15/11/2025
ሰሞኑን ጂንካ ላይ የታየው ወረርሽኝ የኢቦላ ዝርያ ግን ከኢቦላም የከፋ መሆኑ ተረጋገጠ
ወረርሹኙ ማርበርግ የተሰኘ ቫይረስ ( Marburg virus) የሚያስከትለው በሽታ መሆኑን የኢትዮጵያ ጤና ሚንስተር አረጋግጧል።
የአሜሪካው የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ማዕከል (CDC) ቫይረሱን “እምብዛም የማይከሰት ግን በጣም የከፋ በማለት ገልፆት ገዳይ ሊሆን ይችላል” ብሏል።
በሽታው ከ ‘ ግብጿ የፍራፍሬ ለሊት ወፍ’ ( Egyptian fruit bat) የሚመጣ ሲሆን በህመሙ ከሚያዙ ሰዎች ግማሽ ያህሉ ህይወታቸው እንደሚያልፍ ጥናቶች ያሳያሉ።
በሽታዉ የሚተላለፈው በሰውነት ፈሳሽ ንክኪ ፤ ህክምናው ደግሞ እረፍትና ፈሳሽ አብዝቶ መውሰድ (የእገዛ ህክምና) መሆኑ ተዘግቧል።
ህብረተሰቡ የቫይረሱን መተላለፊያ መንገድ በመረዳት አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል።
የበሽታው መተላለፊያ መንገዶች እና ማዳረግ ስለሚገባን ጥንቃቄ ጤና ሚኒስቴር ያወጣውን መረጃ ከላይ ተያይዟል።