Wolaita Zone Youth Association/ ወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • Wolaita Zone Youth Association/ ወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር

Wolaita Zone Youth Association/ ወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር በብቃት እና በጥረት የተካኑ ወጣቶችን ለማፍራት እንተጋለን !

"በሁሉም መዋቅር ትርጉም ያለው የወጣቶች ተሳትፎ እንድረጋገጥ የወጣቶች ማህበር ሚና ወሳኝ ጉዳይ ነው"ብለዋል ወጣት ምህረት ዳናወላይታ ሶዶ፤ታህሳስ 25/2018 ዓም የወላይታ ዞን ወጣቶች ማህ...
03/01/2026

"በሁሉም መዋቅር ትርጉም ያለው የወጣቶች ተሳትፎ እንድረጋገጥ የወጣቶች ማህበር ሚና ወሳኝ ጉዳይ ነው"ብለዋል ወጣት ምህረት ዳና

ወላይታ ሶዶ፤ታህሳስ 25/2018 ዓም የወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የስድስት ወር አፈጻጸምና በቀጣይ ያለው ሥራ አቅጣጫ ዙሪያ ግምገማ አካሂዷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ፌደሬሽን ም/ፕረዚዳንትና የወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር ፕረዚዳንት ወጣት ምህረት ዳና በግምገማው መድረኩ እንደገለጹት በሁሉም መዋቅር የወጣቶች ማህበር ከመቼውም ጊዜ በላይ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሠራ አስረድተዋል ።

የወጣቶች ማህበር በመተዳደሪያ ደንቡና መመሪያና መሠረት በሁሉም መዋቅር በንቃት እንዲሳተፉና ከአቻ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ሥራ እንዲሠሩ ፕረዝዳንቱ አጽንኦት ስጥተዋል።

ማህበሩ በበጀት ዓመት ግማሽ ዓመት አፈጻጸም ላይ የተመዘገቡ መልካም ውጤቶችና የታዩ ክፍተቶችን በመለየት በቀሪ ዕቅድ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ከስምምነት መድረሱን ፕረዚዳንቱ ጠቁመዋል ።

የወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር ም/ፕረዚዳንት ወጣት አረጋኸኝ ብርሃኑ እንደገለጹት በየመዋቅሩ ያሉ የማህበሩ ሰብሳቢዎች የተሰጠውን ኃላፊነት በአገባቡ በመወጣት ውጤታማ ሥራ እንዲሠሩ አሳስበዋል ።

የማህበሩ አሠራሩና ደንቡ በሚፈቅደው መንገድ ሥራቸውን እንዲያከናውኑ ያስታወሱት ም/ፕሬዝዳንቱ በየደረጃው ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ተናግረዋል ።

በግምገማው መድረክ የክልሉ ወጣቶች ፌደሬሽን ም/ፕረዚዳንት ፣የዞኑ፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር የወጣቶች ማህበር ፕረዚዳንቶች ተሳትፈዋል ።

'ጊፋታ' በዓል አከባበር ዙሪያ ከወጣት አደረጃጀቶች እና ከማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነውወላይታ ሶዶ፤ነሓሴ 29/2017 የ2018 ዓ.ም ...
04/09/2025

'ጊፋታ' በዓል አከባበር ዙሪያ ከወጣት አደረጃጀቶች እና ከማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው

ወላይታ ሶዶ፤ነሓሴ 29/2017 የ2018 ዓ.ም የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን በልዩ ድምቀት ለማክበር ከወጣት አደረጃጀቶች እና ከማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በወላይታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የ2018 ዓ.ም የወላይታ ዘመን መለወጫ "ጊፋታ" በዓል "የወጣቶች ሚና በጊፋታ" በሚል መሪ ቃል የንቅናቄ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

