቆየና አሁንም እየተወጣ የሚገኝ የሃገር አለኝታዎች ናቸው ብለዋል።

የሰላም አስከባሪ ሃይል በዲሲፕሊን በመታነፅ፣ በስነ-ምግባር የዳበረ አካባቢውን ከማንኛውም ፀረ ሰላም ሃይል ሊጠብቅ የሚችል የተደራጀ የጸጥታ ሃይል ነው ያሉት አቶ ጌታቸው የአላማ ፅናት ፣ ቁርጠኝነት ፣ አይበገሬነትንም ሊላበስ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

የፎገራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን


የስራ ማስታወቂያ የሀገር መከላከያ ሚኒስትር በመደበኛ ሰራዊት እና ከታች በተዘረዘሩት የሙያ ዘርፎች ፍላጎት ያላቸውን መቅጠርና ማሰልጠን ይፈልጋል ።በአይሲቲ ሙያተኛለእጩ መኮነንነትለህግ ሙያተ...
14/07/2026

የስራ ማስታወቂያ
የሀገር መከላከያ ሚኒስትር በመደበኛ ሰራዊት እና ከታች በተዘረዘሩት የሙያ ዘርፎች ፍላጎት ያላቸውን መቅጠርና ማሰልጠን ይፈልጋል ።

በአይሲቲ ሙያተኛ
ለእጩ መኮነንነት
ለህግ ሙያተኛ
ለመሀንዲስ ሙያተኞች
ለጤና ሙያተኞች
ለሎጅስቲክ
በተጨማሪም
ለኢንጅነሪንግ ፣ለጤና ሳይንስና፣ ለሪሶርስ ማኔጅመንት መግባትና መሰልጠን ለሚፈልጉ
እድሜ ከ18-27
ሙሉ ጤንነትና ያለው
ለወንድ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ
ለሴት ዲፕሎማና በመሰል ያጠናቀቁ
የመመዝገቢያ ጊዜ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ነሃሴ 16/2018
መመዝገቢያ ቦታ ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት  አስመርቋል።በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት የዞንና የወረዳው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የ...
22/06/2026

ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት አስመርቋል።

በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት የዞንና የወረዳው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች አስመርቋል።

በመርሃ ግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ጥላሁን ደጀኔ በአገራችን ታሪክ ውስጥ ሚሊሻ የፅናት ተምሳሌት ነው። የአገር ዳር ደንበር በተደፈረበት ጊዜ በግንባር ቀደምትነት በመሰለፍ መስዕዋትነት በመክፈል ክብሯንና ነፃነቷን ይዛ እንድትቀጥል ያደረገ አሁንም ለአገርና ለህዝብ ሰላም እየተዋደቀ እንደሚገኝ ያመላከቱት አቶ ጥላሁን የአካባቢያችን ሰላም ለማረጋገጥ ተመራቂ የሚሊሻ አባላት በህዝብና በመንግስት ከፍተኛ ኃላፊነት የተጣለባችሁ በመሆኑ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል።

የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ጌታቸው ገብሬ ሚሊሻነት ከራስ ጥቅም በላይ የህዝብን ደህንነት ማስቀደም ነው። ዛሬ የምትረከቡት ኃላፊነት የጋራ ሰላማችንን ለመጠበቅ፣ የህግ የበላይነትን ለማስከበር እና የሀገር ሉዓላዊነትን ለመከላከል የምታደርጉት የቆራጥነት ምልክት ነው።
እናንተ የጀመራችሁት ጉዞ ቀላል አይደለም፤ ነገር ግን ታሪክ የሚዘክረው የሀገር ልጅነት ግዴታችሁን ነው።

ተመራቂ የሚሊሻ አባላት ለህግ የበላይነት መቆም ፣ታማኝነትና ዲሲፕሊን፣ ከህዝብ ጋር ያለን አንድነት የሚሉ መርሆዎችን መከተል እንደሚገባቸው ያመላከቱት አቶ ጌታቸው ሀገር በምትፈልጋችሁ ጊዜ ሁሉ ለህዝባችሁ እና ለሀገራችሁ የደህንነት ጋሻ በመሆን የገባችሁትን ቃል ኪዳን እንደምትጠብቁ ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል ።

