Woreillu culture & tourism office

Woreillu culture & tourism office Viva Menelike ፔጃችንን ላይክ በማድረግ፡- የወረዳዉን የቱሪስት መሰህቦች፣ ባህላዊ ትዉፊቶች፣ ክንዋኔዎችና ሃገር በቀል እዉቀቶች እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎችን በፍጥነት እናደርሶዎታለን!! ከእናንተ እሚጠበቀዉ ፔጁን ጠቅ...ማድረግ ብቻ ነዉ

ለመላው የወረኢሉ አካባቢ የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን በሙሉ በኪነ-ጥበብ ውድድር ለመሳተፍ የምትፈልጉ  በዶሉ አካባቢ ለምትገኙ ዶሉ ንዑስ ማዘጋጃ፣ካቤ አካባቢ ለምትገኙ አንዋር ይመር (ስ.ቁ. ፡-...
17/03/2023

ለመላው የወረኢሉ አካባቢ የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን በሙሉ
በኪነ-ጥበብ ውድድር ለመሳተፍ የምትፈልጉ በዶሉ አካባቢ ለምትገኙ ዶሉ ንዑስ ማዘጋጃ፣ካቤ አካባቢ ለምትገኙ አንዋር ይመር (ስ.ቁ. ፡- 0989871282)፣ሰኞ ገበያ አካባቢ ለምትገኙ ሰኞ ገበያ ንዑስ ማዘጋጃ፣ወረኢሉ ከተማ ለምትገኙ ወረኢሉ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት በአካል በመገኘት እንዲሁም በአጠቃላይ በፌስቡክ ገፃችን መልዕክት መስጫ ላይ ሙሉ ስም ስልክ እና የምትወዳደሩበትን የኪነ-ጥበብ ዘርፍ እና ጸሁፍ በማስቀመጥ መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡

18/06/2022

“አማራ ባንክ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባንክ ነው”

ስራውን በይፋ ዛሬ ጀምሮል እንኳን ደስ አላችሁ አለን!!!!!
የአማራ ባንክ የ 72 ቅርንጫፎች ዝርዝር!
*******
የአዲስ አበባ ቅርንጫፎች
1. አዲሱ ገበያ
2. አድዋ ድልድይ
3. አራት ኪሎ
4. አያት አደባባይ
5. በቅሎ ቤት
6. ቦሌ 24
7. ቦሌ ቡልቡላ
8. ቦሌ መድሃኒዓለም
9. ቦሌ ሚካኤል
10. ኮሜርስ
11. ዱባይ ተራ
12. እህል በረንዳ
13. ፈረንሳይ ለጋሲዮን
14. ጎጃም በረንዳ
15. ጎተራ
16. ሃና ማርያም
17. ጀሞ
18. ላፍቶ
19. ለም ሆቴል
20. ልደታ
21. ሳርቤት
22. ሸማ ተራ
23. ጦር ኃይሎች
24. ለገሀር (ዋና መስሪያ ቤት)
የባህርዳር ቅርንጫፎች
1. ባህርዳር
2. ደ/አዝማች በላይ ዘለቀ
3. ደንገል
4. ፋሲሎ
5. ግዮን
6. ሸምብጥ
7. ዘንባባ
የጎንደር ቅርንጫፎች
1.ጎንደር
2.አባ ሳሙኤል
3.አራዳ
4.ማራኪ
5.አፄ ፋሲለደስ
የደሴ ቅርንጫፎች
1.ደሴ
2.ጦሳ
የደብረታቦር ቅርንጫፎች
1.ደብረታቦር
2.ጉና
የደብማርቆስ ቅርንጫፎች
1.ደብረማርቆስ
2.መንቆረር
የሌሎች ከተሞች ቅርንጫፎች
1. ገንዳ ውሃ
2. ሸዋ ሮቢት
3. ሆሳህና
4. ቢሾፍቱ
5. ይርጋለም
6. ዳባት
7. ሀይቅ
8. ዳንግላ
9. ቢቸና
10. ዳንሻ
11. ወሊሶ
12. ደብረ ብርሃን
13. ፍኖተ ሰላም
14. አረርቲ
15. ኮምቦልቻ
16. ሐዋሳ
17. ሎጊያ
18. ከሚሴ
19. መካነሰላም
20. ሞጣ
21. ማክሰኝት
22. ደብረወርቅ
23. መራዊ
24. ደጀን
25. ሰቆጣ
26. ወልድያ
27. ወልቂጤ
28. ድሬዳዋ
29. አዳማ
30. እንጅባራ
****
ሰኔ 11፣ 2014 ዓ.ም
፩ ሚሊዮን ደብተር፣ በ፩ ጀንበር
አማራ ባንክ፣ ከባንክ ባሻገር!

