የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ይህ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። This is the official page of Snnpr Peace And Security Bureau where you can get latest info in time.

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ለተሾሙት አቶ አቤንኤዘር ተረፈ እና ምክትል ቢሮ ሀላፊና የግጭት አፈታትና መከላከል ዘርፍ ሀላፊ አቶ መንግስቱ መጃ ከቢሮ ማናጅመንት አ...
28/10/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ለተሾሙት አቶ አቤንኤዘር ተረፈ እና ምክትል ቢሮ ሀላፊና የግጭት አፈታትና መከላከል ዘርፍ ሀላፊ አቶ መንግስቱ መጃ ከቢሮ ማናጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ሠራተኞች ጋር ትውውቅ አደረጉ።
‎ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም ወ/ሶዶ
አዲስ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ ሆነዉ የተሾሙት አቶ አቤንኤዘር ተረፈ እና ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ መንግስቱ መጃ ከቢሮ ማናጅመንት አባላት እና ከአጠቃላይ ሠራተኞች ጋር ትውውቅና የቀጣይ ሥራዎች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
የቢሮው ማናጅመንት አካላት እና ሠራተኞች አዲስ ለተሾሙት ኃላፊዎች መልካም የሥራና የትጋት ጊዜ እንዲሆን ምኞታቸውን ገለፀዋል።
የቢሮው ኃላፊዉም ለተደረገላቸዉ አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ ጊዜ ከሰክተሩ ተልዕኮና ግቦች አንጻር የሚታይ ውጤት ለማስመዝገብና ከመንግስትና ከህዝብ የሚጠበቅበትን ሀላፊነት ለመወጣት ከአጠቃላይ ሠራተኞችና ከባለድርሻ አካላት ለውጥ ለማምጣት በቅንጅት እንደሚሠሩም ጠቁመው ቢሮው ላደረገላቸው አቀባበል አመስግነዋል።
በትዉዉቅ መድረክ አዲሱ ተሿሚዎች፣ የቢሮዉ ም/ሀላፊ አቶ በቀለ ሎኮርማ፣ የማኔጅመንት አባላትና አጠቃላይ ሠራተኞች ተገኝተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት የ3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛልበርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ሰብሳቢነት የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበ...
27/10/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት የ3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛል

በርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ሰብሳቢነት የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በአርባ ምንጭ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ጉባኤው ባለፉ ጊዜያት በክልሉ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የሰላምና ፀጥታ ስራዎችን በመገምገም የክልሉን ሰላም ለማፅናት እና የፀጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችሉ ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥ ይሆናል።

የክልሉ መንግስት ከክልሉ ምስረታ ማግስት ጀምሮ ክልሉን የሰላምና የመቻቻል ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ በመሰነቅ በክልሉ የሚገኙ ባህላዊ የሰላም እሴቶችንና ማህበራዊ ተቋማት በመጠቀም እና በህብረተሰቡ ባለቤትነት በርካታ ውጤታማ የሰላምና ፀጥታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ ይታወቃል።

ጉባኤው በ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ክልሉን የሰላምና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የተሰሩ የፀጥታ ስራዎችን በመገምገም፥ ጥንካሬና ክፍተቶችን በመለየት ጥንካሬውን ለማስቀጠል እና ጉደለቶችን ለይቶ ለማረም እና በባለፈው ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈፃፀም ለመገምገም ያለመ ያለመም መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት የሩብ ዓመት አፈፃፀም በክልሉ የቀድሞ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ በአቶ ወገኔ ብዙነህ እየቀረበ ይገኛል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

አቶ አበንኤዘር ተረፈ- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋልመልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንሎት ተመኘን👍👍👍
23/10/2025

አቶ አበንኤዘር ተረፈ- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል
መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንሎት ተመኘን👍👍👍

በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ እና በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳዎች መካከል የእርቅ ሰላም ኮንፍራንስ ተካሄደ‎ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም‎በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ እና ‎በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳዎች ...
12/10/2025

በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ እና በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳዎች መካከል የእርቅ ሰላም ኮንፍራንስ ተካሄደ

ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም

በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ እና ‎በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳዎች መካከል ተፈጥሮ የነበረውን የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በመሎ ኮዛ ወረዳ ሳላይሽ መንደር ሁለት (2) ቀበሌ የእርቅ ሰላም ኮንፍራንስ መድረክ ተካሂዷል።

‎የእርቅ ሰላም ኮንፍራንሱ በሁለቱ መዋቅር ኃይማኖት አባቶች እና ሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት እና ፀሎት ተጀምሯል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሰላም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ በቀለ ሎኮርማ መንግስት ዜጎች በሰላም ወጥቶ በሰላም እንዲገቡ አበክሮ ይሰራል ብለዋል።

