South Ethiopia Regional State Police Commission

South Ethiopia Regional State Police Commission ይህ የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ፖሊሳዊ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ! https://t.me/Southpolicecomm

በበዓላት ወቅት የሚደርሱ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል በሚያስችል መልኩ እየተሰራ እንደሆነ ተገለጸወላይታ ሶዶ ጳግሜ 02/2018 ዓ/ም (ደኢፖኮ)በዜጎች ህይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እ...
07/09/2026

በበዓላት ወቅት የሚደርሱ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል በሚያስችል መልኩ እየተሰራ እንደሆነ ተገለጸ

ወላይታ ሶዶ ጳግሜ 02/2018 ዓ/ም (ደኢፖኮ)

በዜጎች ህይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘዉን የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የትራፊክ ዲቪዥኑ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

በቀጣይ ቀናት የሚከበረዉን የዘመን መለወጫ በዓልን አስመልክቶ የመንገድ ትራፊክ አደጋ እንዳይደርስ ሁሉም በኃላፊነት እንዲወጡ የትራፊክ አደጋ ክትትልና ቁጥጥር ዲቪዥን ኃላፊ ም/ኢ/ር ዳንኤል በደቻ ጠይቀዋል።

አሽከርካሪዎች ይህንን ወቅት ከፍተኛ ኃላፊነት በመዉሰድና በተፈቀደዉ ፍጥነት በማሽከርከር አጠቃላይ የትራፊክ መመሪያና ደንብን አክብረዉ እንዲያሽከረክሩ አደራ ብለዋል።

በዓሉን አስመልክቶ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ለግብይት ወደ ከተማ ስለሚመጡ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ባለመዘናጋት በጥንቃቄ እንዲያሽከረክሩ ኃላፊዉ አሳስበዋል።

አሽከርካሪዎች በመጠጥና በአደንዛዥ ዕጽ ተጠቅመዉ እንዳያሽከረክሩ የተጠየቀ ሲሆን ይህንና መሠል ድርጊቶችን ጥንቃቄ በማድረግ ኃላፊነታቸዉን እንዲወጡ ተጠይቋል።

እግረኞች የዘዉትር ተግባር የሆነዉን ግራ መስመርን ብቻ በመጠቀም መንቀሳቀስና ለመሻገር ሲፈልጉ ለዚህ ተብሎ በተሰራዉ ዜብራን ብቻ በመጠቀም አደጋ እንዳይደረስ የበኩላቸዉን ኃላፊነት እንዲወጡ ይገባል።

በመጨረሻም አዲሱ ዓመት የሰላም የፍቅር የአንድነት እና ከትራፊክ አደጋ የጸዳ በዓል እንዲሆን ኢንስፔክተር ዳንኤል በደቻ መልካም ምኞታቸዉን ገልጸዋል።

ዘገባው የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ ነው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለ8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መጪውን አዲስ ...
06/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለ8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ የይቅርታ አዋጁን መስፈርት ላሟሉ 8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ይቅርታ የተደረገላቸው የሕግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩና በሕግ በተደነገገው አግባብ የይቅርታ መስፈርትን ማሟላታቸው በክልሉ መንግስት የይቅርታ ቦርድ ተጣርቶ የቀረቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የሕግ ታራሚዎቹ በመደበኛ የይቅርታ ሕግ እና ሌሎች ተጨማሪ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተብለዉ በልዩ ሁኔታ የቀረቡ፤ በማረሚያ ቆይታቸው ስለመታረማቸውና ስለመታነፃቸው ማረጋገጫ የቀረበላቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በዚሁ መሰረት የይቅርታው ተጠቃሚዎች በይቅርታ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት አዋጅ እና አዋጁን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ይቅርታ በማያስከለክሉ ወንጀሎች ተሳትፈው፡-

በማረሚያ ቤት የቆዩ፤ በጤና ችግር፤ በዕድሜ መግፋትና ከሕጻናት ጋር አብረዉ የታሰሩ እንዲሁም ከተፈረደባቸው ሲሶ (1/3) እና ከግማሽ (1/2) በላይ የፍርድ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