በወ/ወ/ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ሰኔ11/2014 ዓ.ምስ.ቁ. 0331160051ታላቅ ታሪካዊና ሃይማኖታዊውን የባቄላ መስጅድ ይጎብኙ     የባቄላ መስጅድ በወረኢሉ ወረዳ ዉስጥ ከሚገኙ ጥንታዊና...
18/06/2022

በወ/ወ/ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
ሰኔ11/2014 ዓ.ም
ስ.ቁ. 0331160051
ታላቅ ታሪካዊና ሃይማኖታዊውን የባቄላ መስጅድ ይጎብኙ
የባቄላ መስጅድ በወረኢሉ ወረዳ ዉስጥ ከሚገኙ ጥንታዊና ታሪካዊ መስጅድ አንዱ ሲሆን መስጅዱ በዘመኑ በነበረው (Oromo expanation) ባቄላ መስጅድ ተብሎ እንደተሠየመ የሚነገር ሲሆን በአሁኑ ሰዓት መስጅደል ቀድም ተብሎ ተሰይሟል።
መስጅዱ በቀደምት የኢትዮጵያውያን የቤት አሰራር አይነት ጥበብ በድንጋይ ግንብ ሆኖ በክብ ቅርጽ የተሰራና የሳር ክዳን እንደነበረውና በቅርብ ጊዜ ወደ ቆርቆሮ ክዳን እንደተቀየረ አባቶች ይናገራሉ፡፡ የበርና የመስኮቱ እንጨቶች ከአልብኮ (ሳልመኔ) በመጣ ጽድ ተጠርበው በንጉስ ሚካኤል መሃንዲሶች በልዩ አጠራረቡ፣ በአስገራሚ ዉበትና ቅርጽ የተሰራ ነዉ ፡፡
መስጅዱ ከወረዳዉ በስተሰሜን እስከ ሰኞ ገበያ ከተገጓዙ በኋላ ሰኞን ወጣ ብለን ወደ ቀኝ በመታጠፍ 1፡30 ተጉዘን በ011 ቀበሌ የምናገኘዉ ቦታ ነዉ ፡፡ከአፈ ታሪክ እንዳገኘነዉ መረጃ ይህ ጥንታዊ መስጅድ የተመሰረተዉ በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግስት ሲሆን ቦታዉንም የመሰረቱት አባ ሸህ ማህሙድ ሰኢድ የሚባሉ አሁን ከቦታዉ ላይ የሚገኙት ቅድመ አያት ናቸዉ ፡፡እኝህ ሰዉየ አመጣጣቸዉ በሰሜን ወሎ ከሚገኘዉ ሰፊ ከተማ ወልድያን ወጣ ብለን የጁ ጓጉር ከሚባል ቦታ ተነስተዉ የመጡ ሲሆን ሰዉየዉ በማንኛዉም ቦታ /ለቁርአን ትምህርት/ የሚንቀሳቀሱ ስለነበር እዚህ ቦታ ላይ እንደመጡ የባቄላ ባላባቱ አብይ አብጡ የሚባለዉ አምስት /5/ ጋሻ ከግማሽ ከሁለት /2/ ማሳ መሬት ወቅፍ አድርግልሃለሁ እዚሁ ተቀመጥ ብለዉ ለምነዋቸዉ ተቀመጡ ቤትም ተሰራላቸዉ እዚሁ መኖር ሲጀምሩ አግብተዉ 6 ወንድ 1 ሴት ልጅ ወለዱ በዚሁ እንዳሉ ለትንሽ ጊዜ ያህል ከዚህ ለቀዉ ነጭ ሳር በሚባል አገር በአርጎባ ዉስጥ ሄደዉ አረፉ፡፡ ልጆቻቸዉ እዚሁ ስለነበሩ ዛዉያዉ ተሰርቶ ከ30 ሽህ የበለጠ ወርድ /ዱዓ /እያደረጉ የተጣላን በማስታረቅና ከመንግስቱ ንጉስ ሚካኤል ጋር በመወያየት እየተመካከሩ አጼ ምኒልክ ወረኢሉ በነበሩ ጊዜ ሽህ ማህሙዳ ሰዒድን አስጠርተዉ ነደድ በአሁኑ 04 ቀበሌ በሆነዉ ቦታ ላይ ተገናኝተዉ አብረዉ ዱዓ /ጸሎት /ያደረጉበት ጊዜ እንደ ነበር አባቶች ይናገራሉ፡፡ አጼ ሚኒሊክ ለሳቸዉ አምስት /5/ አጋስስ አቡጀዲና አምስት/5/ቡና ሃድያ/ስጦታ ልከዉላቸዋል ፡፡
