Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wereta
  • Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት በወረዳው ውስጥ የሚከናወኑ ሰላም ነክና ሀገራዊ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ጋር የተያያዙ መረጃዎች ይሰራጭበታል።

የሰላም አስከባሪዎች የሃገር ሰላምና ደህንነትን በማስጠበቅ የሃገር አለኝታዎች መሆናቸውን የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አስታወቀ።በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በወረዳው የሚገኘ...
15/07/2026

የሰላም አስከባሪዎች የሃገር ሰላምና ደህንነትን በማስጠበቅ የሃገር አለኝታዎች መሆናቸውን የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አስታወቀ።

በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በወረዳው የሚገኘውን የሰላም አስከባሪ ሃይል በቀጣይ ህግን ከማስከበር አኳያ ያለውን ዝግጁነት በማጠናከር በስነ ልቦና ዝግጁ እንዲሆን ለማበረታታት በማለም የደቡብ ጎንደር ዞን እና የወረዳው የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የአገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው አካላት በመገኘት የሰላም አስከባሪ ሃይልን አበረታተዋል።

የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ጌታቸው ገብሬ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት የሰላም አስከባሪ ሃይል የህግ የበላይነትን በማስከበርና በማስጠበቅ በኩል ከፍተኛ ሚና ሲወጣ የቆየና አሁንም እየተወጣ የሚገኝ የሃገር አለኝታዎች ናቸው ብለዋል።

የሰላም አስከባሪ ሃይል በዲሲፕሊን በመታነፅ፣ በስነ-ምግባር የዳበረ አካባቢውን ከማንኛውም ፀረ ሰላም ሃይል ሊጠብቅ የሚችል የተደራጀ የጸጥታ ሃይል ነው ያሉት አቶ ጌታቸው የአላማ ፅናት ፣ ቁርጠኝነት ፣ አይበገሬነትንም ሊላበስ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

የፎገራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን


የስራ ማስታወቂያ የሀገር መከላከያ ሚኒስትር በመደበኛ ሰራዊት እና ከታች በተዘረዘሩት የሙያ ዘርፎች ፍላጎት ያላቸውን መቅጠርና ማሰልጠን ይፈልጋል ።በአይሲቲ ሙያተኛለእጩ መኮነንነትለህግ ሙያተ...
14/07/2026

የስራ ማስታወቂያ
የሀገር መከላከያ ሚኒስትር በመደበኛ ሰራዊት እና ከታች በተዘረዘሩት የሙያ ዘርፎች ፍላጎት ያላቸውን መቅጠርና ማሰልጠን ይፈልጋል ።

በአይሲቲ ሙያተኛ
ለእጩ መኮነንነት
ለህግ ሙያተኛ
ለመሀንዲስ ሙያተኞች
ለጤና ሙያተኞች
ለሎጅስቲክ
በተጨማሪም
ለኢንጅነሪንግ ፣ለጤና ሳይንስና፣ ለሪሶርስ ማኔጅመንት መግባትና መሰልጠን ለሚፈልጉ
እድሜ ከ18-27
ሙሉ ጤንነትና ያለው
ለወንድ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ
ለሴት ዲፕሎማና በመሰል ያጠናቀቁ
የመመዝገቢያ ጊዜ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ነሃሴ 16/2018
መመዝገቢያ ቦታ ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት  አስመርቋል።በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት የዞንና የወረዳው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የ...
22/06/2026

ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት አስመርቋል።

በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የሚሊሻ አባላት የዞንና የወረዳው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች አስመርቋል።

በመርሃ ግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ጥላሁን ደጀኔ በአገራችን ታሪክ ውስጥ ሚሊሻ የፅናት ተምሳሌት ነው። የአገር ዳር ደንበር በተደፈረበት ጊዜ በግንባር ቀደምትነት በመሰለፍ መስዕዋትነት በመክፈል ክብሯንና ነፃነቷን ይዛ እንድትቀጥል ያደረገ አሁንም ለአገርና ለህዝብ ሰላም እየተዋደቀ እንደሚገኝ ያመላከቱት አቶ ጥላሁን የአካባቢያችን ሰላም ለማረጋገጥ ተመራቂ የሚሊሻ አባላት በህዝብና በመንግስት ከፍተኛ ኃላፊነት የተጣለባችሁ በመሆኑ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል።

የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ጌታቸው ገብሬ ሚሊሻነት ከራስ ጥቅም በላይ የህዝብን ደህንነት ማስቀደም ነው። ዛሬ የምትረከቡት ኃላፊነት የጋራ ሰላማችንን ለመጠበቅ፣ የህግ የበላይነትን ለማስከበር እና የሀገር ሉዓላዊነትን ለመከላከል የምታደርጉት የቆራጥነት ምልክት ነው።
እናንተ የጀመራችሁት ጉዞ ቀላል አይደለም፤ ነገር ግን ታሪክ የሚዘክረው የሀገር ልጅነት ግዴታችሁን ነው።

ተመራቂ የሚሊሻ አባላት ለህግ የበላይነት መቆም ፣ታማኝነትና ዲሲፕሊን፣ ከህዝብ ጋር ያለን አንድነት የሚሉ መርሆዎችን መከተል እንደሚገባቸው ያመላከቱት አቶ ጌታቸው ሀገር በምትፈልጋችሁ ጊዜ ሁሉ ለህዝባችሁ እና ለሀገራችሁ የደህንነት ጋሻ በመሆን የገባችሁትን ቃል ኪዳን እንደምትጠብቁ ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል ።

የደቡብ ጎንደር ዞን ንግድና ገብያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ እንድርያስ ማሩ በበኩላቸው የፎገራ ወረዳ ሚሊሻ ቀውስ በገጠመን ስዓት የህዝብንና የሀገርን ደህንነት ለመጠበቅ በቀደምትነት የሚሰለፍና የህዝብን ሰላሞ እያስከበረ ያለ ጀግና ህዝባዊ ሃይል ነው። ተመራቂ የሚሊሻ አባላት አላማችን የህዝብን ደህንነትና ሰላም መጠበቅ በመሆኑ ቅድሚያ ለህዝብ ደህንነትና ሰላም መስጠት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የፎገራ ወረዳ ኮሙኒኬሽን

የአማራ ክልል ሚሊሻ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በባህር ዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ነው።የአማራ ክልል ሚሊሻ የተመሰረተበትን 30ኛ ዓመት በዓል "የጀግንነት ታሪካችንን እያደስን፤ ዝ...
06/06/2026

የአማራ ክልል ሚሊሻ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በባህር ዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ነው።

የአማራ ክልል ሚሊሻ የተመሰረተበትን 30ኛ ዓመት በዓል "የጀግንነት ታሪካችንን እያደስን፤ ዝግጁነታችንን እናረጋግጣለን!" በሚል መሪ ቃል ዛሬ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በክልሉ ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ በታላቅ ድምቀት ማክበር ጀምሯል።

በዚህ ታሪካዊ የምስረታ በዓል አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ከእነዚህም መካከል አቶ ተመስገን ጥሩነህ የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ መሀመድ እንድሪስ የኢፌድሪ ሰላም ሚኒስትር፣ ክብርት ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ፣ ኮሚሽነር ጀኔራል ዘላለም መንግሥቴ (ዶ/ር) የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ፣ አቶ ኮሚሽነር አስቻለው አላምሬ የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር፤

እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል እና የክልል የሥራ ኃላፊዎችና እንግዶች በክብረ በዓሉ ላይ ታድመዋል።

የሚሊሻውን 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ለየት የሚያደርገው ለሀገርና ለወገን ውድ ህይወታቸውን የገበሩና የላቀ ተጋድሎ የፈጸሙ አባላትን የሚዘክር መሆኑ ነው።

