04/06/2026
በምርጫው ላይ የታየው የአመራር የተግባርና የአስተሳሰብ አንድነት እና የህዝቡ የነቃ ተሳትፎ በልማት ሥራዎች ላይም ማስቀጠል ያስፈልጋል፦ ወ/ሮ እታገኝ ኃይለማርያም
ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 27/2018 በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር 7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ አፈጻጸም ግምገማ እና ቀጣይ የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎች ላይ ያተኮረ መድረክ ተካሂዷል ።
መድረኩን የመሩት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ እታገኝ ኃይለማርያም እንደተናገሩት 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በተቀመጡ መንትያ ግቦች እንዲጠናቀቅ ያስቻሉ አካላትን አመስግነዋል።
ከንቲባዋ አያይዘውም በድህረ-ምርጫ ወቅት የሚሰሩ ሥራዎች ዙሪያ አመራሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መምራት እንዳለበትም አሳስበዋል።
የከተማ አመራር በሙሉ አቅም ወደ መደበኛ ሥራ መግባት ይገባል ያሉት ከንቲባ ወ/ሮ እታገኝ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ጉዞ፥ ሁሉም የገቢ አማራጮች አሟጥጦ መሰብሰብ ፣ የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ሥርጭት እና ሌሎች ሥራዎች ላይ ልዩ ርብርብ ማድረግ እንዳለበትም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በወላይታ ሶዶ ከተማ በምርጫው ላይ የታየው የአመራር የተግባርና የአስተሳሰብ አንድነት እንዲሁም የከተማ ነዋሪዎች የነቃ ተሳትፎ፥ እየተሰሩ ባሉት ልማት ሥራዎች ላይም ማስቀጠል እንዳለበትም ወ/ሮ እታገኝ አፅንኦት ሰጥቷል ።
በበጀት ዓመቱ ሲሰሩ የቆዩ የፓርቲና የመንግስት መደበኛ ሥራዎች ሳይንጠባጠቡ ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ ያመላከቱት ከንቲባዋ በከተማችን አልፎ አልፎ የሚገነቡ ህገወጥ የቤት ግንባታ መከላከል እንዳለበትና እንዲሁም ያለ ምህረት ማረም እንደሚገባ አሳስበዋል አሳስበዋል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ዘገየ ጳዉሎስ በበኩላቸው 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በተቀመጡ መንትያ ግቦች እንዲጠናቀቅ ያስቻሉ አካላትን አመስግነዋል።
በሁሉም መዋቅር የተቋሙ ዕቅድ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ በመገምገምና በምርጫ ሥራ የተጠቀምንበት አደረጃጀት በልማት ሥራዎች ላይ መድገም እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በወላይታ ሶዶ ከተማ የተጀመሩ የተቀናጀ የኮሪደርና የወንዝ ዳሪቻ ልማት ሥራዎች በፍጥነትና በጥራት መመራት እንደሚገባ ያሳሰቡት ረዳት ፕሮፌሰር በዋናነት በከተማችን በመደበኛና በማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አሳባሰብ ላይ አመራሩ ማተኮር እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በወላይታ ሶዶ ከተማ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰቡት ረዳት ፕሮፌሰር በከተማችን ህዝቡ ያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የዕቅድ አካል ተደርጎ ህብረተሰቡን በማሳተፍ መምራት እንዳለበትም አንስተዋል።
መደበኛ የፓርቲ መዋጮ ፣የፓርቲ ህንጻ ግንባታ ፣ አዲስ የፓርቲ አባላት የማፍራት፥ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የአካባቢው ፀጋ ተኮር በሆነ መልክ መመራት እንደሚገባ እና ኑሮ ዉድነት ለማረጋጋት የተጀመ የስንብት ገበያና ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ተግባር በአመራር ቅኝት መመራት እንደሚገባ ረዳት ፕሮፌሰር አሳስበዋል ።
በመድረኩ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ እታገኝ ኃይለማርያም፥ የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ዘገየ ጳዉሎስ ፣የከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣ የከተማ፥ የክፍለ ከተማ እና የቀበሌ አመራሮች መሳተፍ ችለዋል ።
!