ይህ መስጅድ በአሁን ሰዓት ቆርቆሮ ብቻ የተቀየረለት ሌላዉ ምንም ሳይነካ ያለ መስጅድ ነዉ፡፡ከመስጅድ ዉስጥ አሁን ያሉ አያት ጌታዉ ሸህ መሃመድ ኸየር ቁርዓን የሚቀሩበት ለየት ያለች ክፍል አለች፡፡ ይች ክፍል አሁን ሰው አይገባበትም የቁርዓን ማስቀመጫ ብቻ የሚጠቀሙባት ናት ብለው ያሉን በቦታው ላይ ያሉ የመስጅዱ ባለቤት ናቸው፡፡
በዚሁ ቦታ ሸህ ሙሀመድ ኽየር ከ30 ሺ በላይ ወርድ /ዚክር/ እያደረጉ የነበሩባት ቤት አሰራሩ በግንብና የሳር ክዳን የነበራት እንደሆነች ተረድተናል፡፡ እንግድህ መጀመሪያም ላይ ጠቀስ እንዳደረግነው ከንጉስ ሚካኤል ጋር እየተወያዩ ሲኖሩ የነበሩ ጌታው ሙሃመድ ኽየር በንጉስ ሚካኤል ዘመነ መንግስት መጨረሻ ላይ ህይወታቸው በዚሁ ሰፈር አለፈ፡፡ ህይወታቸው ከማለፉ በፊት ለህብረተሰቡ ሲያገለግሉ የነበሩበት ስራ ነበር ማለትም በአካባቢያቸው ሰው ሲጣላ የደም አስታራቂ ሆነው የቆዩ ሲሆን እናም ይህን ስራ ልጃቸው ሸህ ሙሃመድ አረብ ከበፊት የነበረን የእርሳቸውን ስራ የእርቅ ስነ-ስርዓት ከእሳቸው በመቀበል ማስቀጠል ችለዋል፡፡
በአካባቢ ያሉ ከ100 በላይ የሚሆኑ ደረሶችንም ማቅራት ጀመሩ፡፡ደረሶቹ ከየቦታው የመጡም ጭምር ናቸው፡፡
እነዚህ ለሃይማኖት ትምህርት /ለቁርዓን/ የመጡ ደረሶች አገልግሎት የሚያገኙት ከአካባቢው ህብረተሰብ ነው፡፡ እኝህ ሰውየ ኢማም አቅሪም ሆነው እያሉ ከ60 ሺ በላይ ወርድ/የዚክር/ስራ ይሰራሉ፡፡ሌሊቱን የማይተኙ ቀኑን በጾም ለአላህ/ለጌታቸው/በኢባዳ ላይ የሚያሳልፉ ሰው ናቸው፡፡እንደማንኛውም ሰው ንጉስ ሚካኤል ጋር ሲቀመጡ አብረው በጎን እየተቀመጡ ከመንግስት መንግስት ከትውልድ ትውልድ የታወቁ ሆነው የኖሩ ናቸው፡፡ በዚሁ ላይ እንዳሉ በ1957 ዓ/ም ሞቱ ፡፡ ከዚህ ስዓት ጀምሮ የሳቸውን ስራ ወንድማቸው ሸህ ሙሀመድ አሊ ተቀብለው ሲሰሩና ሲያስተዳድሩ ቆይተው ከብዙ ዓመታት በኋላ ሲሞቱ ልጃቸው ተቀብሎ ሲኖር እሱም በ1991 ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ከዚህ ዓ/ም ጀምሮ በፊት የነበሩ የሸህ ሙሀመድ አረብ ልጅ የሆነው ሸህ ሙሀመድ ሸሪፍ ስራውንም ባህሉንም ይዘው በቦታው ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ታሪካዊ ቦታ ከበፊት ጀምሮ በቀበሌውና በአካባቢው ህብረተሰብ እንድሁም ከወረዳው ውጭ ያሉ የህብረተሰብ ክፍል እንደሌሎች ክብረ በዓል በዓመት አንድ ጊዜ ጥር 30 መውሊድ ተብሎ ይከበራል፡፡ይህ መስጅድ በንጉስ ሚካኤል ዘመነ-መንግስት የተሰራ ሲሆን ቆርቆሮ ብቻ የተቀየረለት ሲሆን ሌላው ድሮ በነበረበት ያለ ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ አሁን እስካለበት ድረስ እንደተጠበቀና ጁምዓ ጁምዓና በማንኛውም ስዓት ሶላት የሚሰገድበት ነው፡፡