የይቅርታ ተጠቃሚ ከሆኑት የሕግ ታራሚዎች መካከል 56ቱ ሴቶች ሲሆኑ፤ 7 መቶ 84 ደግሞ ወንዶች መሆናቸውን አመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑ የሕግ ታራሚዎች የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል በልማት ሊክሱ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ህብረተሰቡም ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች በፈፀሙት ጥፋት የተፀፀቱና በአግባቡ ታርመው የወጡ መሆኑን በመረዳት መልካምና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

በዘይሴ አካባቢ ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር እየተደረገ ያለው ጥረት ቀጣይነት እንዲኖረው  ከመንግሥት ጎን እንደሚቆሙ ነዋሪዎች ገለፁ። ለአካባቢው  የሰላም ግንባታ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የሀገር...
05/09/2026

በዘይሴ አካባቢ ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር እየተደረገ ያለው ጥረት ቀጣይነት እንዲኖረው ከመንግሥት ጎን እንደሚቆሙ ነዋሪዎች ገለፁ።

ለአካባቢው የሰላም ግንባታ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የሀገር ሽማግሌዎች ጥሪ አቅርበዋል።

ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (ደኢፖኮ)

በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዘይሴ ደንብሌ ቀበሌ ጋርዜታ ንዑስ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተወጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት መሪዎችና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት አካሂደዋል።

አለመግባባቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የተቀመጠውን አማራጭ መጠቀም ሰላምን ለማምጣት ብቸኛ መንገድ መሆኑን የሀገር ሽማግሌዎቹ አስገንዝበዋል።

ለዚሁም ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

ህብረተሰቡ ለጋራ ሰላም፣ አንድነትና ወንድማማችነት በፅናት መቆም እንዳለበትም ጠቁመዋል።

መርሀ ግብሩ የተራራቁ የተገናኙበት፤ የተጣሉ የታረቁበት፤ ለቀጣይ የኑሮ መስተጋብራቸው መሰረት የተጣለበት ታሪካዊ ቀን መሆኑን ነዋሪዎች ገልፀዋል።

በአካባቢው ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር እየተደረገ ያለው ጥረት ቀጣይነት እንዲኖረው ከመንግሥት ጎን እንደሚቆሙም አረጋግጠዋል።

ዘገባው የጋሞ ቴሌቭዥን ነው።

"በሠላም ጉዳይ ላይ ስር ነቀል ለውጥ እንድመጣ ሁሉም ቅን ልቦናን ይዞ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት አለበት" ክቡር አቶ አዳማ ትንጳዬ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ...
03/09/2026

"በሠላም ጉዳይ ላይ ስር ነቀል ለውጥ እንድመጣ ሁሉም ቅን ልቦናን ይዞ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት አለበት" ክቡር አቶ አዳማ ትንጳዬ

ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ "ሠላም ለሁሉም ሁሉም ለሠላም" በሚል መሪ ቃል ታላቂ የዕርቀ ሠላም የማጠቃለያ ኮንፍራንስ ተካሂዷል።

በወረዳው በኦርጊሌ ቀበሌ ማዕከል ላይ በተካሄደው በዚሁ ታላቂ መርሃ - ግብር ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፌ - ጉባኤ የተከበሩ አቶ አዳማ ትንጳዬ በዞኑ በሠላም ጉዳይ ላይ ስር ነቀል የሆነ ለውጥ እንድመጣ ሁሉም ቂን ልቦናን ተላብሶ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንዳለበት ገልጸዋል።

ክልሉን የሠላም፣ የመቻቻል እና የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም አፌ - ጉባኤው ጠቅሰዋል።

