06/01/2026
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳችሁ/አደረሰን!፦ ዕጩ ዶ/ር ደገፉ ዳልኬ
የኪንዶ ኮይሻ ወሰዳ ዋና አስተዳዳሪ ዕጩ ዶ/ር ደገፉ ዳልኬ የገና በዓልን በማስመልከት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ዋና አስተዳዳሪዉ ገና በዓል በክርስቲና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ትርጉም ያለውና ተከታዮች መንፈሳዊ ፣ ማህበራዊ እና ሰብዓዊ ውጤቶችን ያገኙበት በዓል በመሆኑ ይህንን በዓል ትርጉም ባለው ሁኔታ ያከብሩታል ብለዋል።
ገና በዓል የፍቅርና የሠላም መልእክት ለዓለም የተላለፈበትና ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ህዝብ ፍቅሩን ያሳየበት ፣ምህረትን ፣ይቅርታንና ሠላምን ለዓለም ህዝብ ያወጀበት በዓል በመሆኑ ትርጉም ተሰጥቶት እንደሚከበርም አብራርተዋል።
ኢየሱስ ክርስቶስ በሰው ልጆች እና በአምላክ መካከል የነበረውን ጥል አስወግዶ በምህረት፣ በይቅርታ እና በታላቅ ፍቅር ወደ ምድር መምጣቱ የሰላም እና ፍቅር ምሳሌ መሆኑ የሚያንፀባርቅ በዓል ነዉ ስሉም ገልፀዋል፡፡
እኛም በዓሉን ስናከብር ያለው ለሌለው እያካፈልን ፣ የታመሙትን በመጠየቅ፣ የተቸገሩትን በመርዳት የአብሮነት እሴቶችን በማስቀጠል ሊሆን ይገባል ስሉም ዋና አስተዳዳሪዉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የወረዳችን ነዋሪዎች የአከባቢያችንን ሰላም ከፀጥታ መዋቅራችንና ከአመራሮች ጋር በጋራ በመሆን አስፈላጊውን መረጃ በመለዋወጥ በዓሉን ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር አሳስበዋል።
በድጋሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት ፤ የመቻቻል እና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል።
!!