"ጊፋታ" በጉጉት እና በከፍተኛ ዝግጅት በየዓመቱ የሚከበር የወላይታ የዘመን መለወጫ በዓል ነው።

ጊፋታ የዕርቅ፣ የሰላም እንዲሁም ለታላቅ የሚሰጥ በዓል ሲሆን በወላይታ ባህል የመጀመሪያው ወርም 'ጊፋታ' ተብሎ ይጠራል።

በጊፋታ በዓል ወጣቶች በሰኔ ወር ማብቅያ አካባቢ ለ" #ጉሊያ” (ደመራ) የሚሆን እንጨት ወደ ጫካ በመዉረድ ቆርጦ በህብረት እየዘፈኑ ጉሊያ ለማቃጠል ወደተወሰነለት ቦታ ይጎትታሉ፣ጊዜዉ ሲደርስ ጉሊያ ያቆማሉ፣” #ዞኪያ” ይጫወታሉ።

በጊፋታ ወቅት ለማገዶ አገልግሎት የሚዉል እንጨት ፈልጠዉ እና ሳር አጭደዉ ይከምራሉ።

በመጨረሻዉም ቀን ከአባቶቻቸዉ ጋር ሥጋ ወደሚታረድበት ደጃፍ ይሄዳሌሉ፣ቅርጫዉ ተከፋፍሎ እስከሚያልቅ የበሬዉን ፊኛ ነፍተዉ እንደ ኳስ ይጫወታሉ፣በመጨረሻም በዕጣ የደረሳቸዉን ሥጋ ከቀርከሃ (ከጭራሮ እንጨትና ሀረግ) በተሠራ አዲስ ቅርጮ (በዘንቢል) አደርገዉ ወደቤት ይወስዳሉ።

ጊፋታ በዓል በወላይታ ህዝብ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅና የማንነት መገለጫ ነው።

በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር ከ1200 በላይ ጧሪ ላጡ፣ አረጋዊያን እና አቅመ-ደካሞች ቤቶችን ለመገንባት እንዘጋጅ፦ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማየወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ...
24/08/2025

በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር ከ1200 በላይ ጧሪ ላጡ፣ አረጋዊያን እና አቅመ-ደካሞች ቤቶችን ለመገንባት እንዘጋጅ፦ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር የሚከናወነው የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መርሃግብር በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በመልዕክታቸው በነገው ዕለት በነሐሴ 19/2017 በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መርሃግብር እንደሚካሄድ ገልፀዋል።

በዚህ መርሃግብር ከ1200 በላይ ቤቶችን ጧሪ ላጡ እናቶች፤ አባቶች፣ አረጋዊያን እና አቅመ-ደካሞች ለመገንባት በሁሉም አከባቢዎች አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

ይህም በክረምት ዝናቡ፣ በበጋው ፀሀዩ ሲፈራረቅባቸው የነበሩ ወገኖቻችን የእፎይታ ህይወትን የሚሰጥ በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የአቅመ-ደካሞችን ቤት በመገንባትና በማደስ ተግባር እናቶቻችንና አባቶቻችን ስሜታቸዉን በደስታ እንባ ሲገልፁ እናያለን ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፥ ይህም ተስፋ የሚያደርግ ማህበረሰብንና ለህዝቡ የሚያስብ ትውልድንም የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ይህ መልካም ተግባር የሰዉ ልጆችን ደስ የሚያሰኝ እና በፈጣሪ ዘንድም የሚያስመሰግን እንደሆነ የተናገሩት ዋና ዋና አስተዳዳሪው፣ በዚህ መልካም ተግባር ላይ ሁሉም መሳተፍ እንዳለበትም አሳስበዋል።

በነገው ዕለት ነሓሴ 19/2017 ዓ.ም የሚከናወነው የአንድ ጀምበር የአረጋዊያንና አቅም ደካሞች ቤቶች ለመገንባት የሁሉም ሐይማኖት ተቋማት፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ዕድሮች፣ በጎ አድራጎት ማህበራት እና ሌሎች ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምረው በነቂስ በመውጣትና ተሳትፎ በማድረግ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ማበርከት እንዳለባቸውም ጥሪ አስተላልፈዋል።

 #2 ቀን ቀረው! በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታበወላይታ ዞን በነሐሴ 19/2017 በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መ...
23/08/2025

#2 ቀን ቀረው! በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ

በወላይታ ዞን በነሐሴ 19/2017 በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መርሃግብር ይካሄዳል።

በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ከ1200 በላይ ቤቶችን ለመገንባትና ለማደስ በቂ ዝግጅት መጠናቀቁን ተገልጿል።