ክልሉ በሠላም ጉዳይ ላይ በየደረጃቸው የጀመራቸው ተግባራትን ከየትኛውም ጊዜ በላይ አጠናክሮ እንደሚያስቀጥልም ጠቁመዋል።

ክቡር ዋና አፌ - ጉባኤው በዞኑ ለዛሬው በአከባቢው አንፃራዊ ሠላም መስፈን ከክልል ጀምሮ ትልቅ ዋጋ ለከፈሉ አካላት ያላቸውን ትልቅ ክብር፣ ዕውቅናና አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አበነዘር ተረፈ በበኩላቸው የአከባቢው ሠላም እንድፀና ሁሉም ሰው አለያይ ከሆኑት ትርክቶች በመራቅ ለሠላም ዙሪያ ላይ የጀመረውን ዜብ የመቆምእሳበውን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ጠይቀዋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሰሀ ጋርደው ሠላም ከሁሉ በላይ ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን በማመላከት ዛሬ ላይ በአከባቢው የጠብ፣ የጥላቻ እና የመናቆር መንፈስ ተቀርፎ ሁሉም ወደ በመተቃቀፍ ዕርቅ መፈፀሙ ከምንም በላይ ትልቅ ነገር እና የአከባቢው ገጽታ የሚገነባ መሆኑን አብራርተዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግንኙነት ኪታሞ በዚህን ወቅት ቀደም ሲል በአከባቢው ተከስተው የነበሩ ግጭቶቾ ህዝቡ ያልተገባ ዋጋ እንድከፍል እና ትልቅ የስነ ልቦና እና ቁሳዊ ክሳራዎችን እንድያልፍ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።

ለግጭቶች መከሰት መንስኤ እየሆነ ያለው የተፈጥሮ ሀብቶች አጠቃቀም ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች ሠላማዊ በሆነ መንገድ እልባት ላይ መድረስ እንድችሉ በልዩ ትኩረት መሰራቱንና በመሰራት ላይ እንዳለም ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

ቀደም ሲል በህዝቡ መካከል ተዘርተው የነበሩ የጥላቻ እና የተዛቡ ትርክቶች ህዝቡ እንድለያይ ምክንያት ሆኗል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ዛሬ ላይ ሁሉም የሠላም ጉዳይ ያገበኛል ብሎ በመነሳሳቱ ቀድሞ የነበሩ የአንድነትና የአብሮነት እሴቶችን ተመልሰው እንድጠገኑ ህዝቡ የጋራ ተግባቦቶችን በመፍጠሩ እነኝህን መልሶ መጠገን መቻሉንም ዋና አስተዳዳሪው በገለፃቸው አክለዋል።

ከአጎራባች ዞኖች ተሳታፊ የነበሩት የኧሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሐርሻሎ አርካሌ እና የኮንሶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት አፌ - ጉባኤ የሆኑት አቶ ገረመው አያኖ በየበኩላቸው ዛሬ በአከባቢው የተካሄደው ይህ ታላቂ ዕርቅ የመጨረሻ መቋጫ መሆን አለበት ብለዋል።

በአከባቢው የሚስተዋሉ ግጭቶች ማህበረሰቡን እንደማይወክል አበክረው የገለጹት አካላቱ አጎራባች ዞኖች የጀመሩትን የጋራ የሠላም ትስስርን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ እንደዚሁ አመላክተዋል።

በኮንፍራንሱ ላይም የተጋጩ ሰዎች በይፋ በአደባባይ ላይ በመውጣት በፀፀት የይቅርታ እና የምህረት መርሃ - ግብሮችን አከናውነዋል።

በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ ቆላማ ቀበሌያት ተከስቶ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸወላይታ ሶዶ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (ደኢፖኮ) ባለፉት ጊዜያት በጋርዱላ...
03/09/2026

በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ ቆላማ ቀበሌያት ተከስቶ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (ደኢፖኮ) ባለፉት ጊዜያት በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ ቆላማ ቀበሌያት ተከስቶ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ተመላክቷል።

በወረዳው ቆላማ አከባቢዎች ላይ የተፈጠረው አለመግባባት ወደአርስ በእርስ ግጭት በማምረት በሰው ሕይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት በማድረሱ የተጸጸቱት የወረዳው ነዋሪዎች አሁን ላይ የሠላምን ጥቅም በውል በመረዳት የተፈጠረውን ችግር በሠላም ለመፍታት በጋራ እየመከሩ መሆናቸው ታውቋል።

የክልሉ እና የዞኑ መንግሥት በአከባቢው ሠላም ለማስፈን ከሐይማኖት አባቶች እና ባህል መሪዎች ጋር በትኩረት ሲሠራ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ይፋዊ የእርቀ ሠላም ኮንፈረንስ እየተካሔደ ነው።

በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳዬ፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሐ ጋረደውን ጨምሮ ሌሎች የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞኑ አስተዳዳሪ፣ የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች፣ የባህል መሪዎች በመታደም ላይ ናቸው።

ዘገባው የደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ነው።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ሕንጻ ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ በማህበራዊ  ሳይን...
03/09/2026