የደቡብ ጎንደር ዞን ንግድና ገብያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ እንድርያስ ማሩ በበኩላቸው የፎገራ ወረዳ ሚሊሻ ቀውስ በገጠመን ስዓት የህዝብንና የሀገርን ደህንነት ለመጠበቅ በቀደምትነት የሚሰለፍና የህዝብን ሰላሞ እያስከበረ ያለ ጀግና ህዝባዊ ሃይል ነው። ተመራቂ የሚሊሻ አባላት አላማችን የህዝብን ደህንነትና ሰላም መጠበቅ በመሆኑ ቅድሚያ ለህዝብ ደህንነትና ሰላም መስጠት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የፎገራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን

የአማራ ክልል ሚሊሻ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በባህር ዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ነው።የአማራ ክልል ሚሊሻ የተመሰረተበትን 30ኛ ዓመት በዓል "የጀግንነት ታሪካችንን እያደስን፤ ዝ...
06/06/2026

የአማራ ክልል ሚሊሻ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በባህር ዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ነው።

የአማራ ክልል ሚሊሻ የተመሰረተበትን 30ኛ ዓመት በዓል "የጀግንነት ታሪካችንን እያደስን፤ ዝግጁነታችንን እናረጋግጣለን!" በሚል መሪ ቃል ዛሬ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በክልሉ ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ በታላቅ ድምቀት ማክበር ጀምሯል።

በዚህ ታሪካዊ የምስረታ በዓል አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ከእነዚህም መካከል አቶ ተመስገን ጥሩነህ የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ መሀመድ እንድሪስ የኢፌድሪ ሰላም ሚኒስትር፣ ክብርት ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ፣ ኮሚሽነር ጀኔራል ዘላለም መንግሥቴ (ዶ/ር) የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ፣ አቶ ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር፤

እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል እና የክልል የሥራ ኃላፊዎችና እንግዶች በክብረ በዓሉ ላይ ታድመዋል።

የሚሊሻውን 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ለየት የሚያደርገው ለሀገርና ለወገን ውድ ህይወታቸውን የገበሩና የላቀ ተጋድሎ የፈጸሙ አባላትን የሚዘክር መሆኑ ነው።

ከበዓሉ መርሃ-ግብር ለማወቅ እንደተቻለው በግዳጅ ቀጠናዎች ላይ በመሰማራት የላቀ ጀብዱ እና የጀግንነት ታሪክ ለፈጸሙ የሚሊሻ አባላት እንዲሁም ለሀገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ሰላም ሲሉ በጀግንነት ለተሰው የሚሊሻ አባላት እና አመራሮች ቤተሰቦች የእውቅና ሽልማት ይበረከትላቸዋል።

ይህ የምስረታ በዓል የሚሊሻውን የቆየ የጀግንነት ታሪክ ከማደስ ባለፈ የአባላቱን ዝግጁነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለቀጣይ ተልዕኮዎች ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በፎገራ ወረዳና ወረታ ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም ተጠናቋል" የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤትበደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ  ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ...
02/06/2026

በፎገራ ወረዳና ወረታ ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም ተጠናቋል"
የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት

በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር ከተማው ፈጠነ "በፎገራ 1 እና 2" 7ኛው ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

የጸጥታ አካላት የተናበበና የተቀናጀ ስራ በመሰራቱ ህብረተሰቡ ያለምንም የፀጥታ ስጋት ድምፁን መስጠት ችሏል ያሉት የፖሊስ አዛዡ ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ፍጹም ገለልተኛ ሆኖ ህገ መንግስታዊ ኃላፊነቱን በመወጣቱ ምርጫው ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በመጨረሻም የምርጫው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን ለተወጡት ጥምር የፀጥታ አካላት ፤ለፎገራና ወረታ ከተማ ማህበረሰብ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Address

Wereta

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share