ከበዓሉ መርሃ-ግብር ለማወቅ እንደተቻለው በግዳጅ ቀጠናዎች ላይ በመሰማራት የላቀ ጀብዱ እና የጀግንነት ታሪክ ለፈጸሙ የሚሊሻ አባላት እንዲሁም ለሀገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ሰላም ሲሉ በጀግንነት ለተሰው የሚሊሻ አባላት እና አመራሮች ቤተሰቦች የእውቅና ሽልማት ይበረከትላቸዋል።

ይህ የምስረታ በዓል የሚሊሻውን የቆየ የጀግንነት ታሪክ ከማደስ ባለፈ የአባላቱን ዝግጁነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለቀጣይ ተልዕኮዎች ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በፎገራ ወረዳና ወረታ ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም ተጠናቋል" የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤትበደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ  ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ...
02/06/2026

በፎገራ ወረዳና ወረታ ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም ተጠናቋል"
የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት

በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር ከተማው ፈጠነ "በፎገራ 1 እና 2" 7ኛው ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

የጸጥታ አካላት የተናበበና የተቀናጀ ስራ በመሰራቱ ህብረተሰቡ ያለምንም የፀጥታ ስጋት ድምፁን መስጠት ችሏል ያሉት የፖሊስ አዛዡ ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ፍጹም ገለልተኛ ሆኖ ህገ መንግስታዊ ኃላፊነቱን በመወጣቱ ምርጫው ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በመጨረሻም የምርጫው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን ለተወጡት ጥምር የፀጥታ አካላት ፤ለፎገራና ወረታ ከተማ ማህበረሰብ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በወረታ ከተማ እና ፎገራ ወረዳ በጋራ  ብልፅግና ፓርቲን ለመደገፍ የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በሰላም ተጠናቋል።
26/05/2026

በወረታ ከተማ እና ፎገራ ወረዳ በጋራ ብልፅግና ፓርቲን ለመደገፍ የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በሰላም ተጠናቋል።

የኢፌዴሪ አየር ኃይል የምልመላ ማስታወቂያ በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል፤ በተዋጊ አውሮፕላን አብራሪነት እና በቴክኒሽያንነት የሙያ ዘርፎች ፍላጎት ያላቸውንና የምልመላ መስ...
13/05/2026

የኢፌዴሪ አየር ኃይል የምልመላ ማስታወቂያ

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል፤ በተዋጊ አውሮፕላን አብራሪነት እና በቴክኒሽያንነት የሙያ ዘርፎች ፍላጎት ያላቸውንና የምልመላ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶችን መልምሎ ለማሰልጠን ይፈልጋል።

✅ አጠቃላይ መመዘኛዎች
• ዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆኑ፤
• ለኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት ተገዥ የሆኑ፤
• መልካም ሥነ-ምግባር ያላቸው፣
• በውትድርና ለማገልገልና ሙያው የሚጠይቀውን ሥልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆኑ፤
• የወንጀል ጥፋት ሪከርድ የሌለባቸው ለመሆኑ ከትውልድ ቦታቸው ወይም ከሚኖሩበት አካባቢ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
• ሙሉ ጤንነት ያላቸውና የሕክምና ምርመራ ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆኑ፤
• ከዚህ በፊት በውትድርና ወይም በፖሊስነት ያልሰሩና የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆኑ እንዲሁም ትዳር ያልመሰረቱ።

✅ ለትምህርትና ሌሎች መመዘኛዎች
ለተዋጊ አውሮፕላን አብራሪነት የምልመላ መስፈርቶች
• የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆነው ከ2015-2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው አጠቃላይ ውጤት 350 እና ከዚያ በላይ ያላቸው፤
• በእንግሊዝኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ ትምህርቶች አማካይ ውጤት 50% እና ከዚያ በላይ ያላቸው፤
• እድሜ ከ18-22 ዓመት፣ ቁመት አንድ ሜትር ከ65 እና ከዚያ በላይ እንዲሁም ክብደት ከ50-65 ኪሎግራም የሆኑ።