‎አክለውም ሰላም የሁሉም ነገር ቁንጮ በመሆኑ ህብረተሰቡ በአከባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እና ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩሉን ሚና መወጣት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።

የከሰሩ አንዳንድ ፖለቲከኞች ለራሳቸው ጥቅም በህዝቦች መካከል ግጭትና ግድያ በመፍጠር የግል ጥቅማቸውን ለማስከበር ብዙ የሰሩ በመሆኑ የሁለቱም መዋቅር ህብረተሰብ በቀጣይ የእነዚህን እኩይ ሴራ በማክሸፍ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በጋራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

‎የጎፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ምናሴ ኤልያስ ሰላም ከሁሉም ነገር ቀዳሚ እና ለሰው ልጆች እጅግ በጣም አስፈላጊ የሆነ በመሆኑ ሁሉም ለሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል ።

‎አክለውም በመሎ ኮዛ ወረዳ እና በሳላማጎ ወረዳ መከከል የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር በሰላም በመፍታት ለረዥም አመታት አብሮ የኖረውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማጠናከርና አብሮ የመኖር እሴት ማዳበር እንደሚገባ ተናግረዋል።

‎ዋንኛው ጠላታችን ድህነት እንጂ ሰው አይደለም ያሉት የሳላማጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ህጉ ቅጣቱ ህብረተሰቡ ከምንግዜውም በላይ የራሱን ሰላም በመጠበቅ አብሮነትና አንድነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

‎ሰላም ማፅናት፣ልማት ማስቀጠል፣ቀጠናው የተረጋጋ እንዲሆን እና ሰላምን በማደፍረስ የራሳቸውን ዓላማ ለማሳካት የሚንቀሳቀሱ አካላት ለህግ እንዲቀርቡ ለማድረግ የሳላማጎ እና የመሎ ኮዛ ወረዳ በቅንጅት መስራት አለባቸው ማለታቸውን የደቡብ ኦሞ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል ዘርፍ ማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዳይረክቶሬት ኮማንደር መከቴ ለማ በበኩላቸው ያለ ሰላም የትኛውንም ነገር ማሰብ ሆነ ማከናወን እንደማይቻል በመግለጽ ህብረተሰቡ የራሱን ሰላም መጠበቅ ብቻ ሳይሆን መንከባከብ ይገባል በማለት ገልፀዋል።

03/10/2025
በደቡብ ኢትዮጽያ ክልል ጌዴኦ ዞንና በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን በጸጥታ ዙሪያ የጋራ ምክክር ተካሄደ።መስከረም 21/2018 ዓ/ምበዉይይቱም የሁለቱም ዞኖች ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊዎች...
01/10/2025

በደቡብ ኢትዮጽያ ክልል ጌዴኦ ዞንና በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን በጸጥታ ዙሪያ የጋራ ምክክር ተካሄደ።

መስከረም 21/2018 ዓ/ም

በዉይይቱም የሁለቱም ዞኖች ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊዎች ፣የአጎራባች ወረዳዎች አሰተዳዳሪዎች የፖሊስ አዛዦችና የጸጥታ መዋቅር የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላቶች ተገኝተዉበታል

አቶ ሽብሩ ሚጁ የጌዴኦ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ እንደገለጹት የጌዴኦ ዞንና የወንድም ምዕራብ ጉጂ ዞን በጸጥታዉ ዘርፍ በጋራ መግባባት እየተሰራ የቆየ ሲሆን በአጎራባች አካባቢ የጸጥታ መደፍረስ እንዳይኖር ይህ የምክክር መድረክ አይነተኛ መፍትሔ መሆኑን ጠቅሰዉ ይህን መሰል ዉይይት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸዋል።

የምዕራብ ጉጂ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ አየለ ዴንባ ሰላምን መጠበቅና ማስጠበቅ የህልዉና ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዉ በሰላሙ ግዜ የተረጋገጠ ሰላም ሊገነባ ይገባል በማለት በሰላም ወዳዱ ህዝብ ለይ የተለያዩ አጀንዳዎችን በመፍጠር በአጎራባች አካባቢ የሰላም መደፍረስ እንዳይኖር ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።

በአጎራባች አካባቢ ምንም አይነት የጸጥታ ችግር እንዳይከሰት በቅንጅት እንደሚሰሩ አስተያየት ሰጪዎች የተናገሩ ሲሆን የህዝብ ለህዝብ ስራን በዘላቂነት እንዲተገበርና ከመቼዉም በበለጠ ተቀራርበዉ እንዲሰሩ ከስምምነት በመድረስ የዛሬዉ የምክክር መድረክ ተጠናቅቋል።

