30/12/2025
የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የዚትሮማክስ ዘመቻ የመጀመሪያ ቀን ውሎ ግምገማ እያካሄደ መሆኑን ገለጸ።
ታህሳስ 21/2018:ወላይታ ሶዶ፤ የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የዚትሮማክስ ዘመቻ የመጀመሪያ ቀን ውሎ ግምገማ ሁሉም ሱፔርቫይዘሮች በተገኙበት እያካሄደ መሆኑን ገልጿል ።
መደረኩን የመሩት የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የጤና ጽ/ቤት ሃላፊ ሲ/ር መስከረም በቀለ ሁሉም ሱፔርቫይዘር ሁሉም ቲም ዘመቻ አጀማመርና ከግብዓት፣ ከመዝገብ አጠቃቀም፣ እንደ ችግር ያጋጠሙ ና እንደተፈቱ መቅረብ እንዳለበት አንስተዋል።
አቶ ቆስቴ እማሞ የዞን ጤና መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ በሁሉም ቀበሌ ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተፈቱና ያልተፈቱ መቅረብ እንዳለባቸው እና ለቀጣይ መፈታት እንዳለበት አንስተዋል።