✅ ለቴክኒሽያንነት የምልመላ መስፈርቶች
• የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆነው በ2015-2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው አጠቃላይ ውጤት 200 እና ከዚያ በላይ ያላቸው፤
• እድሜያቸው ከ25 ዓመት ያልበለጠ፣ ቁመታቸው 1.65 ሜትር እና ክብደታቸው ከ50-65 ኪሎ ግራም የሆኑ።

✅ ለአጫጭር ኮርስ ሰልጣኞች የመመልመያ መስፈርቶች
• በመጀመሪያ ዲግሪ በሜካኒካል፣ በኤሌክትሪካልና በኮምፒውተር የሙያ ዘርፎች የተመረቁ፤ እንዲሁም በተለያዩ የቴክኒክ ሙያዎች በደረጃ 4 እና በደረጃ 5 ተረምቀው የሲኦሲ ምዘና ውጤት ያላቸው፤
• እድሜ ከ27 ዓመት ያልበለጡና ቁመት 1 ሜትር ከ65 የሆኑ።

✅ የሙያ አይነቶቹን ሙሉ ዝርዝር በየምዝገባ ጣቢያዎቹ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

✅ መስፈርቱን የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች የ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ማስረጃዎቻችሁን ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን፤ በአየር ኃይል አካዳሚ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ ይጠበቅባችኋል።

✅ ምዝገባ ቦታ- ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በልማት፣በሰላም፣በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በፓርቲ ተግባራት ዙሪያ ከመንግስት ሰራተኛው ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አስተዳደር...
11/05/2026

የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በልማት፣በሰላም፣በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በፓርቲ ተግባራት ዙሪያ ከመንግስት ሰራተኛው ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።

በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አስተዳደር በልማት፣በሰላም፣በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በፓርቲ ተግባራት ዙሪያ ከመንግስት ሰራተኛው ጋር የክልል፣የዞን እንዲሁም የወረዳ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ገብሬ በኢኮኖሚው ፣በማህበራዊና ፖለቲካዊ ዘርፉ የተሻለ ስራ መስራት ከተቻለ ዘላቂ ሰላምን ማስፈንና መገንባት እንችላለን ብለው ካጋጠመው ችግር ለመውጣት ከሀገር ሽማግሌዎች ፣ከወጣቶች ፣ ሴቶች ፣ነጋዴዎች ጋር ሰላምን ለማጽናት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል።
የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ ፣በህዝቡ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ሁኖ እንዲጠናቀቅ የመንግስት ሰራተኛው የበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

የደቡብ ጎንደር ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ እንድሪያስ ማሩ በበኩላቸው የሰላም እና የልማት ስራዎች ላይ ዘላቂነትን በመፍጠር ተቋማት በትኩረት መስራት ይገባል ብለው የልማት ስራዎች ያላቸውን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች በመረዳት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እድልን መጠቀም ያስፈልጋል ብለዋል።ምርጫ ሁሉንም ዜጋ ስለሚመለከተው ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

በአብክመ ግብርና ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ በምክትል ቢሮ ደረጃ የሆኑት አቶ አምሳሉ ጎበው እንደ ሀገር ፣ክልል፣ዞን ብሎም ወረዳ ግጭት ውስጥ እንገኛለን፤ትልቅ ጸጋ የሆነው የሰው ሀብትእልቂት እየተፈጸመ በመሆኑ የመንግስት ሰራተኛው የተዛባ አመለካከትን በመቅረፍ ለውጥ መምጣት ያስፈልጋል ብለዋል።

ወረዳው ሰላምን ለማስፈን የጸጥታ መዋቅር በማደራጀት እየሰራ ይገኛል ይሁን እንጅ የሰላም ጉዳይ የሁሉም ሚና ስለሚያስፈልግ በመነጋገርና በመቀናጀት ማስፈንና ለሀገራዊ ምርጫተሳታፊ መሆን ይገባል ሲሉ አሳስበዋል ።
ወቅታዊ የነዳጅ እጥረት፣ትራንስፖርት ዘርፍ የታሪፍ ጭማሪን አስመልክቶ ፣የኑሮ ውድነት፣የግብርና ፣የትምህርት እንዲሁም ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይቶች ተደርገው አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