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ሕንጻ ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ሕንጻ ላይ ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም መንስኤው ያልታወቀ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።

የእሳት አደጋው በአሁን ሰዓት በዪኒቨርሲቲውና በአካባቢው ማህበረሰብ ብርቱ ትግል በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው እና የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም የሶዶ ከተማ እና የዞን አስተዳደር አካላት ላደረጉት ብርቱ ትብብርና ርብርብ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ከልብ የመነጨ ምስጋና ያቀርባል።

የደረሰው የእሳት አደጋ የከፋ እንዳይሆን መላው ማህበረሰብና የግል ድርቶች ሁሉ ላደረጋችሁት ሁሉአቀፍ ትብብር የዩኒቨርስቲው አስተዳደር በድጋሚ ያመሰግናል።

የእሳት አደጋው መንስዔና የጉዳቱን መጠን በሚመለከተው አካል ተጣርቶ ሲቀርብ ለማህበረሰቡ መረጃ የሚንሰጥ ይሆናል።

ሳምንታዊ የትራፊክ አደጋ መረጃባሳለፍነው አንድ ሳምንት 5 የትራፊክ አደጋ መመዝገቡን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አስታወቀ።ወላይታ ሶዶ...
03/09/2026

ሳምንታዊ የትራፊክ አደጋ መረጃ

ባሳለፍነው አንድ ሳምንት 5 የትራፊክ አደጋ መመዝገቡን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አስታወቀ።

ወላይታ ሶዶ ሐምሌ 28/2018 ዓ/ም (ደ.ኢ.ፖ.ኮ) በአደጋውም የ2 ሰው ህይወት ማለፉ ተገልጿል።

ባሳለፍነው አንድ ሳምንት በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ከይርጋጨፌ ወደ ዲላ ከተማ ሲንቀሳቀስ የነበረ ባለ ሁለት እግር ሞተር ሳይክል ተገልብጦ በ1 ሰው ላይ ሞት በ1 ሰው ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ማስከተሉን ከተላከልን መረጃ ማወቅ ተችሏል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዛ ቀበሌ ከሶዶ ወደ አዲስ አባባ ሲንቀሳቀስ የነበረ የጭነት ተሳቢ ተሽከርካሪ እግረኛ ገጭቶ 1 ሰው ላይ የሞት አደጋ ሲያደርስ በ1 ሰው ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት አድርሷል ተብሏል።

በጎፋ ዞን ላሀ ከተማ አስተዳደር ቦትሬ ቀበሌ ከቦትሬ ወደ ላሀ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሞተር ሳይክል ተገልብጦ በ1 ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።

በደቡብ ኦሞ ዞን ዲመካ ከተማ አስተዳደር ከጂንካ ወደ ናጋቶም ሲንቀሳቀስ የነበረ ባለሁለት እግር ሞተር ሳይክል እግረኛ ገጭቶ በ1 ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሱን መረጃው አትቷል።

በዲላ ከተማ አስተዳደር ጪጩ ቀበሌ ከገደብ ወደ ዲላ ሲንቀሳቀስ የነበረ ቅጥቅጥ ተሽከርካሪ እግረኛ ገጭቶ በ1ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት አድርሷል ተብሏል።

ባሳለፍነው አንድ ሳምንት ከደረሱ 5 የትራፊክ አደጋዎች መካከል 3ቱ በባለሁለት እግር ሞተር ሳይክል ሲሆን የአደጋው መንስኤ ተብሎ የተመዘገበው ብቃት ማነስና ጥንቃቄ ጉድለት መሆኑ ከተላከልን መረጃ ማወቅ ተችሏል።

ወንጀልና የትራፊክ አደጋን በጋራ እንከላከል!!

በሪፖርተር ኢትዮጵያ ወንድሙ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ የአድማ ብተናና ቪአይፒ ሻለቆች በሚገኙባቸው አከባቢዎች ግምገማ መድረክ እየተካሔደ ይገኛል።ወላይታ ሶዶ 28/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ)ግምገማው ከሰነዱ በተጨማሪ በግ...
03/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ የአድማ ብተናና ቪአይፒ ሻለቆች በሚገኙባቸው አከባቢዎች ግምገማ መድረክ እየተካሔደ ይገኛል።

ወላይታ ሶዶ 28/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ)

