የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Waka
  • የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ግልጽነትን ለማስፈን እና በእውነተኛ መረጃ የበለፀገ ማህበረሰብ በማፍራት ሀገራዊ አንድነትን እና የጋራ መግባባትን ለማምጣት እንሰራለን !

‎በወረዳው ባቶ ቃልቦ ቀበሌ አጠቃላይ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሄደ‎‎ግንቦት 05/2018 ዓ.ም. (የማ/ወ/መ/ኮ)፦‎‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ባቶ ቃልቦ ቀበሌ፣ መልካም አስተዳደርን፣ የል...
13/05/2026

‎በወረዳው ባቶ ቃልቦ ቀበሌ አጠቃላይ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሄደ

‎ግንቦት 05/2018 ዓ.ም. (የማ/ወ/መ/ኮ)፦

‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ባቶ ቃልቦ ቀበሌ፣ መልካም አስተዳደርን፣ የልማት ጉዳዮችን እና ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን መሠረት ያደረገ ሰፊ የህዝብ ውይይት መድረክ ከቀበሌው ማህበረሰብ ጋር ተካሂዷል።

‎በመድረኩ የዳውሮ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃ እና ህብረት ስራ መመሪያ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር በተላ በየነ፣ የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው፣ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ እና የጤና ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አስናቀ አካሉ፣ የወረዳው ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቀስስ ባንተይዋሉ ፎላ፣ የቀበሌ ደጋፊ አመራር እንዲሁም ከወጣት እስከ አዋቂ ያለው በስፋት ተገኝተዋል።

‎በቦታው የተገኙት የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው በንግግራቸው፣ መንግሥት የህብረተሰቡን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በመፍታት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በብልፅግና መንግሥት ዘመን በሀገር ደረጃ ብቻ ሳይሆን በአካባቢውም በርካታ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን በማንሳት፣ ቀጣይም የህዝቡን ጥያቄዎች በትኩረት በመፍታት የብልፅግና ጉዞውን ለማሳካት መንግሥት እና ህዝብ በጋራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

‎የዳውሮ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃ እና ህብረት ስራ መመሪያ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር በተላ በየነ በበኩላቸው፣ በብልፅግና ፓርቲ መሪነት ዳውሮ በልማት እየተቀየረች መሆኗን ጠቅሰው፣ ከህዝቡ የሚነሱ ጥያቄዎች በውይይት እየተፈቱ እንደሚሄዱ ገልጸዋል። ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶችም ቅድመ ሁኔታዎች ተሟልተው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ እንደሚሰራ አስረድተዋል። ብልፅግና ስራውን እየሰራ ችግሮቹን እየፈታ እንደምሄድ አጠንክረው ተናግረዋል።

‎የማረቃ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቀስስ ባንተይዋሉ ፎላ በበኩላቸው፣ ትምህርት የማንኛውም ማህበረሰብ እድገት መሠረት መሆኑን ገልጸው፣ በዘርፉ ያሉ ችግሮችን በመፍታት ተወዳዳሪ እና ብቁ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

‎በውይይቱ የተሳተፈው ማህበረሰብ በዋናነት በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ማነቆ ሆነው የቆዩ የመሠረተ ልማት ጉዳዮችን አንስቷል፤ በተጨማሪም የትምህርት ጥራት ጉዳዮች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ ጥያቄ አቅርቧል። በአካባቢው ያሉ ልዩ ልዩ ችግሮች ተፈትተው ዘላቂ ልማት እንዲረጋገጥም አሳስበዋል።

‎ከማህበረሰቡ ለቀረቡ ጥያቄዎች በቦታው የተገኙ የዞን እና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በቂ ማብራሪያ እና ምላሽ በመስጠት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

‎በመጨረሻም በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የስንዴ ነዶ መሆኑን ለህዝቡ የማስተዋወቅ ስራ ተሰርተው፣ ህዝቡም የስንዴ ነዶን በመምረጥ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማየት ከመንግሥት ጋር በአንድነት እንደሚሰሩ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም የአካባቢው ማህበረሰብ ከመንግሥት ጎን በመቆም በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በንቃት እንደሚሳተፍ ቃል ገብቷል።

