Wereta City Youth and Sport Office

Wereta City  Youth and Sport Office sport

በወረታ ከተማ ጥራቱን የጠበቀና በደቡብ ጎንደር ዞን የመጀመሪያው ዘመናዊ የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል ተገንብቶ በቅርቡ  ለወጣቶች ክፍት እንደሚሆን ተገለጸ።በአገራች ኢትዮጵያ ብሎም በክልላች በተ...
03/06/2023

በወረታ ከተማ ጥራቱን የጠበቀና በደቡብ ጎንደር ዞን የመጀመሪያው ዘመናዊ የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል ተገንብቶ በቅርቡ ለወጣቶች ክፍት እንደሚሆን ተገለጸ።

በአገራች ኢትዮጵያ ብሎም በክልላች በተለያዩ ቦታዎች ሁለገብ የወጣቶች መዝናኛ ማዕከላት በስፋት ባለመገንባታቸውና ባለመኖራቸው የተነሳ የነገ አገር ተረካቢ ትውልዶችና ልማታዊ ወጣቶች በተለያዩ አልባሌና አላስፈላጊ ቦታዎች ጊዜያቸውን በማሳለፍ ለአዕምሯዊና ስነልቦናዊ ችግር እየተጋለጡ በተለያዩ ጊዚያት ወጣቶች ለሰላም ዘብ ከመቆም ወደ የጥፋት ኃይልነት የማዘንበል አዝማሚያ ከልማታዊነት ይልቅ ወደ አፍራሽ ሃይልነት ተለውጠው በወጣትነታቸው ዘመን ለአገራቸው ማድረግ የሚገባቸውንና አገራዊ ግዴታቸውን ሳይወጡ መቆየታቸው የማይዘነጋና የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው።

በወረታ ከተማም በመልካም ስነምግባር የታነጹ በስነልቦና የተገነቡና በአዕምሮ የበለጸጉ ወጣቶችን ለማፍራት መንግስት በሚያደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ የወረታ ከተማ አስተዳደር የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የወረታ ከተማ ሁለገብ የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ በ5.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በማድረግ ሁለገብ የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል በመገንባት ና በቅርቡ ለወጣቶች ክፍት እንደሚሆን የወረታ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አሳምኗል አየሁ ገልጸዋል።

የመዝናኛ ማዕከሉም በደቡብ ጎንደር ዞን ውስጥ የመጀመሪያው ጥራቱን የጠበቀ ውብ ፣ማራኪ ና ዘመናዊ ሁለገብ የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል መሆኑንና በውስጡም የተለያዩ በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የሚደረግባቸው ጅምናዜሞች፣ የፑል አገልግሎት፣ ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ ቤተ መፅሃት፣ መፀዳጃ ቤት፣ ጥራቱን የጠበቀ የካፌ አገልግሎት፣ ሌሎችንም አገልሎቶች የሚሰጥ ሁለገብ የመዝናኛ ማዕከል መሆኑንና ግንባታውም 100% የተጠናቀቀ መሆኑን ስራ ዋና አስኪያጁ ጨምረው አብራርተዋል።

የወረታ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ብርሃኑ ያዜ በበኩላቸዉ ይህን ዘመናዊ ሁለገብ የመዝናኛ ማዕከል ለመገንባት ከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ በጀት በመመደብና ማዕከሉ እንዲገነባ የሆነበት ምክንያት ከቅርብ ጊዜ በፊት ለከተማችን ወጣቶች መዝናኛ የሚሆን ካፌና የተለያዩ ስፖርታዊ ና የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ማድረጊያና አነስተኛ ቤተመጽሃፍት ያለው ማዕከል ተገንብቶ እንደነበር ተናግረዋል።

