25/10/2025
"በዞኑ በሁሉም ሴክተር መሥሪያ ቤቶች የታቀደውን ዕቅድ፥ በጊዜና በጥራት እንዲከናወን የአመራሩ ቁርጠኝነት ይጠይቃል "ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ
ላሾ ቄራ፣ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም የወላይታ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የዞን ሴክተር መሥሪያ ቤቶች አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ገምግሟል።
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደሪና የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በግምገማው ማጠቃለያ እንደገለጹት በሁሉም ሴክተር የታቀደውን ዕቅድ፥ በጊዜና በጥራት እንዲከናወን የአመራሩ ቁርጠኝነት ይጠይቃል ብለዋል።
በአስፈፃሚ መሥሪያ ቤቶች የሚከናወኑና የተከናወኑ አስተዳደራዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት እንቅስቃሴዎችን በትኩረት የማስፈፀም አቅም ማሳደግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል ።
በሩብ ዓመት አፈጻጸም የታዩ ጉድለቶችን በመለየት በቀጣዩ ዕቅድ ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲከታተሉና እንዲያስፈጽሙ አቅጣጫ ተቀምጧል ።
የዞኑን ህዝብ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ የልማት ፖሊሲዎች መሰረት እቅዶች፤ ፕሮጀክቶችና ፕሮግራሞች ተዘጋጅተው በአገባቡ እንዲተገበሩ የቅርብ ክትትል እንድደረግ አጽንኦት ተሰጥተዋል ።
በየዘርፉ አፈጻጸማቸውን በመገምገም በዞኑ የሚኖሩ ሁሉም ህብረተሰብ የልማቱ እኩል ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የበኩሉን አስተዋኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የጠቆመው ፡፡
በአስተዳደራዊ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተሠሩና እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ከውትሮ በላቀ ሁኔታ ትኩረት ሰጥተው አስፈጻሚ አካላት እንዲመሩና እንዲያስፈጽሙ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።
በትምህርት ፣ በጤና፣ በገቢ፣ በግብርና በፋይናንስ በሴቶችና ሕጻናት፣ በፍትህ ተቋማት እንዲሁም በሌሎች ሴክተር በ1ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ጠንካራ ጎኖችን በማቀጠል ክፍተት ያለባቸውን አፈጻጸም የመለየት ሥራ ሊሠራ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥተዋል ።
የዞኑ ፕላንና ልማት መምሪያ የተዘጋጀ የዞን ሴክተር መ/ቤቶች የ2018 በጀት ኣመት የ1ኛ ሩብ ኣመት አፈጻጸም ሪፖርት በማጠቃለል ለዞኑ አስፈጻሚ አካላት አቅርበዋል ።
በመድረኩ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ፣ ም/አስተዳዳሪ አቶ ተስፋሁን ታዲዮስ፣ የዞኑ ካቢኔን ጨምሮ የዞን አመራሮች ተሳትፈዋል።