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በወላይታ ዞን የነገ ሰኞ በነሐሴ 19/2017 ዓ.ም በአንድ ጀምበር በርካታ ቤቶችን ለአረጋዊያንና ለአቅመ ደካሞች የመገንባት መርሃግብር ይካሄዳል።

ለዚህ በሁሉም አከባቢዎች አስፈላጊውን ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን በዘህ መልካም እና የህልና እርካታን በሚሰጥ በበጎ ተግባር ላይ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍል መሳተፍ እንዳለበት ጥሪ ቀርቧል፡፡

በዚህ ትልቅ ዓላማ ላይ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች በዕለቱ ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በነቂስ በመውጣት፤ በመሳተፍ አሻራውን እንዲያሳርፍ ጥሪ ቀርቧል።

በጎ ፈቃደኝነት ይህንን ባደርግ ይህንን አገኛለሁ በሚል ስሌት የሚደረግ ተግባር ሳይሆን መለኪያ የሌለው የህሊና እርካታ ይሰጣል፤ ያጎናጽፋል።

በወላይታ ዞን አምና በዚህ ወቅት በብልፅግና ፓርቲ መሪነት እና በህዝቡ ከፍተኛ ተሳትፎ በአንድ ጀምበር የብዙዎች ዕንባን ያበሰ ከ2665 በላይ ቤቶችን መገንባቱን ይታወሳል።

#በጎነት መልካምነት!

ሰውን ለመረዳት ሰው መሆን በቂ ነው!

በወላይታ ዞን የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፍቃድ ተሳታፊ ወጣቶች በዱጉና ፋንጎ ወረዳ የተለያዩ የበጎ ተግባራትን አከናወኑወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 8/2017 ዓ/ም የዳሞት ወይዴ...
14/08/2025

በወላይታ ዞን የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፍቃድ ተሳታፊ ወጣቶች በዱጉና ፋንጎ ወረዳ የተለያዩ የበጎ ተግባራትን አከናወኑ

ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 8/2017 ዓ/ም የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፍቃድ ተሳታፊ ወጣቶች " በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በዱጉና ፋንጎ ወረዳ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን አከናውነዋል።

ወጣቶቹ በዱጉና ፋንጎ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ታካሚዎች ተዘዋውሮ በመጠየቅና ለአቅመ ደካሞች የቤት ግንባታ ሥራ በመስራት የበጎ አድራጎት ስራዎችን አከናውነዋል።

የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መንግስቱ ዮሴፍ ለበጎ ፈቃደኛ ወጣቶቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ በዛሬው እለት ከዳሞት ወይዴ ወረዳ የመጡ ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፍቃድ ተሳታፊ ወጣቶች በዱጉና ፋንጎ ወረዳ በመገኘት የበጎ ተግባር ሥራን ማከናወናቸው የሁሉቱ ወንድም ህዝብ ፍቅርን ፣ ወንድማማችነትን እና አንድነትን እጅጉን የሚያጎላ ነው ብለዋል።

ሁለቱ የወንድም ህዝቦች የተዋሀዱና ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶችን በጋራ የሚቋደስ ወንድማማች ህዝብ መሆናቸውንም ጭምር አቶ መንግስቱ ገልፀዋል።

የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ረዳው ሦራቶ እንደገለጹት በዱጉና ፋንጎ ወረዳ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል በማመስገን በጎነት ወሰን የለለውና የበጎ አድራጎት ተግባሩ ታሪካዊ የወንድማማችነትና የእህትማማችነትን ስሜት ይበልጥ የሚያጎላ ኩነት መሆኑን ገልፀዋል ።

የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ውብሸት መኮንን በበኩላቸው የበጎ ፈቃድ ስራው በዋናነት አንድነታችንንና ወንድማማችነትን የምናጠናክርበት እንዲሁም ወጣት ለወጣት ያለውን ግንኙነት የማጠናከር
በጎ ተግባር ነው ብለዋል ።

በበጎ ሥራ ቦታ የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ፊት አመራሮች ፣ የወረዳው አመራሮች ፣ የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ረዳው ሦራቶ ፣ የዳሞት ወይዴ ወረዳ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ውብሸት መኮንን እና የበጎ ፈቃድ ተሳታፊ ወጣቶች ተገኝተዋል።