ይሁን እንጅ ከተማ አስተዳደሩ ለማዕከሉ አስፈላጊውን ቁሳቁስ አሟልቶ ወጣቶቹ በማዕከሉ ከሚዝናኑ ወጣቶች የገቢ በማግኘት እራሳቸውን ተጠቃሚ የሚያደርጉበትአስረድተዋል። የስራ ዕድል የፈጠረላቸው ቢሆንም በወቅቱ ወጣቶቹ ሰበብ አስባብ በመፍጠር እራሳቸውን እንኳ በፋይናንስ ማስተዳደር ባለመቻላቸው ማዕከሉ የሚጠበቅበትን አገልግሎት ለከተማው ወጣቶች ሳይሰጥ ቆይቷል ሲሉ ከንቲባው

በመሆም በከተማችን በስነምግባር የታነጸ ፣በስነልቦናው ጠንካራና አምራች ልማታዊ ወጣት ለመፍጠር ያስችል ዘንድ በከተማችን ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል ገንብተን ለወጣቶች አገልግሎት እንዲውልና ወጣቶች እየተዝናኑ እውቀት እንዲጨብጡበት ሁኔታዎች ተመቻችተዋል ብለዋል።

የመረጃ ምንጭ፦ የወረታ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቡድን

በሳምንቱ መጨረሻ ቅዳሜና እሁድ  የተጀመረው የወረታ ከተማ አስተዳደር  የመ/ቤቶች እና የግል ድርጅቶች የእግር ኳስ ውድድር ፕሮግራም መጋቢት 20/2015 ዓ.ም
29/03/2023

በሳምንቱ መጨረሻ ቅዳሜና እሁድ የተጀመረው የወረታ ከተማ አስተዳደር የመ/ቤቶች እና የግል ድርጅቶች የእግር ኳስ ውድድር ፕሮግራም

መጋቢት 20/2015 ዓ.ም

በሳምንቱ መጨረሻ ቅዳሜና እሁድ  የተጀመረው የወረታ ከተማ አስተዳደር  የመ/ቤቶች እና የግል ድርጅቶች የእግር ኳስ ውድድር ውጤቶች             ፨ ቅዳሜ   ወ/2ኛ/ደ/ት/ቤት  2   ...
28/03/2023

በሳምንቱ መጨረሻ ቅዳሜና እሁድ የተጀመረው የወረታ ከተማ አስተዳደር የመ/ቤቶች እና የግል ድርጅቶች የእግር ኳስ ውድድር ውጤቶች

፨ ቅዳሜ
ወ/2ኛ/ደ/ት/ቤት 2 ለ 1 ፎገራ 2ኛ/ደ/ት/ቤት

ወረታ ግብርና ኮሌጅና ቴ/ሙ ኮሌጅ 1 ለ 5 ቤቶች ል/ኮ ፑል

፨ እሁድ

ወረታ ደረቅ ወደብ ጉምሩክ መቅረጫ 2 ለ 0 ባንኮች

ነጋዴዎች 4 ለ 1 ከንቲባ ፑል

በማሸነፍ ውድድሩ ተጠናቋል

መጋቢት 19/2015 ዓ.ም

የ2015 ዓ.ም የወረታ ከተማ አስተዳደር የመስሪያ ቤቶች ስፖርት  ቅድመ ውድድር ውይይት ተካሄደ።የወረታ ከተማ አስተዳደር  ባህል ፣ ቱሪዝም ፣ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሰፋ መን...
21/03/2023

የ2015 ዓ.ም የወረታ ከተማ አስተዳደር የመስሪያ ቤቶች ስፖርት ቅድመ ውድድር ውይይት ተካሄደ።

የወረታ ከተማ አስተዳደር ባህል ፣ ቱሪዝም ፣ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሰፋ መንጌ በመሩት ውይይት የዘንድሮውን የማስ ስፖርት ውድድር በስፖርታዊ ጨዋነት በመምራት ስፖርትን ለማህበራዊ ግንኙነት ማጠናከሪያ ልናውለው ይገባል ብለዋል።

