Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

  • Home
  • Ethiopia
  • Werabe
  • Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ  መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። ይህ ፔጅ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ቲጋገዞት የበጎ አድራጎት ማህበር ለ220 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ገለጸ፡፡ቃዋቆቶ መስከረም 5/2019 አልቾ ኮሙኒኬሽንበአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ ላይ የሚገኘው ቲጋገ...
15/09/2026

ቲጋገዞት የበጎ አድራጎት ማህበር ለ220 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ገለጸ፡፡

ቃዋቆቶ መስከረም 5/2019 አልቾ ኮሙኒኬሽን

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ ላይ የሚገኘው ቲጋገዞት የበጎ አድራጎት ማህበር ለ220 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል፡፡

ማህበሩ ከአባላቱ እና ከተለያዩ የበጎ አድራጊ ግለሰቦች በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ለ220 ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ተማሪዎች ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል፡፡

በድጋፉ ወቅት የተገኙት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን ቲጋገዞት የበጎ አድራጎት ማህበር ከተመሰረተ ጀምሮ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍን ጨምሮ አቅመ ደካማ ግለሰቦችን በተለያዩ ጊዜያት በማገዝ ረገድ ውጤታማ ስራዎች እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ማህበሩ እንደ ወረዳ ከመንግስት ጎን በመቆም በወረዳው አስተዳደር ተደራሽ ያልሆኑ ግለሰቦችን እያገዘ መሆኑን የተናገሩት ወ/ሮ መህድያ እየተረገ ላለው ድጋፍ በወረዳው አስተዳደር ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ተማሪዎች መማር እየፈለጉ በቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይርቁ ተደራሽ መሆን እንዳለበት በመጥቀስ ማህበሩ መጪው ትውልድ ላይ የሚሰራውን ስራም አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ሰማን ኸይረዲን በበኩላቸው በጎነት የህሌና ስራ መሆኑን በመጥቀስ ማህበሩ እያገዘ ያለው ተማሪዎችን ሳይሆን ማህበረሰብን መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተቋም ደረጃ ማህበሩን አስፈላጊ በሆነ መልኩ የማገዝና የማደራጀት ስራ እንደሚሰራም አቶ ሰማን አስታውቀዋል፡፡

የማህበሩ ሰብሳቢ ተወካይ የሆኑት አቶ ሳቢት መሀመድ ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ከትምህት እንዳይሰተጓጎሉ ገንዘብ በማሰባሰብ ሂደት ለተሳተፉ የማህበሩ አባላት እና በሂደቱ የተሳተፉ ግለሰቦችን ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በድጋፉ ወቅት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሰማን ኸይረዲን የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ካሚል ፈረጃ የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሳረት ረዲ የወጣቶች ክንፍ ሃላፊ ወ/ሪት መህድያ ኡስማንን ጨምሮ የማህበሩ ሰብሳቢዎች እና አባላቶች ተገኝተዋል፡፡

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የመረጃ አያያዙን ለማዘመንና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ /PMDMS/ የሶፍትዌር ሲስተም  ላይ ለፓርቲ ኮሚቴ አመራር ስልጠና ተሰጠ ቃዋቆቶ ...
14/09/2026

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የመረጃ አያያዙን ለማዘመንና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ /PMDMS/ የሶፍትዌር ሲስተም ላይ ለፓርቲ ኮሚቴ አመራር ስልጠና ተሰጠ

ቃዋቆቶ መስከረም 4/2019 አልቾ ኮሙኒኬሽን

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ ጽ/ቤት የመረጃ አያያዙን ለማዘመንና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ /PMDMS/ የሶፍትዌር ሲስተም ላይ ለፓርቲ ኮሚቴ አመራር ስልጠና ሰጥቷል ።

የፓርቲውን የመረጃ አያያዙን ለማዘመን፣ የአባላት መረጃ በየማህበራዊ መሰረቱ ለማደራጀት እንዲሁም አንድ እቅድ አንድ ሪፖርት ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም የዌብ ፖርታል ዲጂታል መረጃ በማዘመንና በማደራጀቱ ዙሪያ ለፓርቲው አመራሮች ስልጠና ተሰጥቷል።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙዘይን መሀመድ እንዳገለጹት፦ ሀገራችን የጀመረችውን የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በተግባር ለማሳየትና በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን መረጃን ማዘመንና ለፓርቲው የመረጃ አያያዙን በዘመናዊ መንገድ ለማደራጀት እና ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ PMDMS ሶፍትዌር ፣ የአባላት መረጃ እንዲሁም አዲሱ የዌብ ፖርታል ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑንና አስፈላጊውን መረጃ ማደራጀት ላይ የፓርቲ ኮሚቴ አመራር የጀመራቸውን የመረጃ ማዘመን ስራ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል ።