 #5 ቀን ቀረው! በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታበወላይታ ዞን በነሐሴ 12/2017 በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መ...
14/08/2025

#5 ቀን ቀረው! በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ

በወላይታ ዞን በነሐሴ 12/2017 በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መርሃግብር ይካሄዳል።

በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ከ1200 በላይ ቤቶችን ለመገንባትና ለማደስ በቂ ዝግጅት መጠናቀቁን ተገልጿል።

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በወላይታ ዞን በነሐሴ 12/2017 ዓ.ም በአንድ ጀንበር በርካታ ቤቶችን ለአረጋዊያንና ለአቅመ ደካሞች የመገንባት መርሃግብር ይካሄዳል።

ለዚህ በሁሉም አከባቢዎች አስፈላጊውን ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን በዘህ መልካም እና የህልና እርካታን በሚሰጥ በበጎ ተግባር ላይ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍል መሳተፍ እንዳለበት ጥሪ ቀርቧል፡፡

በዚህ ትልቅ ዓላማ ላይ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች በዕለቱ ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በነቂስ በመውጣት፤ በመሳተፍ አሻራውን እንዲያሳርፍ ጥሪ ቀርቧል።

በጎ ፈቃደኝነት ይህንን ባደርግ ይህንን አገኛለሁ በሚል ስሌት የሚደረግ ተግባር ሳይሆን መለኪያ የሌለው የህሊና እርካታ ይሰጣል፤ ያጎናጽፋል።

በወላይታ ዞን አምና በዚህ ወቅት በብልፅግና ፓርቲ መሪነት እና በህዝቡ ከፍተኛ ተሳትፎ በአንድ ጀምበር የብዙዎች ዕንባን ያበሰ ከ2665 በላይ ቤቶችን መገንባቱን ይታወሳል።

#በጎነት መልካምነት!

ሰውን ለመረዳት ሰው መሆን በቂ ነው!

በመትከል ማንሰራራት! በወጣቶች አደረጃጀት!በመትከል ማንሰራራት! በወጣቶች አደረጃጀት!
31/07/2025

በመትከል ማንሰራራት! በወጣቶች አደረጃጀት!
በመትከል ማንሰራራት! በወጣቶች አደረጃጀት!

የወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከአበላ አባያ ወረዳ እና ከሆቢቻ ወረዳ ወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመሆን ከካዎ ኮይሻ ወረዳ በ2016 ዓ/ም ለተፈናቀሉ ዘጎችን ለማቋቋም በአበላ አባያ ወረዳ በ...
24/07/2025

የወላይታ ዞን ወጣቶች አደረጃጀት ከአበላ አባያ ወረዳ እና ከሆቢቻ ወረዳ ወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመሆን ከካዎ ኮይሻ ወረዳ በ2016 ዓ/ም ለተፈናቀሉ ዘጎችን ለማቋቋም በአበላ አባያ ወረዳ በጥጣ መንደር ለሚገነባው ቤት የግብዓት ማሰባሰቢያ ሥራ አከናውኑ፤

ወላይታ ሶዶ፣ ሐምሌ 17/2017 (ወዞመኮጉመ)

የወላይታ ዞን በአባላ አባያ ወረዳ ከካዎ ኮይሻ ወረዳ በናዳ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች የሚሠፍሩበት የሰፈራ ጣቢያ ላይ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን የማገዝ ሥራ የክረምት ።

የወላይታ ዞን በአባላ አባያ ወረዳ ከካዎ ኮይሻ ወረዳ በናዳ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች የሚሠፍሩበት የሰፈራ ጣቢያ ላይ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን የማገዝ ሥራዎችን በቦታ ተገኝተው አከናውነዋል ።

በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በ2017/18 ዓ.ም የተጀመረው የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አንዱ የሆነው ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን ወጣቶች በጉልበታቸው መርዳት ሲሆን እነዝህን ጨምሮ በዞኑ በ18 ዘርፎች ከ500 ሺ በላይ ወጣቶች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተገልጿል።