ግምገማው ከሰነዱ በተጨማሪ
በግዳጅ አፈፃፀም፣ በካምፕ አኗኗር፣ በጦር መሣሪያ አያያዝና ቁጥጥር ፣ የተመለከቱ ጉዳዮች ተካተውበታል።

ዎላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀምሯል፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ወላይታ ሶዶ   ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም(ደኢፖኮ...
02/09/2026

ዎላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀምሯል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም(ደኢፖኮ)

የዎላይታ ሶዶ ከተማ አስ/ር ፖሊስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የአፈፃፀም ግምገማ በሶዶ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

በግምገማ መድረኩ የዎላይታ ከተማ አስ/ር ም/ካንቲባ መንግስቱ ትግሮ ፣የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽኔር እና የምርመራ ዘርፍ ኮ/ር ጉራማይለ ጉርኦ፣ ኢንስፔክተር ጣሰዉ ጥላሁን ፣ የከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሠፋ እንዲሁም የከተማና የክ/ከተማ ፖሊስ አዛዦች እና የማኔጅመንት አካላት ተገኝተዋል።

በመድረኩ የተገኙት የከተማዉ ምክትል ከንቲባ እና ሥራ እና ክሎት መምሪያ ሀላፊ መንግስቱ ትግሮ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግራቸው ፣ የፖሊስ አባላት በቁርጠኝነትና በትጋት የተሰጣቸውን ተልዕኮ በመወጣት ውጤታማ ሥራ ማከናወናቸውን ገልፀው ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ መድረኩ ደካማ ጎን ላይ ትኩረት የምናደርግበት ነው አሉ

ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር እና የምርመራ ዘርፍ ሀላፊ ኮማንደር ጉራማይለ በበኩላቸው ግምገማው ለህብረተሰቡ የሚሰጥ አገልግሎት አሰጣጥ ፣የተቋሙ እሴት እና ገጽታ የሚያበላሹ ጉዳዮች ትኩረት እንደምደረግ ገልጸዋል።

‎በቡርጂ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 ዓ/ም የአፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ መሆኑ ተገለፀ፤ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 27/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ) በበጀት ዓመቱ ተግባር አፈፃፀም ላይ በታዩ ጉድ...
02/09/2026

‎በቡርጂ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 ዓ/ም የአፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ መሆኑ ተገለፀ፤

ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 27/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ)
በበጀት ዓመቱ ተግባር አፈፃፀም ላይ በታዩ ጉድለቶችና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስመልከት የተሀድሶ ግምገማ መድረክ እየተደረገ ይገኛል።

‎የቡርጂ ዞን ም/አስተዳዳሪና የፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሉላ ግና በአፈፃፀም ግምገማው ወቅት እንደተናገሩት በጉድለት የታዩ ጉዳዮችን በጥልቀት ማረምና በጥንካሬ የተነሱ ተግባራትን ደግሞ አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኙ ምዕራፍ እንደሆነ አንስተው መድረኩ በፀጥታው ዘርፍ በቀጣይ ለሚሰሩ ሥራዎች ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም ምክትል ኃላፊ ም/ኮ/ር ዶ/ር ጎዓ ካሣ በበኩላቸው መድረኩ ሥራና ተግባርን መሠረት ያደረገ መሆን አለበት ብለው ጉድለት የታየባቸው አከባቢዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ ለማረም እና እንደክልል ወጥ የሆኔ ተቋም ለመገንባት አላማ ያደረገ ግምገማ መሆኑን አመላክተዋል።

‎በ2018 ዓ/ም ተግባር አፈፃፀም ላይ በታዩ ጉድለቶችና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስመልከት የተሀድሶ ግምገማ ዙርያ የተዘጋጀ ሰነድ ክልሉ ፖሊስ ኮምሽን ፎረንስክ ምርመራ ዳይሬክተር ኢ/ር አስራት ቱማቶ አማካኝነት ቀርቦ በስፋት ዉይይት እየተደረገበት ነው።

‎በመድረኩ የቡርጂ ዞን ም/አስተዳዳሪና የፍትህ መምሪያ ኃላፊ ሉላ ግናን ጨምሮ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች በዞኑ ያሉ የሦስቱም መዋቅር አዛዦች፣ዞኑ ማነጅመንት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

Address

Wolaita
S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Regional State Police Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to South Ethiopia Regional State Police Commission:

Shortcuts

Share