‎ዘገባው፡የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

ከስራ ዕድል ፈጠራ አኳያ የክልሉ መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ የስራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ሀላፊ ዶ/ር ...
13/05/2026

ከስራ ዕድል ፈጠራ አኳያ የክልሉ መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ የስራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ሀላፊ ዶ/ር ዐብይ አንዴሞ ቢሮው በክልሉ በ2018 በጀት አመት 10 ወራት ውስጥ የዜጎችኝ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ማከናወኑን ተናግረዋል።

ሀላፊው አክለውም ከስራ ዕድል ፈጠራ አኳያ በግብርና፣በኢንዱስትሪና አገልግሎት ዘርፎች በአጠቃላይ ለ62 ሺ 72 ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩንም አብራርተዋል።

የቢሮው ምክትል ሀላፊና የስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ዳዊት ወንድሙ በበኩላቸው ቢሮው ከፋይናንስ አቅርቦት አንፃር 694 ሚሊየን 186 ሺ 27 ፋይናንስ በማቅረብ ወጣቶች ወደ ስራ እንዲገቡም መደረጉን ገልጸዋል።

በመስሪያና መሸጫ አቅርቦት ዙሪያ 5 ሺ 595 ሄክታር መስሪያና መሸጫ ቦታ እንዲሁም 87 መስሪያና መሸጫ ሼዶችን ማቅረብ መቻሉ ተገልጿል።

ለኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ከመፍጠር አኳያ 168 ሚሊየን 411 ሺ 359 ብር የገበያ ትስስር መፍጠር ተችሏል።

በሜካናይዜሽን እርሻ ለወጣች የስራ ዕድል ለመፍጠር የክልሉ መንግስት 15 የእርሻ ትራክተሮችን ገዝቶ ለዞኖች በማውረድ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውንም አቶ ዳዊት ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል በየአካባቢው የመኖ ማቀነባበሪያ በማመቻቸት የሌማት ትሩፋት ዘርፍን ውጤታማነት ለማላቅና በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ቢሮው እየተጋ መሆኑ ተመላክቷል።

ቢሮው GHUCC ከተባለ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ስራ አጥ ዜጎችን በማሰልጠንና የብድር አገልግሎት በማመቻቸት በተለያዩ ዘርፎች ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ እያስቻለ ይገኛል።

በመጨረሻም ወጣቶች በሚሰጣቸው ስልጠና መሠረት የተመቻቸላቸውን የብድር አገልግሎት በመጠቀም የተለያዩ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው ውጤታማ ተግባራትን እንዲያከናውኑም አሳስበዋል ሲል ደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።

‎በወረዳው ባላ ዮዮ ቀበሌ አጠቃላይ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሂደ  ‎‎ግንቦት 04/2018 ዓ.ም (የማ/ወ/መ/ኮ)፦‎‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ባላዮዮ ቀበሌ፣ ከአጠቃላይ ከቀበሌው ማህበረሰ...
12/05/2026

‎በወረዳው ባላ ዮዮ ቀበሌ አጠቃላይ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሂደ

‎ግንቦት 04/2018 ዓ.ም (የማ/ወ/መ/ኮ)፦

‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ባላዮዮ ቀበሌ፣ ከአጠቃላይ ከቀበሌው ማህበረሰብ ጋር መልካም አስተዳደርንና ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን መሠረት ያደረገ ሰፊ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሂዷል።

‎በመድረኩ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ፣ የወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ፣ የቀበሌው ደጋፊ አመራሮች፣ የፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ከወጣት እስከ አዋቂ ተገኝተዋል።

‎በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው ዋና አስታተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው መንግሥት ህብረተሰቡን የመልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስና ሁለንተናዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሲሰራ ቆይቷል ፤ አሁንም የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ትኩረት ሰጥተው እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በተጨማሪም በወረዳ ውስጥና በዞናችን እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎችን አንስተዋል።