በዳኝነት ዙሪያ ሁሉም ዳኞች የእግር ኳስ ህጎችን መሰረት ባደረገ መልኩ ውድድሩን መምራት እንደሚገባ እንዲሁም ዳኞችና ኮሚቴዎች ጋር በተገቢው መልኩ በመናበብ ውድድሩን ጀምሮ ማጠናቀቅ ይገባል በማለት አሳስበዋል።

ተሳታፊ የቡድን ወኪሎች ፣ ዳኞችና ኮሚቴዎች በበኩላቸው የሚወሰኑ ውሳኔዎች በተገቢው መልኩ ተፈፃሚ ማድረግ እና ውጤታማ ስፖርተኛ ለማፍራት ሁላችንም ማገዝና መረባረብ አለብን ብለዋል።

በመጨረሻም ተቋሙ ለውድድሩ አስፈላጊ የሆኑ ጉዳዬች ከኮሚቴዎች ጋር በጋራ በመሆን ስራዎችን ለመስራት በመግባባት የ2015 ዓ.ም የመስሪያ ቤቶች ስፖርት ውድድር በመጭው ቅዳሜ 16/07/2015 ዓ.ም ለመጀመር ስምምነት ላይ በመድረስ የቅድመ ውድድሩ ውይይት ተጠናቋል።

መጋቢት 12/2015 ዓ.ም
ወረታ

17/03/2023

መጋቢት 08/2015 ዓ/ም

ለደ/ጎ/ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ
ደ/ታቦር

ጉዳዩ፦ የዲስፕሊን ቅጣት ስለመስጠት
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው 8ኛው የመላው ደ/ጎንደር ዘመናዊ ስፖርት ውድድር በመካነ እየሱስ ከተማ አዘጋጅነት ከጥር 27- የካቲት 05/2015 ዓ/ም ተካሂዷል። በዚህም ውድድር ከተማችን በ3 የስፖርት አይነት ተሳትፎ አድርጓል። ሆኖም በዚህ ውድድር አዘጋጁ ከተማ የአልጋ እጥረት ስለገጠመው ሌላ አማራጮችን በመጠቀም በመካነ እየሱስ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ በሚገኘው የደ/ታቦር ዩንቨርስቲ ባስገነባው የጤና ተማሪዎች አፓረንት መውጫ ዶርምተሪ ውስጥ የወረታ ከተማና ሌሎች ወረዳዎች የለምንም ክፍያ በነፃ እንድናርፍ ተደርጓል። ነገር ግን በእግር ኳስ ስፖርት ከተሳተፉት ስፖርተኞቻችን መካከል ለ6 ሲተኙበት ከነበረው ክላስ ውስጥ የአንደኛውን አልጋ ፎም ፍርናሽ በመቅደድ ያልተገባ ተግባር በመፈፀም የወከሉትን ህዝብ በማሰደብ፣ ከተማው ተጨማሪ ወጭ እንዲያወጣ በማድረግ፤ የቡድን መሪውን፣ የቴ/ባሙያውን፣ ኮሜቴውን፣ አሰልጣኙን እና አጠቃላይ የቡድኑን አባላት በመናቅ ይህን ተግባር በፈፀሙት ተጫዋቾች ላይ የቡድን መሪ፣ አሰልጣኙ፣ ኮሚቴውና ቴ/አማካሪው በጋራ በቀን 16/06/2015 ዓ/ም በመሰብሰብ የዲስፕሊን የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል። በዚህም መሰረት
1. ካስዬ አናግሬ ፍርናሽ በመቅደዱ በ2015 ዓ/ም በሚካሔዱ በማንኛውም የስፖርት አይነት ከተጫዋችነት፣ ከአሰልጣኝነት፣ ከቡድን መሪነትና ከወጌሻነት ታግዷል።
2. ከድር ዑስማን፣ አንዋር ይሃ፣ አብዱሰመድ ሙሃመድ፣ ያሬድ ጋሻውና በላቸው እሸቴ ላይ ደግሞ ፍርናሽ ሲቀደድ በቸልተኝነት በማየትና ተባባሪ በመሆናቸው ከባድ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል።