ቀጣይ በሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ተሳታፊ እንደሚሆኑና በሌሎች የልማት ስራዎችላይም የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።
ፎገራ ኮሙዩኒኬሽን

የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ኃይላችን  ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጋር በግንባር ቀደምትነት በመሰለፍና በቁርጠኝት በመፋለም የዘራፊ ቡድኑን ህልም ቅዠት ሆኖ እንዲቀር አድርጓል"፡፡የፎገራ ወረዳ ዋ...
24/04/2026

የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ኃይላችን ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጋር በግንባር ቀደምትነት በመሰለፍና በቁርጠኝት በመፋለም የዘራፊ ቡድኑን ህልም ቅዠት ሆኖ እንዲቀር አድርጓል"፡፡
የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ገብሬ

በፎገራ ወረዳና ወረታ ከተማ አስተዳደር 30ኛ አመት የሚሊሻ ፅህፈት ቤት የምስረታ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ነው።
በዚሁ ዝግጅት ንግግር ያደረጉት የፎገራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ገብሬ ከሀምሌ 2015 ጀምሮ ክልሉ የገጠመውን የሰላም መደፍረስ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ኃይላችን ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጋር በግንባር ቀደምትንት በመሰለፍና በቁርጠኝት በመፋለም የዘራፊ ቡድኑን ህልም ቅዠት ሆኖ እንዲቀር አድርጓል ፡፡
አሁን የመጣው አንፃራዊ ሰላም ከፍተኛ ዋጋ ተከፍሎበታል ፣ ዛሬም ድረስ በዓላማው እንደጸና ዋጋ እየከፈለ ይገኛል ብለዋል ፡፡

እንደ ዋና አስተዳዳሪው ማብራሪያ የሚሊሻና ሰላም አስከባሪ ሃይላችን ህግና ስርዓት በማስከበር ብቻ አይደለም ፣ በወረዳችን በኢኮኖሚው እና በማህበራዊ ልማት ዘርፎችም እያደረገው ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው፡፡ ሚሊሻው ራሱን ለልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች አርዓያ በመሆን ሌሎችን በማበረታታትና በማነሳሳት የመንግስት ተልዕኮዎች በስኬት እንዲፈፀሙ በማድረግም የአንበሳውን ድርሻ የሚወጣው ሚሊሻ መሆኑን አመላክተዋል ፡፡

የደቡብ ጎንደር ዞን ሚሊሻ መምሪያ ኃላፊ አቶ በላይ አያሌው በበኩላቸው ይህ ክብረ በዓል ከሌሎች ክብረ በዓላት ለየት የሚያደርገው ሚሊሻው ለአገርና ለወገን ክብር ሲል ክብር ሂዎቱን መስዕዋት እያደረገ የመጣ መሆኑን ለየት እንደሚያደርገው አመላክተዋል።

የፎገራ ወረዳና  ወረታ ከተማ አስተዳደር  30ኛ አመት  የሚሊሻ ፅህፈት ቤት የምስረታ በዓል የደቡብ ጎንደር ዞን፤የፎገራ ወረዳና የወረታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጥሪ የተ...
24/04/2026

የፎገራ ወረዳና ወረታ ከተማ አስተዳደር 30ኛ አመት የሚሊሻ ፅህፈት ቤት የምስረታ በዓል የደቡብ ጎንደር ዞን፤የፎገራ ወረዳና የወረታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት የተከበረ ሲሆን የላቀ አበርክቶ ላደረጉ አካላት የሽልማትና የእውቅና መርሃ ግብር ተካሂዷል።

Address

Wereta

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fogera Woreda Peace & Security Office /ፎገራ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share