‎የወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ዘካሪያስ ወንድሙ ፓርቲው የህዝብ አንድነት፣ ሰላምና ልማትን በማረጋገጥ ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሠራ ገልጸው፣ ህብረተሰቡም በልማትና በሰላም ጉዳዮች ተሳትፎውን እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።

‎የዳውሮ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ስነምግባር ኮሚሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ወንድሙ ህዝቡ ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ያለውን ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።

‎የዳውሮ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር በተላ በየነ በበኩላቸው፣ የህዝቡ ንቁ ተሳትፎና የመንግሥት ተቋማት የተቀናጀ አሰራር በአካባቢው የሚፈለገውን ፈጣን ለውጥ ለማምጣት ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ህብረተሰቡ በልማት ስራዎችና በማህበራዊ አንድነት ላይ ያለውን ተሳትፎ ይበልጥ እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።

‎በውይይቱ ላይ ተሳታፊዎች ከመልካም አስተዳደርና ከመሰረተ ልማት ጋር በተያያዘ በቀበሌው ለብዙ ዘመናት ያልተፈቱ ጥያቄዎች እንዳሉ በማንሳት፣ በዋናነት የመብራት፣ የንፁህ መጠጥ ውሃና የመንገድ ችግሮች መሆናቸውን ገልፀዋል። እነዚህ ችግሮች ለረጅም ጊዜ የህዝቡ ጥያቄ ሆነው መቆየታቸውን በማንሳት፣ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ በአፋጣኝ እንዲፈታቸው ጠይቀዋል።

‎ከመድረኩ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል። በዚህም አፋጣኝ መፍትሄ የሚጠይቁ ጉዳዮችን ፈጥነው እንደሚፈቱ፣ ሌሎቹን ደግሞ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሠሩ በቦታው የተገኙ የዞንና ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ገልጸዋል።ህዝቡም ከመንግሥት ጎን በመቆም በልማት፣ በሰላምና በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በንቃት እንደሚሳተፍ ቃል ገብቷል።

በመጨረሻም የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲ ምልክት ስንዴ መሆኑ ለህዝቡ ተስተዋውቋል፤ ህዝቡም ስንዴን በመምረጥ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማየት እንደሚሠራ ተስማምቷል።

‎ዘገባው፣ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

በክልሉ የሕዝቡን ችግር በማድመጥ ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሰ በብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮችና...
11/05/2026

በክልሉ የሕዝቡን ችግር በማድመጥ ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሰ በብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ጋር በቀጣይ ተልዕኮዎች ዙሪያ በቦንጋ ከተማ የተካሄደው የምክክር መድረክ ተጠናቋል።

በምክክር መድረኩ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም በመገምገምና በቀጣዩ ጊዜያት መፈጸም በሚገባቸው ተልዕኮዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

የምክክሩ ተሳታፊ የሁለቱ ክልል ምክር ቤት የሕዝብ ተወካዮች ፤ የክልሉ ሕዝብ የዘመናት በክልል የመደራጀት ጥያቄ መመለስ የተቻለው በብልጽግና ፓርቲ ዘመን ነው ያሉት።

ይህም እንደክልል የመደመጥ ዕድል የተረጋገጠበት ነው ያሉት ተወካዮቹ፤ በዚህም ፓርቲው የሕዝብን ችግር ወርደው በማዳመጥ የልማት ተደራሽነት በማረጋገጥ ሕዝብን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አስረድተዋል።

የተመዘገቡ ውጤቶች እንዲቀጥሉና ቀሪ የሕዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ከሕዝቡ ጋር ወርደው በመነጋገር ምላሽ እንዲሰጥ በትኩረት እንደሚሰሩ የሁለቱ ምክር ቤት ተወካዮች አንስተዋል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር),ባለፉት ጥቂት ዓመታት የክልሉ አቅም በፈቀደው ልክ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለህዝብ አገልግሎት ማብቃት መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም አመራሩ በቀጥታ እስከ ቀበሌ ድረስ በመውረድ የህዝቡን ጥያቄዎች እንዲያዳምጥና ተጨባጭ ምላሽ እንዲሰጥ ተደርጓል ነው ያሉት።