በጾም ወቅት ማታማታ ከ300 ሰው በላይ የሚሰግድ ሲሆን ከዚህ በላይ ሰው ሲበዛ ግቢው ውስጥ እንጂ መስጅድ ውስጥ አይበቃም ፡፡ በመስጅዱ ውስጥ ረጅም እድሜን ያስቆጠረ ቅዱስ ቁርዓን የገኛሉ የውጭ ሽፋኑ በብራና ያጌጠና በላዩም ላይ መስቀል ያለው ሆኖ ሲያዮት በእጅጉ ይገረማሉ።
በዚህ ታላቅ ታሪካዊ እና ሀይማኖታዊ ቦታ ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለው ባህላዊ የእርቅ ስነ-ስርዓት ይካሄዳል፡፡
በታላቁ የባቄላ መስጅድ አካባቢ የሚደረው የእርቅ ስነ-ስርዓት
በወረዳው ውስጥም ይሁን ከወረዳው ውጭ ሁለት ተጣሊዎችን የደም እርቅ ሲደረግላቸው የገደለ ወገን አስታራቂ ይፈልጋል አስታራቂው አካል አንካሴና ሙስብሃ ይዘው ከሁለቱም ውጭ የሆነ ቦታ ዳስ ተሰርቶላቸው ቢያንስ እስከ 20 ቀን ድረስ የሞተበትም የገደለም ወገን እስከሚሰባሰብ እኝህ አስታራቂ አባት እዚያ ዳስ ውስጥ ይቀመጣሉ ከተሰባሰቡ በኋላ የአገር ሽማግሌና የቀበሌ ፖሊስ ሆነው አብረው ሸምግለው ያስታርቃሉ፡፡ሲታረቁ ግርዶሽ ይጋረዳል እርድ ይታረዳል፣ዳቦ ይጋገራል፣ የሞተበትም የገደለም ከግርዶሽ ውጭ ሆነው እጅ እጃቸው ላይ አንድ አይነት ሃይማኖት ከሆነ ስጋ የተለያየ ከሆነ ዳቦ ተሰጥተው ከገዳይ እጅ ላይ ቆርጠው ለሞተበት ከሞተበት እጅ ላይ ቆርጠው ለገዳይ በአፍ በአፋቸው አስታራቂዎችያጎርሷቸዋል፡፡አንካሴውና ሙስባሃውን አጋድመው ካሁን ጀምሮ በክፉ ላንፈላለግ ብላችሁ ማሉ ይባላሉ፡፡ ከማሉም በኋላ የተጋደመውን ይራመዳሉ፡፡የደበቁትም ነገር ካለ እውነቱን በማስወጣት በህብረተሰቡ ፊት ማህላውን ይምላሉ፡፡
ይህ ታሪካዊ/ሃይማኖታዊ/ቦታ ከሌሎች ለየት የሚያደርገው በቀበሊያቸውም ይሁን በሌላ ቀበሌ እየተዘዋወሩ የሚያደርጉት የደም እርቅ ስነ-ስርዓት ነው፡፡ ታላቁ የባቄላ መስጅድ ተአምራዊ ስራን ትውልድን አስተምረው ባህላዊ ዳኝነት በጋራ ይዳኙበት የነበረ የጋራ ስምምነት ህግ መፍለቂያና ከትውልድ ትውልድ እየተላለፈ አሁንም በዚሁ ስርዓት ላይ የሚገኝ ነው፡፡
እንግዲህ ስለዚህ ታላቅ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ቦታ ይህን ያክል ካልን ማየት ማመን ስለሆነ ሂዳችሁ እንድትጎበኙ እየጋበዝን የመስጅዱን የውሃ፣ የመብራትና የመንገድ ችግር የሚመለከተው አካል እንዲፈታላቸውና የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ መልዕክታችን ነው፡፡
ማጋራት አይርሱ!!!