ዘገባዉ የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

01/10/2025
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ እና ተጠሪ ተቋም ሚሊሻ ጽ/ቤት አመራሮችና አጠቃላይ ሠራተኞች " የታደሰ ጂኦ ስትራቴጂያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮጵያዊ  ትጋት" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ...
01/10/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ እና ተጠሪ ተቋም ሚሊሻ ጽ/ቤት አመራሮችና አጠቃላይ ሠራተኞች " የታደሰ ጂኦ ስትራቴጂያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮጵያዊ ትጋት" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ስልጠና መስጠት ተጀምሯል።
መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ/ም
የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ ወገኔ ብዙነህ " የታደሰ ጂኦ ስትራቴጂያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮጵያዊ ትጋት" በሚል መሪ ሀሳብ ስለተዘጋጀዉ ስልጠና አስፈላጊነትና ዓለማ በተመለከተ የመንግስት ሠራተኛዉ ወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮችን ማወቅ፣ በንቃት መከታተልና የሚቀመጡ ሀገራዊ አቅጣጫዎችን የመፈጸም ሀላፊነት ያለበት የህብረተሰብ ክፍል ስለሆነ በሰነዱ የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮችን ጭምር በማንሳትና ስልጠናዉን በትኩረት መሳተፍ እንደሚጠበቅባቸዉ በመከፈቻ ንግግራቸዉ አሳስበዋል ።
የስልጠና ሰነዱን የሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ የሆኑት ክቡር አቶ ተስፋዬ እያቀረቡ ይገኛሉ። በመድረኩ የቢሮዉና የጽ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ናቸዉ።

በደቡብ ኢትዮጵያ እና በሲዳማ ክልል በአባላ አባያና በሎካ አባያ አዋሳኝ አካባቢዎች አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታን በተመለከተ የሁለቱም ክልል የፀጥታው ሴክተር አመራሮች በሀዋሳ ከተማ በጋራ መክረዋል...
30/09/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ እና በሲዳማ ክልል በአባላ አባያና በሎካ አባያ አዋሳኝ አካባቢዎች አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታን በተመለከተ የሁለቱም ክልል የፀጥታው ሴክተር አመራሮች በሀዋሳ ከተማ በጋራ መክረዋል።

‎መስከረም 20/2018ዓ.ም ፦ወ/ሶዶ
የደቡብ ኢትዮጵያና የሲዳማ ክልል የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊዎች በሁለቱ ህዝቦች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በዘላቂነት ለመፍታትና አሁናዊ የአካባቢውን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ የጋራ ውይይት አድርገዋል።
የውይይቱ ዓላማ የግጭቱ መንስኤ በሆኑ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት በመሥራት በቀጣይ የሁለቱን ህዝቦች አንድነት ወደነበረበት ለመመለስ እንደሆነ ተገልጿል ።
በወላይታና በሲዳማ ህዝቦች መካከል ያለው አንድነት የአጭር ጊዜ አለመሆኑን በውይይቱ የተገለፀ ሲሆን ይህንን አንድነት ወደ ነበረበት ለመመለስ በጋራ መሥራት እንደሚገባም በውይይቱ ተነስቷል ።
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ዳዊት ዳንጊሶ እንደገለጹት በየጊዜው በሚፈጠር ግጭት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረስ እንደሌለበት አንስተው የተፈጠረውን አለመግባባት የሁለቱ ክልል የሀገር ሽማግሌዎችን በማወያየት መፍታት እንደሚቻልም አንስተዋል።
የሲዳማና የወላይታ ህዝቦች አብረው የኖሩና በደም የተሳሰረ ህዝብ መሆኑን ያነሱት ሀላፊው በቀጣይ የሁለቱን ህዝቦች አንድነት ለማጠናከር በትኩረት መሠራት እንዳለበትም ገልጸዋል።
በሎካ አባያና በአባላ አባያ አዋሳኝ አካባቢዎች አሁን ላይ ከፀጥታ ሥጋት ነጻ መሆኑን አቶ ዳዊት ጠቁመው በቀጣይ የሁለቱ ወረዳ አመራሮችና የሀገር ሽማግሌዎች ለአካባቢው ዘላቂ ሠላም በጋራ መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ በበኩላቸው በህብረተሰቡ መካከል ግጭት ለመፍጠር የሚሯሯጡ ግለሰቦች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ ገልጸው የአካባቢውን ሠላም ወደነበረበት ለመመለስ የሁለቱ ክልል አመራሮች በትኩረት መሥራት ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል ።
#ሲክሠፀቢ

የደመራ እና የመስቀል በዓላትን ህብረተሰቡ እጅግ ሰላማዊ በሆነ መልኩ  እንዲያከብር በቂ ዝግጅት መደረጉን የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አሳወቀ። መስከረም 16 እና 17 በመላው ...
26/09/2025