አክለውም የፓርቲ ኮሚቴ አመራሮች ከወትሮው በተለያ ሁኔታ በመቀነጃት ተቋሙ የሚፈልጋቸውን ማናቸውንም አይነት መረጃዎችን በአንድ ቋት ውስጥ አደራጅቶ በሲስተሙ በማስገባት ውጤታማ ለመሆንና አንድ እቅድ አንድ ሪፖርት ሲስተም/ ቴክኖሎጂ / ላይ በትኩረት መሰረት እንዳለበት አንስተው በቀጣይ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተቀምጠው መግባባት ተደርሶ መድረኩ ተጠናቋል ።

የሀዘን መግለጫበስልጤ ዞን በተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩት የቀድሞው የስልጤ ዞን ምክር ቤት  ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አህመዲን ጀማል በመኪና አደጋ ሕይወታ...
13/09/2026

የሀዘን መግለጫ

በስልጤ ዞን በተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩት የቀድሞው የስልጤ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አህመዲን ጀማል በመኪና አደጋ ሕይወታቸው አልፏል።

የቀድሞው የስልጤ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ አቶ አህመዲን ጀማል በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች በማገልገል ለስልጤ ዞን ልማትና እድገት የበኩላቸውን አሻራ ያኖሩ ታታሪ የህዝብ አገልጋይ ነበሩ።

የስልጤ ዞን አስተዳደር በአቶ አህመዲን ጀማል ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው የስልጤ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል።

የአልቾ ዉሪሮ ወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት የ2019 ትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ቅድመ ዝግጅት  ማጠናቀቁን ገለጸቃዋቆቶ መስከረም 2/2019{አልቾ ኮሙኒኬሽን}በስልጤ ዞን የአልቾ...
12/09/2026

የአልቾ ዉሪሮ ወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት የ2019 ትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለጸ

ቃዋቆቶ መስከረም 2/2019{አልቾ ኮሙኒኬሽን}

በስልጤ ዞን የአልቾ ዉሪሮ ወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት የ2019 ዓ.ም የእስካሁን የምዝገባ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት አጀማመር የንቅናቄ ዕቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሂዷል።

መድረኩን የመሩት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ሂደት ምቹ ማድረግና የተጓደሉ መምህራኖችን ሟሟላት እንደሚገባና የተመዘገቡ ተማሪዎች በአደረጃጀት ተቀስቅሰው ወደ ትምህርት ገበታ እንዲገቡና በወቅቱ ትምህርት እንዲጀምሩ የትምህርት አመራሩና የወረዳው ደጋፊ አመራሮች ከተማሪ ወላጆች ጋር በጋራ በኃላፊነት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

በ2018 በ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና የተመዘገበውን ውጤት ቀጣይነት እንዲኖረው ከወዲሁ መስራት እንደሚገባ ያነሱት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ለአዲሱ የትምህርት ዘመን አስፈላጊውው ግብዓት በማሟላት በተቀመጠው ቀን ትምህርት ማስጀመር እንደሚገባ ገልጸዋል።

የአልቾ ዉሪሮ ወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ አቶ ካሚል ፈረጃ በበኩላቸው የተመዘገቡ ተማሪዎች በሙሉ በተቀመጠው የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም በወረዳው በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ አንደኛ እና በመደበኛ ከ27 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለመቀበል መታቀዱን ጠቁመው እስካሁን የተመዘገበው ከ26ሺ በላይ የተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልፀዋል ።ከዚህ አኳያ የተመዘገቡ ተማሪዎች በሙሉ ከመስከረም 04/2019 ጀምሮ መደበኛ ትምህርት እንደሚጀመር ገልጸዋል።

በንቅናቄ መድረኩ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ፣ የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ አቶ ካሚል ፈረጃና ምክትላቸው አቶ መሀመድ ሱልጣን እና ርዕሰ መምህራኖችና ሱፐርቫይዘሮችና የጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አካላት ተገኝተዋል።

አለም አቀፍ የህጻናት መርጃ ድርጅት/Unicef ለሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገቃዋቆቶ መስከረም 2/2019 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}አለም አቀፍ የህጻናት መርጃ ድርጅት ...
12/09/2026

አለም አቀፍ የህጻናት መርጃ ድርጅት/Unicef ለሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ

ቃዋቆቶ መስከረም 2/2019 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}

አለም አቀፍ የህጻናት መርጃ ድርጅት Unicef መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ- ሰናይ ድርጅት ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ለሚገኙ ለመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የትምህርት መርጃና ለሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል።

ድርጅቱ በወረዳው ቅድመ-መደበኛ እና ከ1-8ተኛ ክፍል የመማሪያ መጽሐፍቶችን፣ የሴቶቾ የንጽህና መጠበቂያ ሳሙና፣ፓዶችን እንዲሁም ለተማሪዎቹ የልብስ መቀየሪያና ማረፊያ ክፍል የሚሆኑ ፍራሾችንና የተለያዩ አልባሳቶችን ድጋፍ ማድረጉን የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ገልጿል።

ድጋፉን ያበረከቱት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን ድጋፉ የሴቶችን በራስ መተማመንና የትምህርት ተሳትፎ በማሳደግ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያግዝ መሆኑን በማንሳት ድጋፍ ያደረገውን ድርጅት አመስግነዋል።

በድጋፉ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ፣ የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ አቶ ካሚል ፈረጃና ምክትላቸው አቶ መሀመድ ሱልጣን እና ርዕሰ መምህራኖችና ሱፐርቫይዘሮች ተገኝተዋል።

በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ቀረሶ ቀበሌ በክላስተር እየለማ ያለ የመኸር ባቄላ የደረሰበት ደረጃጳጉሜ 5/2018 አልቾ ኮሙኒኬሽን
10/09/2026

በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ቀረሶ ቀበሌ በክላስተር እየለማ ያለ የመኸር ባቄላ የደረሰበት ደረጃ

ጳጉሜ 5/2018 አልቾ ኮሙኒኬሽን

በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FSRP ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነባው የቀረሶ የመስኖ ፕሮጀክት የደረሰበትን ደረጃ ምልከታ ተደረገቃዋቆቶ ጳጉሜ 5/20...
10/09/2026

በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FSRP ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነባው የቀረሶ የመስኖ ፕሮጀክት የደረሰበትን ደረጃ ምልከታ ተደረገ

ቃዋቆቶ ጳጉሜ 5/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}

በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክብርት ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን፣ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ እና የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሱልጣን በርጋ በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FSRP ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በቀረሶ ቀበሌ የሚገነባውን የቀረሶ የመስኖ ፕሮጀክት የደረሰበትን ደረጃ ምልከታ አድርገዋል

የመስኖ ፕሮጀክቱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ሰፊ መሬቶችን በማልማት የአከባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን የግንባታውን ሙሉ ወጪ በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም/FSRP የሚሸፈን ይሆናል።

አስሚድ ለቤዛ የበጎ አድራጎት ማህበር ለ385 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ገለጸ፡፡በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ኩተሬ ከተማ ላይ የሚገኘው አስሚድ ለቤዛ የበጎ አድራጎት ማህበር ለ385 ...
10/09/2026

አስሚድ ለቤዛ የበጎ አድራጎት ማህበር ለ385 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ገለጸ፡፡

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ኩተሬ ከተማ ላይ የሚገኘው አስሚድ ለቤዛ የበጎ አድራጎት ማህበር ለ385 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል፡፡

ማህበሩ ከአባላቱ እና ከተለያዩ የበጎ አድራጊ ግለሰቦች በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ 250 ደረዝን ደርዘን እና 22 ፓኬት ስክርቢቶ ድጋፍ አድርጓል፡፡

በድጋፉ የተገኙት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን ማህበሩ በየጊዜው አቅሙን በማሳደግ በመንግስት ሊሸፈኑ የማይችሉ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

እንደ ወረዳ ማህበሩ ለማህበረሰቡ እና ለወረዳው አስተዳደር አጋዥ መሆኑን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪዋ ከትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ በተጨማሪ የአቅመ ደካሞችን ቤት መገንባትን ጨምሮ ሌሎች የበጎ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በጎነት ሰው መሆን እና ሰው እሆናለሁ ብሎ ማሰብና መስጠትን መሰጠት ነው ያሉት ወ/ሮ መህድያ ማህበሩ ተሞክሮዎችን ማስፋት ይጠበቅበታል በማለት መህበሩ ላደረገው ድጋፍ በወረዳው አስተዳደር ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በጎ ስንሰራ ለሌሎች ተስፋ ከመሆን በተጨማ በበጎነት ውስጥ ራሳችንን ማየት እንችላለን ያሉት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ተደራሽነቱን ከወረዳ ባለፈ በዞን ደረጃ ማስፋት ይገባል ብለዋል፡፡

ማህበሩ አርቆ አሳቢ እና ትውልድን ሊያሻግር የሚችል ስራ እየሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሙዘይን የአባላት ቁጥርን መጨመር እና ወርሃዊ የአባላት መዋጮችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡

የአስሚድ ለቤዛ የበጎ አድራጎት ማህበሩ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ፈድሉ አሽራቅ በበኩላቸው የድጋፍ ገንዘቡ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሃገር ከሚገኙ የበጎ አድራጊ ግለሰቦች መሰብሰቡን ገልጸው በሂደቱ ለተሳተፉ አካላት በማህበሩ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በድጋፍ ፕሮግራሙ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ሱልጣን በርጋ የወረዳው ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ሰማን ኸይረዲን የትምህርት ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ካሚል ፈረጃ የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሃላፊ ወ/ሮ ሳረት ረዲ የኩተሬ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ሚፍታህ ድሌቦ የአስሚድ ለቤዛ ማህበር ሰብሳቢ አቶ ፈድሉ አሽራቅ እና ሌሎች የማህበሩ አባላት እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተዋል፡፡

ጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ
በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338

በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/

በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk

በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication

በቲክቶክ https://vm.tiktok.com/ZM6BRmsNa/

ኢንስታግራም https://www.instagram.com/p/C1Za_1HtXH1/?igsh=YWYwM2I1ZDdmOQ==

ጷግሜ 5 የነገው ቀን "የዲጅታል ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት"በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ጷግሜ 5 የነገው ቀን በቃዋቆቶ ኮንስትራክሽ እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል፡...
10/09/2026

ጷግሜ 5 የነገው ቀን "የዲጅታል ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት"

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ጷግሜ 5 የነገው ቀን በቃዋቆቶ ኮንስትራክሽ እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡

በዓሉ "የዲጂታል ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት በሚል በኮሌጁ ቅጥር ግቢ እየተከበረ ይገኛል፡፡

ጿግሜን ስናከብር አመቱን ሙሉ ስናከናውናቸው የነበሩ የልማት ስራዎች የሚዘከሩበት እና የቀጣይ አመት ተጨማሪ ስንቅ የሚሰነቅበት መሆኑን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን ገልጸዋል፡፡

የነገው ቀን ስንል ትናንት የያዝናቸውን ስኬቶች አስጠብቀን ለነገ ራእይ የምንሰንቅበት እና ሀገራችንን ወደ ተሻለ ደረጃ የምናሸጋግርበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

እንደ ሀገር ለዲጅታል አለም ልዩ ትኩረት በመስጠት ሀገር ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት በርብርብ እየተሰራ መሆኑን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪዋ በዓሉ ኮሌጁ ላይ ሲከበር የብዙ ፈጠራዎች መገኛ መሆናቸውን በማሰብ መሆኑን አሳውቀዋል፡፡

የቃዋቆቶ ኮንስትራክሽን እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጃፈር መሀመድ ኮሌጁ የአካባቢው ማህበረሰብ ፍላጎት ለማሳካት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እና የስልጠና መስኮች ተደራሽ ለመሆን እየሰራ መህኑን አንስተዋል፡፡

በእለቱም በኮሌጁ የተከናወኑ ስራዎች ምልከታ የተደረገ ሲሆን በዲጂታል አይዲ ምዝገባ የተሻለ ተደራሽ ላደረጉ ባለሙያዎች እና በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ውጤታማ ለነበሩ አካላት የእውቅናና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል ፡፡

09/09/2026

ጳግሜ 4 የህብር ቀን "ብዝሀነት የኢትዮጲያ ጌጥ" በሚል መሪ ቃል በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ በእንስላስ ችኩል ተራራ ላይ

አልቾ ኮሙኒኬሽን

Address

Silte
Werabe
KAWAKOTO

Opening Hours

Monday 07:00 - 19:00
Tuesday 07:00 - 19:00
Wednesday 07:00 - 19:00
Thursday 07:00 - 19:00
Friday 07:00 - 17:00
Saturday 07:00 - 17:00
Sunday 07:00 - 19:00

Telephone

+251924711807

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።:

Shortcuts

Share