ቅጅ//
• ለወ/ከ/አስ/ባ/ቱ/ወ/ስ/ጽ/ቤት
• በከተማችን ለሚገኙ ሁሉም ቡድኖች
ወረታ፣

24/12/2022
ወረታ ከተማን ወክለው እየተሳተፉ የሚገኙት የባህል ስፖርት ልዑክ ቡድን ፦1.  12 ጉድጓድ ገበጣ በሴቶች እና2.  18 ጉድጓድ  ገበጣ ወንዶች  ለዋንጫ ፍፃሜ ውድድር ደርሰዋል ለልዑክ ቡድና...
22/12/2022

ወረታ ከተማን ወክለው እየተሳተፉ የሚገኙት የባህል ስፖርት ልዑክ ቡድን ፦
1. 12 ጉድጓድ ገበጣ በሴቶች እና
2. 18 ጉድጓድ ገበጣ ወንዶች ለዋንጫ ፍፃሜ ውድድር ደርሰዋል ለልዑክ ቡድናችን መልካም እድል።

በ19ኛው የደቡብ ጎንደር ዞን ባህል ስፖርት እና በ6ኛው የደቡብ ጎንደር ዞን የባህል ፌስቲባል   ወረዳ አቀፍ ውድድር ከተማችን ወክለው ለሚሳተፉ የስፖርት ልዑክ ቡድን አሸኛኘት ተደረገለት።1...
16/12/2022

በ19ኛው የደቡብ ጎንደር ዞን ባህል ስፖርት እና በ6ኛው የደቡብ ጎንደር ዞን የባህል ፌስቲባል ወረዳ አቀፍ ውድድር ከተማችን ወክለው ለሚሳተፉ የስፖርት ልዑክ ቡድን አሸኛኘት ተደረገለት።

19ኛው የደቡብ ጎንደር ዞን ባህል ስፖርት እና 6ኛው የደቡብ ጎንደር ዞን የባህል ፌስቲባል ወረዳ አቀፍ ውድድር ከታህሳስ 8/2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 16/2015 ዓ.ም በስማዳ ወረዳ አዘጋጅነት በወገዳ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን በውድድሩ ከተማችን ወክለው ለሚሳተፉ ልዑካን የወ/ከ/አስ/ባ/ቱ/ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አሰፋ መንጌ በተገኙበት አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል፡፡

የጽ/ቤት ሀላፊው እንደተናገሩት ከተማችን ወክላችሁ የምትሳተፉ ስፖርተኞች ስነ ምግባር በተሞላበት መልኩ ስፖርታዊ ጨዋነት በተላበሰ በዘርፉ አሸናፊ በመሆን የከተማችንን ገፅታ በማስተዋወቅ በኩል የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ በማለት መልዕክታቸውን አስተላላፈዋል፡፡

ከተማ አስተዳደሩ የሚሳተፍባቸው የውድድር መድረኮች
1.ቀስት ወንድ
2.ቀስት ወንድና ሴት/ድብልቅ/
3. ኮርቦ ወንድ
4. ገበጣ ባለ 12 ጉድጓድ ወንድ
5. ገበጣ ባለ 12 ጉድጓድ ሴት
6 ገበጣ ባለ 18 ጉድጓድ ወንድ
7. ገበጣ ባለ 18 ጉድጓድ ሴት
8. ባህል ፌስቲባል

ታህሳስ 7/2015 ዓ.ም
የወ/ከ/አስ/ባ/ቱ/ወ/ስፖርት ጽ/ቤት
ወረታ

Address

Wereta

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wereta City Youth and Sport Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Wereta City Youth and Sport Office:

Share