ለአቅም ደካሞችን በመደገፍ በበጎ አገልግሎት ላይ በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ የማህበረሰቡን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመፍታትና የበጎ ፈቃደኝነት ባህል ለማጎልበት ዓላማ ያደረገ እንደሆነ ተጠቁሟል ።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜጎችን አብሮነት፣ መተሳሰብ፣ ሁለንተናዊ ትብብርና መተጋገዝ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው በመገንዘብ በርካታ ወጣቶች በክረምት ወራት ጊዚያቸውን በበጎ ዓላማ በማዋልና አቅም ደካሞችን የመደገፍ ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ተጠቁሟል ።

የዞን ወጣት አደረጃጀት ከሁሉም መዋቅር ወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር ቀጣይነት ያለው ድጋፍ የማድረግ ሥራ እንደሚሠራ ተገልጿል ።

ከዞንና፣ ከሁለቱ መዋቅር የተወጣጡ ወጣት አደረጃጀት አመራሮችና አባላት በበታው ተገኝተው ለቤት ግንባታ የሚሆኑ ግብአት ከማቅረብ አኳያ በጉልበታቸው የማገዝ ሥራ ተሠርተዋል ።

አምና 2016 ዓ.ም በካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌሐምሌ ወር ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተፈጠረ የመሬት መንሸራተት እና ናዳ የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል።

የዞኑ ወጣት አደረጃጀቶች እንደገለፁት ወጣቶች በጎነት ከፈጣሪ በረከትን የሚያስገኝ ተግባር በመሆኑ በሁሉም መዋቅር ያሉ ወጣቶችና የበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች በዚህ ተግባር በቦታው በመገኝት በጉልበታቸው መሳተፍ እንድችሉ የዞን ወጣቶች ክንፊ ጽ/ቤት ጥሪ አቅርበዋል ።

በቦዲቲ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል።በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል።“የዲጅ...
18/07/2025

በቦዲቲ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

“የዲጅታል ኢትዮጵያ” ግቦች በማሳካት ሂደት ፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ ትልቅ ድርሻ አለው። ፋይዳ የብሄራዊ መታወቂያ አሰጣጥን ማሳካት በርካታ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል፤

• የዲጅታል ሲስተም ተጠቃሚ ህዝብ መፍጠር፤
• ኢኮኖሚያችንን ዲጅታል ማድረግ፤
• የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ማቀላጠፍ፤
• መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ፣
• የተጀመረውን ሪፎርም የተሟላ ማድረግ፣
• የተለያዩ ህገወጥ ተግባራትን መቆጣጠር፣
• አስተማማኝ ሰላም ማስፈን፣
• የንግድ ስርአቱን እና የገቢ አሰባሰብ ስርአታችንን ዘመናዊ ማድረግ ተጠቃሾቹ ናቸው።

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ህብረተሰቡ በተጨባጭ ተጠቃሚ እንዲሆን ልዩ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል፦ ዶ/ር አማረ አቦታወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 11/2017 በወላይታ ዞን የ2017 የክረምት ወራ...
18/07/2025

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ህብረተሰቡ በተጨባጭ ተጠቃሚ እንዲሆን ልዩ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል፦ ዶ/ር አማረ አቦታ

ወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 11/2017 በወላይታ ዞን የ2017 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ያለበት ደረጃ የዞኑ ዐቢይ ኮሚቴ ገምግሞ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር አማረ አቦታ የዘንድሮ የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በተዘጋጀው ዕቅድ ላይ መግባባት በመፍጠር ወደ ተግባር መግባቱን አስታውሰዋል።

ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚታይ፣ የሚለካ ዕቅድ አዘጋጅቶ ወደ መግባት እንዳለበት ያሳሰቡት ኃላፊው፥ የታቀዱ ተግባራትን ለማሳካትና ለመፈጸም ባለድርሻ አካላት መቀናጀት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠቃሚ የሚሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን በተገቢው ሁኔታ መለየት አለበት ያሉት ኃላፊው፥ የግብዓት አቅርቦት የማሟላት ስራ መሰራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የኢትዮ-ኮደርስና የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) አብዛኛው ወጣቱ ክፍል ለራሱ እንዲጠቀምና ሌላውን እንዲሳተፍ ማድረግ ይጠብቅበታልም ብለዋል።

የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን ከአረንጓዴ አሻራ፣ ከኮሪደር ልማትና ከአካባቢ ጥበቃ ጋር አስተሳስሮ መሰራት እንደሚገባ ያመለከቱት ኃላፊው፥ ለዚህም ባለድርሻ አካላት መቀናጀት አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በቤት ግንባታና እድሳት ላይ ህብረተሰቡ በተጨባጭ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መሰራት ያስፈልጋል ያሉት ኃላፊው፥ በየቀበሌው ተግባራዊ እንዲሆን ያለውን አቅም መጠቀም ያስፈልጋል ብለዋል።

በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎችን የመጀመሪያ ዙር በተዘጋጀው ሰፈራ ቦታ ላይ መልሶ ለማስፈር ልዩ ርብርብ ማድረግ እንደሚጠይቅ በመገለጽ፥ የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመደገፍ ሁሉም የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበትም አሳስበዋል።

በግብርና ዘርፍ ሰብል የተጎዳባቸው አከባቢዎች ዘር በማመቻቸት መዝራት ይገባል ያሉት ኃላፊው፥ በጤናው ዘርፍ ህብረተሰቡ ደም እንዲለግሱ ግንዛቤ ስራ መሰራት ያስፈልጋልም ብለዋል።

የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት በሁሉም አከባቢዎች ላይ ትኩረት መሰጠት እንዳለበት ያሳሰቡት ኃላፊው፥ የትምህርት ቁሳቁስ የማሰባሰብ ስራ መጀመር እንዳለበትም አመላክተዋል።

እንደዞን ዘንድሮ በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እንዲሆኑ በሁሉም ዘርፍ የታቀዱ ተግባራት በልዩ ትኩረት መምራት እንዳለባቸውም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የወላይታ ዞን ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ቶማስ የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰራት በልዩ ትኩረት መምራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የዐቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ ተግባራት እየገመገመ መምራት እንዳለባቸው ያሳሰቡት አቶ መስፍን፥ የተደራጀ የሰራ ሪፖርት በየወቅቱ መዘጋጀትና ለሚመለከታቸው አካላት መደረስ እንዳለበትም አሳስበዋል።

ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን የግብዓት አቅርቦት ማሟላት እንደሚገባም አመላክተዋል።

ለተግባራዊነቱና ውጤታማነቱ ቅንጅታዊ አሠራር መጠናከር እንዳለበትም አንስተዋል።

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሁሉም ሰው በመሳተፍ የራሱን አሻራን ማበርከት ይገባል፦ዶ/ር አማረ አቦታወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 4/2017 በወላይታ ዞን "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የክረም...
11/07/2025

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሁሉም ሰው በመሳተፍ የራሱን አሻራን ማበርከት ይገባል፦ዶ/ር አማረ አቦታ

ወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 4/2017 በወላይታ ዞን "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ ተጠናቀቀ።

ማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር ለማከናወን ጠንካራ ዕቅድ መዘጋጀት እንዳለበት አሳስበዋል።

የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባርን ለማሳለጥ የታቀደው ዕቅድ የአከባቢ ነባራዊና ተጨባጭ ሁኔታን ያገናዘበ መሆን እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

ዕቅዱን ለመተግበር በተባበር ክንድ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች ማሳተፍ እና ባለድርሻ አካላት በንቃት እንዲሳተፉ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

በመጪው ነሐሴ ወር "በአንድ ጀንበር" የብዙዎች እምባን ያበሰ የአቅም ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶች ለመገንባት ከወዲሁ መዘጋጀት ይጠብቅብናል ብለዋል።

በየአካባቢው የሚገኙ ሁሉም ወጣቶች እንዲሳተፉ የመንቀሳቀስ ስራ መሰራት ያስፈልጋል ያሉት ኃላፊው፥ ወጣቶችና ህዝቡ የሰላም ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት።

ማህበራዊ ሚዲያዎችን ለገዢ ትርክት ግንባታ፣ ለበጎ ዓላማ፣ የህዝቡን አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ መጠቀም እንዳለበትም አሳስበዋል።

የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ም/ኃላፊና የወጣት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማርቆስ ማቴዎስ በጎ ፈቃድ የሚሰሩ ወጣቶች በተገቢው ሁኔታ መለየት ያስፈልጋል ብለዋል።

በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ተጠቃሚ የሚሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መለየት ያስፈልጋል ያሉት ያሉት አቶ ማርቆስ፥ የተለዩት ተጠቃሚ ለማድረግ በቂ ዝግጅት መደረግ እንዳለበትም አሳስበዋል።

በዐቢይ ኮሚቴና የቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ ለተግባር ማነቆ የሚሆኑ ጉዳዮች እየተገመገመ መምራት ያስፈልጋል ያሉት አቶ ማርቆስ፥ ኮሚቴዎች በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ተግባራትን እየገመገሙ መምራት አለባቸው ብለዋል።

እንደክልል በወጣቶች ተሳትፎ "አንድ ተራርን ለማልማት" መታቀዱን የገለጹት አቶ ማርቆስ፥ ለዚህም በሁሉም አከባቢዎች ዝግጅት እንዲደረግ አሳስበዋል።

የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ም/ኃላፊ እና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታምራት ከበደ በጎ ስራ የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ለማዳን ያለመ በመሆኑን ሁሉም አካላት በንቃት እንዲሳተፉ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የበጎ ፈቃድ ተግባርን ለማሳካት በዐቢይ ኮሚቴ ደረጃ እየተገመገመ መምራት እንዳለበት ያሳሰቡት አቶ ታምራት የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሠራር መጠናከር እንደሚገባም አመላክተዋል።

ክልላዊ የወጣቶች አደረጃጀት አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ተጀመረወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 2/2017 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች አደረጃጀት "ወጣቱ ትውልድ ሀገርንና ተ...
10/05/2025

ክልላዊ የወጣቶች አደረጃጀት አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ተጀመረ

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 2/2017 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች አደረጃጀት "ወጣቱ ትውልድ ሀገርንና ተፈጥሮን የመጠበቅና የመንከባከብ ታራካዊ ኃላፊነት ይወጣል" በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የ2017 አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በይ አስጀምሯል።

በማስጀመሪያው መርሃግብር ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት አማኑኤል ሳሙኤል ወጣቱ ትውልድ ሀገርን እና ተፈጥሮን የመጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነትን መውጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

በመቀናጀት፣ በመተባበርና እጅ ለእጅ ተያይዘን በመስራት በሀገራችን ብልፅግና ጉዞ ላይ አሻራን ማሳረፍ ይጠብቅብናልም ብለዋል።

መርሃግብር እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በተቀናጀና በተደራጀ አገባብ በንቅናቄ መመራትና መጠናከር እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ሚካኤል ዋዳ ችግኝን መትከል ብቻ ሳይሆን የመጠበቅና የመንከባከብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።

የሚተከሉ ችግኞች በብዛት በወጣቶች ስብዕና መገንቢያ አከባቢዎች መሆን እንዳለበት ያሳሰቡት ወጣት ሚካኤል የሚንተክላቸው ችግኞች ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው መሆን እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ለውጤታማነቱ ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት መሰራት ያስፈልጋል ያሉት ወጣት ሚካኤል በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ማሳተፍ እንደሚገባም አመላክተዋል።

ዛሬ የተጀመረው ክልላዊ የወጣቶች አደረጃጀት የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ሁሉንም ወጣቶችን ባሳተፈ መልኩ መሆን እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል።

የክልሉ ወጣቶች ፌዴሬሽን ም/ፕሬዚዳንት ወጣት ምህረቱ ዳና በበኩላቸው ወጣቱ በልማት በማሳተፍና ሰላምን ለማጽናት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የተተከለውን በመንከባከብ የማሳደግ ኃላፊነት አለብን ያሉት ወጣት ምህረቱ የተከለውን እስከሚያድግ ድረስ የመጠበቅና የመንከባከብ ስራ መሰራት እንደሚገባም አመላክተዋል።

ይህ መርሃግብር በዞኖች፣ በወረዳና ከተማ አስተዳዳሮች ወጣቱን በማሳተፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።

Address

Ligaba
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Zone Youth Association/ ወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Wolaita Zone Youth Association/ ወላይታ ዞን ወጣቶች ማህበር:

Share