ቀጣይ ከሕዝቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የአመራሩን የመፈጸምና የማስፈጸም የበለጠ በመገንባትና የታችኛውን መዋቅሮችን ማጠናከር ለነገ የማይባል ተግባር ነው ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ።

በክልሉ የሕዝቡን ችግር በማድመጥ ምላሽ የመስጠቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም የተናገሩት ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህም የሁለቱ ምክር ቤት ተወካዮች ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች በመደመር እሳቤ ውጤታማ ስራዎች የተከናወኑበት በብልጽግና ፓርቲ ዘመን ነው ብለዋል።

​ክልሉ ካለው ሰፊ አቅም አንጻር ገና ብዙ መስራትና መልፋት እንደሚጠይቅም ያነሱት አቶ ፍቅሬ አማን፤ በሚቀጥሉት 5ዓመታት ክልሉ አሁን ካለበት የዕድገት ደረጃ እጥፍ እንዲያድግ በትኩረት መሥራት ይገባል ብለዋል።

በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ምርጫው ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በተቀናጀና በተደራጃ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አንስተዋል አቶ ፍቅሬ አማን።

ከሁለቱ ምክር ቤት ተወካዮች ጋር የተደረገወሰ የምክክር መድረኩ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎችን በግልጽ ለይቶ ለማስቀመጥ፣ የህዝብ ጥያቄዎችን ለይቶ ለመረዳትና ዕጩዎች በተቀናጀ መንገድ እንዲሰሩ የጋራ መግባባት መፍጠር የተቻለበት ነዉ ሲል የዘገበው የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ ክልላዊ የበልግ አረንጓዴ አሻራ ተከላ በይፋ አስጀመሩ።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሸካ ዞን ተገ...
10/05/2026

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ ክልላዊ የበልግ አረንጓዴ አሻራ ተከላ በይፋ አስጀመሩ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሸካ ዞን ተገኝተው የሁለተኛው ዙር ክልላዊ የበልግ አረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሐግብርን በይፋ አስጀምረዋል።

በመርሐግብሩ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የሸካ ዞን በተፈጥሮ ሀብት የታወቀ መሆኑን ገልጸው፣ ይህንን እምቅ ጸጋ ወደ ላቀ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሸጋገር ተግባር በልዩ ትኩረት ሊከናወን እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይም በቡና ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮችና አልሚዎች የምርት ጥራትና መጠንን ለማሳደግ ትኩረት እንዲሰጡ ያሳሰቡት ዶ/ር ነጋሽ፤ ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በአካባቢው የተገኘው ሰላም ቀጣይነት እንዲኖረውና የልማት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ኅብረተሰቡ ከመንግሥት ጎን እንዲቆም የጠየቁት ርዕሰ መስተዳደሩ፤ የብልፅግና ፓርቲ ለሕዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ እየሰጠ መሆኑንና ይህ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ዓመታት በክልሉ ከ 1.6 ቢሊዮን በላይ ቡናን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በ328 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ መተከላቸውን ገልጸዋል።

ኅብረተሰቡ የመርሐግብሩን ጠቀሜታ በመረዳት በንቃት እየተሳተፈ በመሆኑም የችግኞቹ የፀድቀት መጠን 86 በመቶ መድረሱንም ጠቁመዋል።

በ2018 ዓ.ም የበልግ ተከላ ወቅትም ከ85 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በ20 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ለመትከል የታቀደ ሲሆን፤ በተለይም በቡና ምርት በሚታወቁ የክልሉ አከባቢዎች ያረጁ የቡናዎችን በአዲስና በምርጥ ዝርያዎች የመተካት ሥራ የበልግ ተከላ አካል መኾን እንዳለበት ተናግረዋል።

የዘንድሮው የሁለተኛው ዙር ተከላ የማጠቃለያ ምዕራፍ በመሆኑም መላው የክልሉ ሕዝብ በነቂስ በመውጣት ዕቅዱ እንዲሳካ አሻራውን እንዲያኖር አቶ ማስረሻ ጥሪ ቀርቧል።

የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ እና የየኪ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ተሰማ እንደገለጹት፤ በአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት የዞኑን ተፈጥሮአዊ ሀብት ከመጠበቅ ባለፈ ለነዋሪው ዘላቂ ጠቀሜታ እያመጡ ይገኛሉ።

በተከላ መርሐግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞንና የወረዳ አስተዳዳሪዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ በየኪ ወረዳ ጪ ቀበሌ በሚገኝ 3.2 ሄክታር ማሳ ላይ ዝርያቸው የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ተተክለዋል ሲል የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

‎በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ የመሰረተ ልማት የውሃ ቱቦና ቀሽር ቡና መያዙን የማረቃ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። ‎‎መነሻውን ኢሰራ ባለ ከተማ በማድረግ መድረሻውን ወላይታ ...
09/05/2026

‎በህገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ የመሰረተ ልማት የውሃ ቱቦና ቀሽር ቡና መያዙን የማረቃ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

‎መነሻውን ኢሰራ ባለ ከተማ በማድረግ መድረሻውን ወላይታ ሶዶ ያደረገው ISUZU የጭነት ተሽከርካሪ መኪና፣ የኋላ ታርጋ ቁጥር B42706 Code 3 ISUZU የሆነው፣ በሚሊዮን ብር የሚገመት ለመሰረተ ልማት የመጣውን የውሃ ቱቦን በመቆራረጥና ከጭድ ጋር በማቀላቀል በማዳበር ውስጥ በመደበቅ ለማሳለፍ ሙከራ ሲያደርግ ተይዟል።

‎በተጨማሪም ተሽከርካሪው ስድስት ኩንታል ቀሽረ ቡና ጭኖ በህገ-ወጥ መንገድ ለማለፍ ሲንቀሳቀስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት በወረዳው ኢየሱስ ቀበሌ በተለምዶ “ሮብ” ተብሎ በሚጠራበት አካባቢ በቀን 30/8/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ መያዙን የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ዘላለም ማሞ ገልጸዋል።

‎ረዳት ኢንስፔክተር ዘላለም ማሞ በሰጡት መግለጫ፣ ለህዝብ ጥቅም ተብለው የሚመጡ የመሰረተ ልማት ግብዓቶች በአግባቡ ተጠብቀው ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ ሁሉም አካላት በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል። “የህዝብ ሀብት የህዝብ ነው፤ ይህንን ሀብት በህገ-ወጥ መንገድ ለግል ጥቅም ለማዋል የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ በጥብቅ ይከታተላል፤ ህብረተሰቡም የሚያውቀውን መረጃ በወቅቱ ለጸጥታ አካላት ማሳወቅ አለበት” ሲሉም አሳስበዋል።

‎የማረቃ ወረዳ ማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ማስተባበሪያ ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር አጥናፉ አባቴ በበኩላቸው፣ በተደረገው ጠንካራ ክትትል በህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረው ዕቃ መያዙን ገልጸዋል።

‎እንደዚህ ዓይነት ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች ለአካባቢው ልማት፣ ለህዝብ ጥቅምና ለሰላም ትልቅ እንቅፋት እንደሚፈጥሩ ጠቁመው፣ ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ተመሳሳይ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን በማጋለጥ የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

‎በዚህ የተሳካ የክትትል ስራ ውስጥ በትጋት የተሳተፉ የፖሊስ አባላትና ወቅታዊ መረጃ በመስጠት ትብብር ያደረጉ የህብረተሰብ አባላትም ልዩ ምስጋና ተገልጾላቸዋል።

‎‎በመጨረሻም በህገ-ወጥ መንገድ የተያዙ ንብረቶች በአሁኑ ወቅት በማረቃ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን፣ ምርመራው ከተጠናቀቀ በኋላም ፍርድ ቤት ቀርበው ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ የማረቃ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

‎ዘገባው፣ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

በማሪ ማንሳ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ዓላማና የለውጥ ጉዞ ለመደገፍ የተዘጋጀው ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ በከፍተኛ ድምቀት ተካሄደ በዳውሮ ዞን ማሪ ማንሳ ወረዳ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በ...
08/05/2026

በማሪ ማንሳ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ዓላማና የለውጥ ጉዞ ለመደገፍ የተዘጋጀው ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ በከፍተኛ ድምቀት ተካሄደ

በዳውሮ ዞን ማሪ ማንሳ ወረዳ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ጉዞን የሚደግፍና ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ በማሪ ከተማ ተካሂዷል።

የወረዳው ነዋሪዎች ለሀገራዊ አንድነትና ለልማት ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተለያዩ መፈክሮች፣ በዜማዎችና በባህላዊ ጭፈራዎች የታጀበ ደማቅ ድባብ ፈጥረዋል።

ይህ ታላቅ ሰልፍ የነገዋን ኢትዮጵያ በሁለንተናዊ ዘርፍ ተምሳሌት ለማድረግ በወረዳው የታየው አንድነትና መነቃቃት ትልቅ ተስፋ የፈነጠቀ መሆኑም ተመላክቷል።

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ባለፉት አምስት ዓመታት በብልፅግና ፓርቲ መሪነት የተመዘገቡ ስኬቶችንና የልማት ትሩፋቶችን ለማፅናት ፓርቲውን መምረጥ ብልህነት ነው ብለዋል።

አቶ ዳዊት በማሪ ማንሳ ወረዳ የታየው ህዝባዊ አንድነትና ድጋፍ በዞኑ ለሚከናወኑ የልማትና የሰላም ስራዎች ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን በመግለፅ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት እንዲሳካ የህዝብ አንድነት መሰረት መሆኑንም አፅንኦት ሰጥተዋል።

የማሪ ማንሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳመነ ዳዋና በበኩላቸው ብልፅግና ፓርቲ አካታች፣ አቃፊና አሰባሳቢ ፓርቲ መሆኑን ጠቅሰው የሀገሪቱን ብልፅግና ለማረጋገጥና ኢትዮጵያን ተምሳሌት ሀገር ለማድረግ ህዝቡ የፓርቲው ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶ እንዲመርጥ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ዳመነ አክለውም የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ እንዲሆንና ወረዳው የልማት ተምሳሌት እንዲሆን ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመቆም እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ የማረቃ ገና ምርጫ ክልል ዕጩዎቹ ተገኝተው ራሳቸውን ያስተዋወቁ ሲሆን ለህዝብ በታማኝነትና በቁርጠኝነት ለማገልገል ቃል ገብተዋል።

ሰልፈኞቹም በወረዳው የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን እንደሚደግፉና ለሀገራዊ አንድነት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ በሰላማዊ ድባብ ገልጸው ሰልፉ በሰላም ተጠናቋል ስል የወረዳው ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

‎ወጣቶች በሀገር ግንባታና ሰላማዊ ምርጫ ለማስፈን ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ‎‎ማረቃ፣ ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም (የማ/ወ/መ/ኮ)‎‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ የጌንዶ ክላስተር ወጣቶች...
08/05/2026

‎ወጣቶች በሀገር ግንባታና ሰላማዊ ምርጫ ለማስፈን ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ

‎ማረቃ፣ ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም (የማ/ወ/መ/ኮ)

‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ የጌንዶ ክላስተር ወጣቶች አንድ ላይ በመሆን የብልፅግና ፓርቲን የድጋፍ ሰልፍ አካሂደዋል። “የወጣቶች ተሳትፎ ለሰላማዊ ምርጫ” እና “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው ሰልፍ፣ ወጣቶች ለሀገራቸው ሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲያዊ ሂደት ያላቸውን ቁርጠኝነት በግልፅ ያሳየ መሆኑ ተገልጿል።

‎በሰልፉ ላይ የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው እና የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስናቀ አካሉ ተገኝተው ለወጣቶች መልዕክት አስተላልፈዋል። አመራሮቹ በንግግራቸው፣ ወጣቶች የሀገር ተስፋና የለውጥ ኃይል መሆናቸውን ጠቅሰው፣ በሰላማዊና ፍትሃዊ ምርጫ ሂደት ውስጥ ያላቸው ንቁ ተሳትፎ ለሀገር መረጋጋትና ለዴሞክራሲ ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

‎በተጨማሪም ወጣቶች ከግጭትና ከአሉባልታ በመራቅ በአንድነት፣ በሥራና በልማት ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ተጠቁሟል። በየአካባቢያቸው ሰላምን በማስጠበቅ፣ ሕዝብን በማንቃትና በምርጫ ሂደት ውስጥ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ በመሳተፍ ለተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ ቀርቧል።

‎በሰልፉ የተሳተፉ ወጣቶች በበኩላቸው፣ ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር በአንድነት እንደሚሰሩና ሰላማዊ ምርጫ እንዲሳካ ከመንግሥትና ከሕዝብ ጎን በመቆም ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል።በተጨማሪም ወጣቶች ፓርቲን በመደገፍ ለፓርቲው ያላቸውን እምነትና ቁርጠኝነት በተግባር አሳይተዋል። እንዲሁም የፓርቲውን ራዕይና ፖለቲካዊ አቋም በማጠናከር ለሀገር ሰላም፣ ልማትና አንድነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ገልፀዋል።

‎ዘገባው፣ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

በዳውሮ ዞን ዛባ ጋዞ ወረዳ የብልጽግና ጉዞን የሚደግፍና ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛልበዛባ ጋዞ ወረዳ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ቃል...
07/05/2026

በዳውሮ ዞን ዛባ ጋዞ ወረዳ የብልጽግና ጉዞን የሚደግፍና ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል

በዛባ ጋዞ ወረዳ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ቃል በወረዳው የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች ደማቅ የድጋፍ ሰልፍ ማካሄድ ጀምረዋል።

የወረዳው ነዋሪዎች ለሀገራዊ አንድነትና ለልማት ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተለያዩ ዘማዎች፣ በባህል ጭፈራዎች እየገለጹት ይገኛሉ።

ይህ ታላቅ ሰልፍ የነገዋን ኢትዮጵያን በሁለንተናዊ ዘርፍ ተምሳሌት ለማድረግ በዛባ ጋዞ ወረዳ የታየው አንድነት ተስፋ ጭሯል ስል የዛባ ጋዞ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

 ከታች በስም ዝርዝር የተጠቀሳችሁ ወጣቶች ብቻ ዛሬ 8:00 ሰዓት በማረቃ ወረዳ ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት የብድር ስርጭት ስለሚካሄድ፣ በሰዓቱ እንዲትገኙ ጽ/ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል።
07/05/2026


ከታች በስም ዝርዝር የተጠቀሳችሁ ወጣቶች ብቻ ዛሬ 8:00 ሰዓት በማረቃ ወረዳ ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት የብድር ስርጭት ስለሚካሄድ፣ በሰዓቱ እንዲትገኙ ጽ/ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል።

የማረቃ ወረዳና ዋካ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች በነቂስ ወጥተው ያሳዩት የብልጽግና ፓርቲ ድጋፍ ሰልፍ በምስል።
06/05/2026

የማረቃ ወረዳና ዋካ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች በነቂስ ወጥተው ያሳዩት የብልጽግና ፓርቲ ድጋፍ ሰልፍ በምስል።

Address

B52
Waka
SWEPR,DAWUROZONEMAREKAWEREDA

Telephone

+251976984842

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት:

Share