በወረኢሉ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ዋስል የባህል ቡድን የተዘጋጀው 4 ኛ ዙር የውይይትና የሴሪሞኒ ፕሮግራምሰኔ 8/2014 ዓ.ም  አማተር ክበባትን ጨምሮ ወ 7    ሴ 8    ድ 15  ...
16/06/2022

በወረኢሉ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ዋስል የባህል ቡድን የተዘጋጀው 4 ኛ ዙር የውይይትና የሴሪሞኒ ፕሮግራም
ሰኔ 8/2014 ዓ.ም
አማተር ክበባትን ጨምሮ ወ 7 ሴ 8 ድ 15 አባላቶች ያሉት ዋስል የባህል ቡድን አሁን ላይ ቋሚ ተቀጣሪዎቹ 5 ብቻ ናቸው ባህል ቡድኑ በሰኔ 8/2014 ዓ.ም 4 ኛ ዙር ውይይቱን ያደረገ ሲሆን ባህል ቡድኑ ከጦርነት ማግስት በጣም ችግር ውስጥ ያለ ባህል ቡድን መሆኑ አባላቱ ገልፀዋል፡፡
የባህል ቡድኑ ያሉበት ችግሮች
የማቴሪያል ማለትም የሙዚቃ መሳሪያዎቹን ጨምሮ ሞንታርቦ አለመኖር (በጁንታው መወሰዱ)
የተሟላ የሰው ሀይል አለመኖር
የተሟላ አልባሳት አለመኖር (በጁንታው መወሰዱ)
የባህል ቡድን ደመወዝ አናሳ በመሆኑ አባላቱ ወደ ሌላ ወረዳ እየፈለሱ መሄዳቸው
ደጋፊ ጽ/ቤቱ ላይ በዘርፉ እነሱን የሚያግዝ ባለሙያ አለመኖሩ
ከወረዳው አስ/ም/ቤት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች፡- ከላይ የተዘረዘሩት ጥያቄዎች መልስ ሰጥቶ ባህል ቡድኑ እንዲጠናከር ቢደረግ በሚል ውይይቱን በአጭር አጠናቀናል፡፡
ትኩረት ለዋስል ባህል ቡድን!!!

ኬንያ አዲስ የሰራችውን ሀይዌይ በቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ስም ጠርታዋለች።
15/06/2022

ኬንያ አዲስ የሰራችውን ሀይዌይ በቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ስም ጠርታዋለች።

ጥንታዊቷንና ታሪካዊቷን ወረኢሉን ይጎብኙ
11/06/2022

ጥንታዊቷንና ታሪካዊቷን ወረኢሉን ይጎብኙ

02/06/2022
31/05/2022
ስለ ወይብላ ማርያም በጥቂቱ
29/05/2022

ስለ ወይብላ ማርያም በጥቂቱ

በደቡብ ወሎ ዞን ወረኢሉ ወረዳ የወይብላ ማሪያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት  ተከበረ።*************************************** በደቡብ ወሎ ዞን ወረኢሉ ወረዳ የወይብ...
29/05/2022

በደቡብ ወሎ ዞን ወረኢሉ ወረዳ የወይብላ ማሪያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ።
***************************************
በደቡብ ወሎ ዞን ወረኢሉ ወረዳ የወይብላ ማሪያም ዓመታዊ ክብረ በዓል የሐይማኖት አባቶችና ምዕመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

ታሪካዊ ቤቶች Vs የቱሪዝም መስህብእነዚህ ድንቅ ታሪካዊ ቤቶች አስተውሎ ለተመለከታቸው የእምዬ ወረኢሉን እድሜ ጠገብነት፣ ታሪካዊ ምድር ምስክር ናቸው። እኒህ ድንቅ ቤቶች በብዛት በንጉስ ምኒ...
15/03/2022

ታሪካዊ ቤቶች Vs የቱሪዝም መስህብ

እነዚህ ድንቅ ታሪካዊ ቤቶች አስተውሎ ለተመለከታቸው የእምዬ ወረኢሉን እድሜ ጠገብነት፣ ታሪካዊ ምድር ምስክር ናቸው። እኒህ ድንቅ ቤቶች በብዛት በንጉስ ምኒልክ ቤተመንግስት ዙሪያ የሚገኙ ናቸው። በላይኛው ከቄራው አደባባይ እስከ ጊዮርጊስ በር አካባቢ ድረስ ያለው የጥርጊያ መስመር በላይ እስከ ቤተመንግስቱ ድረስ ባለው በርካታ ታሪካዊ ቤቶች ይገኛሉ። ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ እነዚሁ ጥንታዊ ቤቶች እየፈረሱ በአዲስ መልክ እየተተኩ ነው። በቱሪዝም የበለፀጉ አገራት እንደነዚህ ያሉ ታሪካዊ ቤቶች ተከልለው፣ በደንብ ተውበውና አምረው በጎብኝዎች ይጨናነቃሉ። በእኛ ሀገር ግን ብዙም አልተጠቀምንበትም በአንፃሩ እንደ ሐረር፣ ድሬዳዋ፣ አ/አ እና ጎንደር ያሉ አካባቢዎችን ብንወስድ የተለዬ ትኩረትና እንክብካቤ አላቸው። በወረኢሉም የከተማውን ማስተር ፕላን ልማት ሲተገበር እነዚህን ውብ ታሪካዊ ቤቶች ታሳቢ ያደረገ ቢሆንና ይህን ማድረግ ቢቻል ከሌሎች የተፈጥሮ፣ ቱባ ባህሎች፣የእምነት ቦታዎች፣አድዋ ሁነቶችና መሰል በርካታ ሐብቶች ጋር ተደምሮ ወረኢሉን የተሻለ የቱሪስት መንደር ማድረግ ይቻላል።

Address

Woreilu
Were Ilu

Telephone

+251331160051

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woreillu culture & tourism office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Woreillu culture & tourism office:

Share