15/07/2026
የሰላም አስከባሪዎች የሃገር ሰላምና ደህንነትን በማስጠበቅ የሃገር አለኝታዎች መሆናቸውን የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አስታወቀ።
በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በወረዳው የሚገኘውን የሰላም አስከባሪ ሃይል በቀጣይ ህግን ከማስከበር አኳያ ያለውን ዝግጁነት በማጠናከር በስነ ልቦና ዝግጁ እንዲሆን ለማበረታታት በማለም የደቡብ ጎንደር ዞን እና የወረዳው የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የአገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው አካላት በመገኘት የሰላም አስከባሪ ሃይልን አበረታተዋል።
የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ጌታቸው ገብሬ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት የሰላም አስከባሪ ሃይል የህግ የበላይነትን በማስከበርና በማስጠበቅ በኩል ከፍተኛ ሚና ሲወጣ የቆየና አሁንም እየተወጣ የሚገኝ የሃገር አለኝታዎች ናቸው ብለዋል።
የሰላም አስከባሪ ሃይል በዲሲፕሊን በመታነፅ፣ በስነ-ምግባር የዳበረ አካባቢውን ከማንኛውም ፀረ ሰላም ሃይል ሊጠብቅ የሚችል የተደራጀ የጸጥታ ሃይል ነው ያሉት አቶ ጌታቸው የአላማ ፅናት ፣ ቁርጠኝነት ፣ አይበገሬነትንም ሊላበስ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
የፎገራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን