Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

  • Home
  • Ethiopia
  • Werabe
  • Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ  መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። ይህ ፔጅ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር የ2018 በጀት አመት የእስካሁን አፈጻጸምና የቀሪ ቀናት የትኩረት መስኮች ላይ የውይይት መድረክ ማካሄድ ጀምሯል።‎‎ቃዋቆቶ፣ ሰኔ 3/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን...
10/06/2026

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር የ2018 በጀት አመት የእስካሁን አፈጻጸምና የቀሪ ቀናት የትኩረት መስኮች ላይ የውይይት መድረክ ማካሄድ ጀምሯል።

‎ቃዋቆቶ፣ ሰኔ 3/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)

‎በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ዝርዝር አፈጻጸምንና የቀሪ ቀናት የትኩረት መስኮች ላይ የወረዳው አመራርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የግምገማና የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

‎በውይንት መድረኩ ላይ የጽ/ቤት ሀላፊዎች የእስካሁን አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ሲሆን የውይይት መድረኩን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱልዋሪስ ጀማል የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክብርት መህዲያ ሀሰን የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ዋና ሀላፊ አቶ ሙዘይን መሀመድ በጋራ እየመሩት ይገኛል።

‎በመድረኩ ላይ የወረዳው አስተባባሪ አባላት፣ የክልል ደጋፊ አመራሮች፣የወረዳው አመራሮች ተሳትፈዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘትከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ

‎በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338

‎በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/

‎በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk

‎በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication

‎በቲክቶክ
http://www.tiktok.com/

‎ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/Alichocomm25.

በወረዳው "8ኛ እና 6ኛ ክፍል ክልላዊ  ፈተና አሰጣጥን በተመለከተ ለባለድርሻ አካላት  ኦረንቴሽን ተሰጠቃዋቆቶ ሰኔ 2/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ትምህርት ...
09/06/2026

በወረዳው "8ኛ እና 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አሰጣጥን በተመለከተ ለባለድርሻ አካላት ኦረንቴሽን ተሰጠ

ቃዋቆቶ ሰኔ 2/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ትምህርት ቤቶች በቀጣይ ለሚሰጠው ለ8ኛ እና 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በተመለከተ ለሚመለከታቸው ለትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች ኦረንቴሽን ሰጥቷል።

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ካሚል ፈረጃ እንዳሉት እንደ ሀገር የትምህርት ስብራትን ለመጠገን ከተወሰዱ የእርምት እርምጃዎች አንዱና ዋነኛው የምዘና ሥርዓትን ማስተካከል ስለሆነ ፈተናው በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቅ እንዳለበትና መምህራን በዲስፕሊን በተሞላበት መልኩና በውጤት የታጀበ ስራ መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

ክልላዊ ፈተናው ከመስከረም እስከ ሰኔ የተሰራውን ስራ የሚመዘንበት እንደሚሆን ያነሱት ሀላፊው ተማሪዎችን ከኩረጃ የፀዳ ፈተና በመስጠት ሁሉም የተሰጠውን ሀላፊነት ወስዶ መተግበር እንደሚገባ በማንሳት በቀሪ ጊዜያት ተማሪዎችን በስነ-ልቦና ማዘጋጀት ይገባል ብለዋል ።

በ18 የፈተና ጣቢያዎች በሚሰጠው የ6ኛ ክፍል ፈተና 2576 ተማሪዎች ፈተናውን ከሰኔ 8-9/2018 የሚወስዱ ሲሆን የ8ኛ ክፍል ደግሞ በ17 የፈተና ጣቢያዎች 2703 ተማሪዎች ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 11-12/2018 እንደሚወስዱ ተገልጿል።

በኦሬንቴሽን አሰጣጡ ላይ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ካሚል ፈረጃ፣ ምክትላቸው አቶ መሀመድ ሱልጣን፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ ርዕሰ መምህራኖችና የጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አካላት ተሳትፈዋል።

አንጋፋው የጊንዶ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር  በወሻኖ 2 ( ቡርደና) እግር ኳስ ቡድን አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡ቃዋቆቶ ሰኔ 2/2018 አልቾ ኮሙኒኬሽን4ኛው ዙር የጊንዶ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር...
09/06/2026

አንጋፋው የጊንዶ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር በወሻኖ 2 ( ቡርደና) እግር ኳስ ቡድን አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡

ቃዋቆቶ ሰኔ 2/2018 አልቾ ኮሙኒኬሽን

4ኛው ዙር የጊንዶ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር በዛሬው እለት ፍጻሜውን ሲያገኝ ወሻኖ 2 ( ቡርደና) እሴትን 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል፡፡

የወሻኖ 2 (ቡርደና ) ለዋንጫ ያበቃች ብቸኛ ጎል ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ኢዘዲን (ኢዜ) ከመረብ አሳርፏል፡፡

በፍጻሜው ውድድር ላይ መልእክት ያስተላለፉት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ምክር ቤት የህግ እና አስተዳደር ዘርፍ ሃላፊ የተከበሩ አቶ ነስሬ ኑሪ ውድድሩ ዋና አላማው የጊንዶ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስታንዳርድን ለማሻሻል ያለመ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ውድድሩ ስፖርታዊ ጨዋነትን በተላበሰ መልእኩ እንዲካሄድ እና ቀጣይነት እንዲኖረው ለውድድሩ የተዋቀሩ ኮሚቴዎች ሚናቸው ከፍተኛ እንደነበረም የተከበሩ አቶ ነስሬ ተናግረዋል፡፡

በመዝጊያ ፕሮግራሙ ከ1-3ኛ ለወጡ ቡድኖች የማለያ የሚዳሊያ የምስክር ወረቀት እና የዋንጫ ሽልማት ሲበረከትላቸው ለኮሚቴዎች ለዳኞች እና ለውድድሩ መሳካት የራሳቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትም እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡

በውድድሩ 20 ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን ከዚህ ውድድርም ስድስት መቶ ሺህ ብር ለጊንዶ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ የተበረከተ ሲሆን ለግንባታ የሚያገለግል ብሎኬት ግዥ መፈጸሙ ታውቋል፡፡

በጊንዶ ካፕ የመዝጊያ ጨዋታ ላይ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ምክር ቤት ምክትል አፈ- ጉባኤ የተከበሩ አቶ ከድር ድሌ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ነጃ መሀመድ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ካሚል ፈረጃ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ሰማን ኸይረዲን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ጽ/ቤት እና የዩራፕ ዘርፍ ሃላፊው አቶ ጀማል ቢረዳ ጨምሮ ሌሎች የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

‎የተቀመጡ የግብርና ኢኒሼቲቮችን በአግባቡ ለተገበሩ መዋቅሮች ለእያንዳንዳቸው 100 ሺህ ብር ሽልማት ተበረከተ!‎‎​ቃዋቆቶ — ሰኔ 2/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)‎በስልጤ ዞን የተቀመጡ የግብ...
09/06/2026

‎የተቀመጡ የግብርና ኢኒሼቲቮችን በአግባቡ ለተገበሩ መዋቅሮች ለእያንዳንዳቸው 100 ሺህ ብር ሽልማት ተበረከተ!

‎​ቃዋቆቶ — ሰኔ 2/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)

‎በስልጤ ዞን የተቀመጡ የግብርና ኢኒሼቲቮችን ውጤታማ በሆነ መልኩ በመተግበር ላቅ ያለ አፈጻጸም ላሳዩ መዋቅሮች፣ ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ ሽልማት ተበረከተላቸው።

‎​ሽልማቱ የተበረከተው የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ “የተቀናጀ ግብርና ለቤተሰብ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል በስልጢ ወረዳ፣ ሰደ በረንጎ ቀበሌ ባካሄደው የመኸር ወቅት የተቀናጀ ግብርና የንቅናቄ መድረክ ላይ ነው።

‎​በዞኑ የተጀመሩ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግና ምርታማነትን ለማሳደግ በተቀመጡት የተለያዩ የግብርና ዘርፍ ኢኒሼቲቮች ላይ የተሻለ አፈጻጸም በማስመዝገብ ተሸላሚ የሆኑት መዋቅሮች የሚከተሉት ናቸው~
‎​ላንፉሮ ወረዳ፡ በፍራፍሬ ልማት ኢኒሼቲቭ፣
‎​አሊቾ ውሪሮ ወረዳ፡ በአትክልት ልማት ኢኒሼቲቭ፣
‎​ሳንኩራ ወረዳ፡ በቡና ልማት ኢኒሼቲቭ፣ እንዲሁም
‎​ምስራቅ ስልጢ እና ምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳዎች፡ በበሬ፣ በበግና ፍየል ማድለብና ማሞከት ኢኒሼቲቭ።

‎​የተዘጋጀውን የማበረታቻ ሽልማት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካን ጨምሮ ሌሎች የዞኑ አስተባባሪዎች የዞን፣የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ለተሸላሚዎቹ በክብር አስረክበዋል።

‎​ይህ አይነቱ የዕውቅናና የማበረታቻ መርሃ-ግብር በዞኑ የግብርናውን ዘርፍ ይበልጥ ለማነቃቃትና በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች መካከል ጤናማ የውድድር መንፈስ በመፍጠር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የቤተሰብ ብልጽግናን እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተመልክቷል።

@ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን

08/06/2026

ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የተላለፈ የጥንቃቄ መልእክት

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ከወረዳው ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡

በአለም ላይ በገዳይነቱ ቀዳሚ ሆኖ የተፈረጀው የትራፊክ አደጋ በወረደችን ባለፉት ቀናት ብቻ 15 ሰዎች ህይወት ቀጥፏዋል፡፡

ስለሆነም ማብቂያ የሌለዉ ችግርና ስጋት ሆኖ በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት አደጋውን በሂደት ለመቀነስ ፖሊስ የሚያደርገዉ ጥረት ስኬታማ ይሆን ዘንድ ህብረተሰቡ እራሱንና ቤተሰቡን ከትራፊክ አደጋ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ጽ/ቤቱ መልእክቱን ያስተላልፋል፡፡

በሰላም ወጥቶ መግባትን ታሳቢ አድርገዉ የተሻለ ህይወት ለመምራት በተሰማሩበት የሙያ መስክ ደፋ ቀና የሚሉ ለሀገርና ለህዝብ ጠቃሚ የሆኑ ዜጎች በትራፊክ አደጋ ተሰናክለዉ እንደወጡ ሳይመለሱ ቀርተዋል።

ከመሞት የተረፉት ደግሞ ለአካል ጎደሎነት ተዳርገዋል።

በመሆኑም ፖሊስ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የትራፊክ አደጋን በሂደት ለመቀነስ በትምህርት ቤቶች የተማሪ ክበባትን በማቋቋም ፣የህዝብ ስብሰባዎች ላይ ፣ በትላልቅ የገበያ ስፍራዎች በመገኘት በትራፊክ አደጋ ሳቢያ የሚደርሰዉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀዉስ ለአደጋዉ የሚያጋልጡ ሁኔታዎችና ሊወሰድ የሚገባ የጥንቃቄ እርምጃ ህብረተሰቡ በቂ እዉቀት ጨብጦ ተገቢዉ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን እየሰጠ ቢሆንም አደጋዉን በተፈለገዉ ልክ ለማስቆም አልተቻለም።

በመሆኑም አሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በለይ በለ ማሽከርከር የትራፊክ ምልክትና ማመልከቻዎችን አክብሮ ለእግረኛ ተጓዥና ለተሽከርካሪ ቅድሚያ ሰጥቶ ማሽከርከር አሽከርከሪዎች በህግ አግባብ ሰልጥነዉ ተምረዉ መንጀ ፍቀድ ይዘዉ ማሽከርከር እንዲሁም ከተፈቀደው በላይ አለመጫን ይኖርበቸዋል ከኋላና ከፊት ለሚንቀሳቀስ ተሽከርካሪ አስጠንቃቂ የሆነ መረጃ በመስጠትና የትራንስፖርት አዋጅና ደንብ አክብሮ በመንቀሳቀስ የተጣለባቸዉ ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል።

እግረኛ ተጓዦች የመንገዱን ግራ ጠርዝ ይዘዉ በመንቀሳቀስ መንገድ ለማቋረጥ የዜብራ ቅብን መጠቀም ግራ ቀኝ በማስተዋል መንገድ በማቋረጥ ጥንቃቄ በማድረግ ለህይወት ክብር መስጠት ያስፈልጋል የሚል መልእክት አስተላልፏል፡፡

@የትራፊክ አዳጋን በጋራ እንከላከል@

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት

ቃዋቆቶ ሰኔ 1/2018

የቂን ጣንዤ ደቦራር አንድን በመለያ ምት በማሸነፍ የ2018 የጣንዤ አረፋ ካፕ የእግር ኳስ አሸናፊ ሆነ፡፡ቃዋቆቶ ሰኔ 1 /2018 አልቾ ኮሙኒኬሽንየቂን ጣንዤ ደቦራር አንድን 5 ለ 4 በሆነ...
08/06/2026

የቂን ጣንዤ ደቦራር አንድን በመለያ ምት በማሸነፍ የ2018 የጣንዤ አረፋ ካፕ የእግር ኳስ አሸናፊ ሆነ፡፡

ቃዋቆቶ ሰኔ 1 /2018 አልቾ ኮሙኒኬሽን

የቂን ጣንዤ ደቦራር አንድን 5 ለ 4 በሆነ መለያ ምት በማሸነፍ የ2018 የጣንዤ አረፋ ካፕ የእግር ኳስ አሸናፊ ሆኗል፡፡

የሁለቱ ቡድኖች መደበኛ ጨዋታ ሁለት አቻ የተጠናቀቀ ሲሆን አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠ ፍጹም ቅጣት ምት የቂን ጣንዤ ደቦራር አንድን 5 ለ 4 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

በፍጻሜው ውድድር ላይ የተገኙት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል እና የስፖርት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ቶፊቅ በድሩ በተለያዩ ቀበሌዎች የሚካሄዱ የአረፋ ካፕ የእግር ኳስ ውድድሮችን ውጤታማ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራቶች እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የጣንዤ ማዘጋጃ ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱልማሊክ የከሲ በበኩላቸው ውድድሩ ለሁለተኛ ጊዜ መካሄዱን በመጥቀስ ውድድሩን ቀጣይነት እንዲኖረው እና ለትውልድ የሚተላለፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የውድድሩ ዋና ዓላማ የጣንዤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትን በትምህርት ቁሳቁስ ለማገዝ ያለመ ሲሆን ከ12 ተሳታፊ ቡድኖች 180 ሺህ ብር ለትምህርት ቤቱ ተበርክቷል ፡፡

በፍጻሜው ጨዋታ ለተሳታፊ ቡድኖች ለዳኞች እና ለውድድሩ መሳካት አሻራ ላሳረፉ አካላት የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ሲሆን ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ላጠናቀቀው ደቦራር አንድ የማለያ እና የምስክር ወረቀት ለኮከብ ጎል አስቆጣሪ እና ለእለቱ ኮከብ ተጨዋች የገንዘብ ሽልማት እንዲሁም ለውድድሩ አሸናፊ የዋንጫ እና የማለያ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል ፡፡

ጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ
በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338

በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/

በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk

በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication

በቲክቶክ https://vm.tiktok.com/ZM6BRmsNa/

ኢንስታግራም https://www.instagram.com/p/C1Za_1HtXH1/?igsh=YWYwM2I1ZDdmOQ==

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ወቅታዊ የግብርና ተግባራትን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አሰቀመጠቃዋቆቶ ​ሰኔ 1/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}​በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ...
08/06/2026

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ወቅታዊ የግብርና ተግባራትን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አሰቀመጠ

ቃዋቆቶ ​ሰኔ 1/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}

​በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ወቅታዊ የግብርና ሥራዎችና የተቋሙን የ11 ወር አፈጻጸም ከአጠቃላይ ባለሙያዎች ጋር በመገምገም ቀሪ ስራዎችን በአጠረ ጊዜ ለማካካስ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

መድረኩ በዋናነት እስካሁን በተከናወኑ ተግባራት ላይ የታዩ ክፍተቶችን በመለየት እና በሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ምክንያት ያልተከናወኑ ተግባራትን በቀጣይ ለማካካስ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ተመላክቷል።

​በመድረኩ በዋናነት ትኩረት የተደረገባቸው የግብርና ስራዎች የመኸር እርሻ ዝግጅት ፣ የፍራፍሬ፣ የቡናና የቅመማ ቅመም ልማት በክላስተር ለማሳካት በሙሉ አቅም ርብርብ ማድረግ ላይ ሲሆን በተመሳሳይ የመኖና የደን ችግኝ ተከላ የጉድጓድ ዝግጅት በማጠናቀቅ የአረንጓዴ ልማት አሻራ ዝግጅትን የማጠናከር ስራ ላይ ውይይት ተደርጓል ።

ሁሉንም የግብርና ፅ/ቤት ስራዎች በማቀናጀት በየዘርፉ የተቀመጡ የልማት ግቦችን ለማሳካት ተቋማዊ አሰራር ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶችን በማጠናከር በቀጣይ አንድ ወርና በክረምቱ የሚሰሩ የየዘርፉን ዝርዝር ግቦች ማለትም የመኸር ፣ የፍራፍሬ የቡናና ቅመማቅመም ኤንዲሁም የአረንጓዴ አሻራና የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ስራዎችን ከወዲሁ በትኩረት መምራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

​የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ማፋጠንና የእንስሳት ማድለብና ማሞከት እንዲሁም የመኖ ልማትና ተከላ ሥራዎችን በቁርጠኝነት መፈጸም እንደሚገባ ተገልጿል።

እንዲሁም የተቋም ሥራዎችን ይበልጥ ማጠናከርና የታዩ ጉድለቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማረም እንደሚገባም ተነስቷል።

መድረኩን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብራር አክመል፣ የጽ/ቤቱ የተፈጥሮ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ነስሬ ሱሌ እና የእንስሳት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሻሚል የሱፍ በጋራ መርተውታል።

ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር የተላለፈ የሀዘን መግለጫ‎*********‎በዛሬው እለት መነሻውን አልቾ ውሪሮ ወረዳ አድርጎ ወደ አዲስ አበባ 18 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ መለስተኛ የህዝብ ...
07/06/2026

ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር የተላለፈ የሀዘን መግለጫ
‎*********
‎በዛሬው እለት መነሻውን አልቾ ውሪሮ ወረዳ አድርጎ ወደ አዲስ አበባ 18 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ በምስራቅ ጉራጌ ዞን ኤደና አደባት ቀበሌ መንገድ ስቶ ገደል ውስጥ በመግባት በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።

‎በአደጋው እናቶች፣ህጻናት፣ወጣቶችና አባቶችን ጨምሮ 11 ሰዎች በአደጋው ህይወታቸው ያለፋ ሲሆን ሾፌሩን ጨምሮ ሶስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

‎ከመኪና አደጋው ሁለት ህጻናትን ጨምሮ አራት ሰዎች በሙሉ ጤንነት ሊተርፋ ችለዋል።የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር በአደጋው ህይወታቸው ያለፋ ሰዎችን ከቡታጀራ ሆስፒታል ወደ ወራቤ ኮምፔርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስክሬን በማምጣት ለቤተሰቦቹ የማስረከብ ስራ እየሰራ ሲሆን ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎችን በቡታጀራ ሆስፒታልና በወራቤ ሆስፒታል ህክምና እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል።

‎የወረዳው አስተዳደር በአደጋው ህይወታቸውን ባጡ ወገኖቻችን የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን ይመኛል።


‎ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም
‎ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር
‎ቃዋቆቶ

ግብርናን አዘምኖ ሀብት የሚፈጠርበት ኑሮ የሚደላደልበት ማድረግ እንደሚቻል በተጨባጭ ታይቷል:-አቶ ኡስማን ሱሩር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ለስልጤ ዞን የልማት ሰራተኞች እና የግ...
07/06/2026

ግብርናን አዘምኖ ሀብት የሚፈጠርበት ኑሮ የሚደላደልበት ማድረግ እንደሚቻል በተጨባጭ ታይቷል:-አቶ ኡስማን ሱሩር

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ለስልጤ ዞን የልማት ሰራተኞች እና የግብርና ባለድርሻ አካላት በወራቤ ዩንቨርሲቲ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

ስልጠናውን ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ግብርናን አዘምኖ ሀብት የሚፈጠርበት ኑሮ የሚደላደልበት ማድረግ እንደሚቻል ባለፉት የለውጥ አመታት በተሰሩት የግብርና ልማት ስራዎች በተጨባጭ መታየቱን ገልፀዋል ።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የተለያዩ የግብርና ማቀነባበሪያ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ስራ ማስገባት መቻሉንም አቶ ኡስማን ገልፀዋል።

በቀጣይም አርሶአደሮችን በህብረት ስራ ማህበራት በማደራጀት የተለያዩ የግብርና ምርቶችን የሚያቀናብሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ስራ ለማስገባት አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉንም ጠቁመዋል ።

እስከ ዛሬ በግብርናው ዘርፍ ለመጣው ተጨባጭ ውጤት የልማት ሰራተኛው ሚና የላቀ ቢሆንም ካለው ፀጋና እድል አንፃር ከተሳኩት የሚቀሩት በርካታ መሆናቸውንም አቶ ኡስማን ተናግረዋል ።

ቁልፉ ጉዳይ አመለካከትንና አስተሳሰብን መቀየር መሆኑን የገለፁት አቶ ኡስማን የዛሬው መድረክ ሁነኛ ዓላማም ቀጣይ በትንሽ መሬት ከፍ ያለ ምርት በሚያስገኙና አርሳ አደሩን ተጠቃሚ በሚያደርጉ አዳዲስ ኢኒሼቲቮችን ወደ ውጤት የመቀየር ስራ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

ጥራት ያለው ምርት እንዲመርት በማድረግ አርሶአደሮች ከራሳቸው ፍጆታ ተሻግረው ኤክስፖርት እንዲያደርጉ የልማት ሰራተኞች በትጋት መስራት ይጠበቅባቸዋል ሲሉም ተናግረዋል ።

ገጠሪቱ ኢትዮጵያ ዜጎች ተደላድለው የሚኖሩባት ትሆናለች መሆንም ጀምራለች ያሉት ኃላፊው ይህንን ለማሳካት ደግሞ የልማት ሰራተኞች ሀላፊነት ከፍ ያለ መሆኑንም ገልፀዋል።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ባስተላለፉት መልዕት የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየርና የሀገርን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የልማት ሰራተኞች ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

በትጋት በተሰራባቸው ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን የገለፁት አቶ ዘይኔ የተለያዩ አዳዲስ ኢኒሼቲቮችን በማውረድ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

የሀገራችንን ኢኮኖሚ ሁለንተናዊ ሽግግር ለማድረግና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የግብርናው ዘርፍ ሚና አይተኬ መሆኑን ገልፀው ስለሆነም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

ፀጋዎችን ወደ ሀብች ለመቀየር በተሰራው ስራም አበረታች ውጤት መመዝገቡን የገለፁት አቶ ዘይኔ ለዚህ ደግሞ የልማት ሰራተኞች አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ።

ከሰብል ልማት ተሻግሮ በፍራፍራ፣ በቅመማቅመም እና ሌሎች ቋሚ እና ጊዜያዊ ሰብሎች እየተሰሩ ያሉ ስራዎችም አበረታች ውጤት ማስገኘት መቻላቸውን ጠቁመዋል።

በቀጣይም ለአየር ሁኔታ የማይበገሩ የግብርና ልማት ስራዎችን ለማሳካት እየተደረገው በሚገኘው ጥረት የልማት ሰራተኞች በትጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

ባህርዛፍን በማንሳት አርሶአደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የግብርና ልማቶችን በመተካቱ ሂደት በአብዛኞቹ ቀበሌዎች ስኬታማ መሆናቸውን አንስተው ለዚህም የልማት ሰራተኞች ሚና ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

የስልጤ ህዝብ አምኖ በገባባቸው ዘርፎች ሁሌም ውጤታማ መሆኑን የገለፁት አቶ ዘይኔ በግብርና ልማት መበልፀግና የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻል የግንዛቤ ለውጥ እንዲመጣ የልማት ሰራተኞች ተግተው መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

የአርሶ አደሩን ብሎም የሀገራችንን የድህነት ታሪክ ለመቀየር በሚደረገው ሁለንተናዊ ጥረት የልማት ሰራተኞች መሪ ተዋናይ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

የዞኑ የኢኮኖሚ ምንጭ የገጠሩ ልማት መሆኑን በመግለፅ ይህንን ታሳቢ ያደረጉ በርካታ የአምራች ኢንዱስትሪ ዞኖች እየተዘጋጁ ነው ብለዋል።

ስልጤ ኤፍ ኤም

የ9ኛው የለምለምቻይ አረፋ ካፕ ውድድር ‎በ​ሀምቡቄ ሻምፒዮንነት ተጠናቋል!‎‎ቃዋቆቶ፣ግንቦት 29/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)‎‎በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዳምዘገር ክላስተር ላይ በደማቅ ሁኔታ ሲካ...
06/06/2026

የ9ኛው የለምለምቻይ አረፋ ካፕ ውድድር ‎በ​ሀምቡቄ ሻምፒዮንነት ተጠናቋል!

‎ቃዋቆቶ፣ግንቦት 29/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)

‎በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዳምዘገር ክላስተር ላይ በደማቅ ሁኔታ ሲካሄድ የሰነበተውና በርካታ ስፖርት ወዳዶችን ሲያነጋግር የቆየው የ9ኛው ዙር የለምለምቻይ ዓረፋ ካፕ ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታውን አድርጓል።

‎ከዒድ አል-አድሃ (ከዓረፋ በዓል) ማግስት ጀምሮ ለተከታታይ 8 ቀናት በዳምዘገር ሜዳ ሲካሄድ የቆየው ይህ ተወዳጅ ውድድር፥ በሀምቡቄ እና በአሊፍ መካከል በተደረገ እጅግ አጓጊ እና ተጠባቂ የፍፃሜ ጨዋታ ፍፃሜውን አግኝቷል።

‎​በጨወታውም ሀምቡቄ ጠንካራ ተቀናቃኙን አሊፍን 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት በማሸነፍ የዘንድሮውን የዓረፋ ካፕ በደስታና በክብር ማንሳት ችሏል።

‎​የዛሬውን ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታ ለመታደም ከዳምዘገር እና አካባቢው የተሰባሰቡ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በሜዳው ዙሪያ በመገኘት ለጨዋታው ልዩ ድምቀትና ግርማ ሞገስ ሰጥተውታል።

‎ይህን ታላቅ ውድድር ሙሉ በሙሉ በበጎ ፈቃደኝነት በማስተባበር፣ በመምራትና እዚህ የክብር ደረጃ ላይ እንዲደርስ በማድረግ ረገድ የሶስቱ ለምለም ወጣቶች ሚና እጅግ ከፍተኛ የነበረ ሲሆን፥ በተለይም የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት ለውድድሩ መሳካት ሌሊት ከቀን ያደረጉት ወደር የለሽ አስተዋፅኦ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ትልቅ አድናቆትን አትርፏል።

‎​🏅 የኮከቦች ሽልማት (Tournament Awards)
‎​ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በነበረው ደማቅ የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ የውድድሩ ኮከቦች ተለይተው ተሸልመዋል፡
‎​🥇 የውድድሩ ሻምፒዮን (Champions): ሀምቡቄ
‎​🥈 ሁለተኛ ደረጃ (Runners-up): አሊፍ
‎​🌟 የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች (Player of the Tournament): አብዲራሂም (ከአሊፍ) — በውድድሩ ላይ ባሳየው እጅግ አስደናቂ ብቃት።
‎​🧤 የውድድሩ ኮከብ ግብ ጠባቂ (Goalkeeper of the Tournament): ሪሃድ — መረቡን በብቃት በመጠበቅና ቡድኑን በመታደግ።
‎​👔 የውድድሩ ኮከብ አሰልጣኝ (Coach of the Tournament): አብዱልመጂድ — ታክቲካዊ ብስለቱንና መሪነቱን ላስመሰከረው።

‎​​ውድድሩ በሰላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ የላቀ አስተዋፅዖ ላበረከቱ አካላት ማለትም፤ ለወረዳው አስተዳደር፣ ለወረዳው የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት፣ ለቀበሌ አስተዳዳሪዎች፣ ለሜዳ ዝግጅት ባለሙያዎች፣ ለሚዲያ እና ለፀጥታ አካላት እንዲሁም ለሌሎችም አጋሮች በአዘጋጆቹ የእውቅናና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
‎​
‎መረጃውን ያደረሰን የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ ነው።
‎​👇


‎ #ሲሴ ስፖርት

Address

Silte
Werabe
KAWAKOTO

Opening Hours

Monday 07:00 - 19:00
Tuesday 07:00 - 19:00
Wednesday 07:00 - 19:00
Thursday 07:00 - 19:00
Friday 07:00 - 17:00
Saturday 07:00 - 17:00
Sunday 07:00 - 19:00

Telephone

+251924711807

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።:

Share