የደመራ እና የመስቀል በዓላትን ህብረተሰቡ እጅግ ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲያከብር በቂ ዝግጅት መደረጉን የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አሳወቀ።
መስከረም 16 እና 17 በመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ የደመራ እና የመስቀል በዓላት በታላቅ ድምቀት ይከበራሉ ።
የእምነቱ ተከታዮች በዓሉን ከስጋት ነፃ
ሰላማዊና ፀጥታው ተጠብቆ እንዲያከብር የቅደመ ዝግጅት ስራው መጠናቀቁን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ አስታውቀዋል ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚከበረው የደመራና የመስቀል በዓል ከሃይማኖታዊ በዓል ባሻገር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው የቢሮ ሀላፊው ገልፀዋል ።

በዓሉን ለማክበር በርካታ የሀገር ውስጥና የዉጭ ቱሪስቶች ወደ ክልሉ እንደሚመጡ የገለፁት ሃላፊው እንግዶች፣ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ የፀጥታ መዋቀሩ በየደረጃ ካሉት አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ የህዝብን አንድነት ለማደፍረስና ክልሉ ሌላ ገፅታ እንዲይዝ የሚንቀሳቀሱ አካላት በክልሉ መኖራቸውን የገለጹት አቶ ወገኔ ፣ሰላም ወዳዱ ህዝብ በዓሉን ሲያከብር የአካባቢዉን ስላም ለማስጠበቅ እየተደረገ ላለው ሂደት የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል ።

በደመራ ስነ-ስርዓት ላይ ከበዓሉ አከባበር ጋር ግንኙነት የሌላቸውን ነገሮች ይዞ መምጣት ክልክል መሆኑን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ለፀጥታ ሃይሎች ሥራ ተባባሪ እንዲሆን ተናግረዋል።

ሕብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጎን በመቆም በዓሉ በሰላም እንዲከበር የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ በመግለጽ፣ ነዋሪዎች በበዓሉ አከባበር ወቅት አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከቱ ለፀጥታ አካላት በማሳወቅ የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

በክልሉ በመስከረም ወር ከሚከበሩ ባህላዊ የብሄረሰቦች የዘመን መለወጫ በዓላት መካከል የዎላይታ "ጊፋታ"፣ የጎፋ "ጋዜ ማስቃላ"፣ የኦይዳ "ዮኦ" የጋሞ "ዮ" ማስቃላ ዘመን መለወጫ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታ መዋቅርና የበዓሉ ተሳታፊዎች ላበረከቱት አሰተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመጨረሻም ለመላው የእምነቱ ተከታዮች የደመራ እና የመስቀል በዓላት የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮትና የአንድነት እንዲሆን ተመኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ የወላይታ ሶዶ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን  መርቀው ከፈቱ መስከረም 15/2018 ዓ.ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ የወ...
25/09/2025

ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ የወላይታ ሶዶ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን መርቀው ከፈቱ

መስከረም 15/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ የወላይታ ሶዶ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከልን መርቀው ከፍተዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በሳይንስና ኢኖቬሽን ሚኒስትር የአይ ሲ ቲ ዲጂታልና ኢኖቬሽን ሚንስትር ዲኤታ አቶ ሙሉቀን ቀሬ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ አልማዝ መሰለ እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስጫ ህብረተሰቡ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም የኢሚግሬሽን፣ አገልግሎት፣ የብሄራዊ መታወቂያ አገልግሎት ኢንቨስትመንት፣ ገቢዎች፣ንግድና ገበያ ልማትን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተመላክቷል።

በክልሉ የመጀመሪያ የሆነው የወላይታ ሶዶ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከልን ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።

#ደኢክመኮጉቢሮ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን ወይጦ ከተማ የአቅመ ደካማ /አዕምሮ ህመምተኛ / ለሆኑት ግለሰብ የመኖሪያ ቤት ግንባታ  ጀምሯል።ወ/ሶዶ፦ መስከረም 14 ቀን 201...
24/09/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን ወይጦ ከተማ የአቅመ ደካማ /አዕምሮ ህመምተኛ / ለሆኑት ግለሰብ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ጀምሯል።
ወ/ሶዶ፦ መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ/ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን ወይጦ ከተማ የአቅመ ደካማ /አዕምሮ ህመምተኛ / ለሆኑት ለአቶ አሪቶ ዋዶ የመኖሪያ ቤት ግንባታ በዛሬዉ ዕለት በግለሰቡ ይዞታ ላይ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የቢሮአችን ም/ቢሮ ሀላፊና የሠላም ዕሴት ግንባታና ብዙሀን አያያዝ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ በቀለ ሎኮርማ ለግንባታዉ የሚያስፈልጉ አስፈላጊ ቁሳቁሶችን አሟልተው ይዞ በመሄድ ግንባታዉን አስጀምረዋል።

Address

S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ:

Share