በጀግንነት መጠበቅ በስብዓዊነት ማገልገል

በጀግንነት መጠበቅ በስብዓዊነት ማገልገል ወንጀልን በጋራ እንከላከል

29/05/2026

''ማዕረግ የህዝብን ደህንነት በታማኝነት የመጠበቅ ትልቅ አደራ ነው''-ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የቆይታ ጊዜያቸውን ላጠናቀቁ፣ በዲሲ...
29/05/2026

''ማዕረግ የህዝብን ደህንነት በታማኝነት የመጠበቅ ትልቅ አደራ ነው''-ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የቆይታ ጊዜያቸውን ላጠናቀቁ፣ በዲሲፕሊናቸውና በስራ አፈጻጸማቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራርና አባላት የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት በድምቀት አካሂዷል።

በዚህ ደማቅ መርሐ-ግብር ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር፣ የፍትህ፣ ፀጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱሰላም አህመድ፣ ወ/ሮ ሹክሪ አብዱረህማን የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ባለስልጣን ኃላፊ፣ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ፣ የሁርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አመራሮች፣ የጠቅላይ መምሪያው ምክትል ኮሚሽነሮች እና በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ላይ የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

በመርህ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ፣ ዛሬ በትከሻችሁ ላይ ያረፈው ማዕረግ የደከማችሁበት የሙያ ስኬት መገለጫ ብቻ ሳይሆን፣ ለድሬዳዋ ህዝብ ሰላምና ደህንነት ይበልጥ እንድትተጉ የተሰጣችሁ ታላቅ የህዝብና የሀገር አደራ ነው ብለዋል።

ማዕረግ የህዝብን ደህንነት በታማኝነት የመጠበቅ ትልቅ አደራ ነው ያሉት ክቡር ከንቲባው የከተማችንን ልማትና ኢንቨስትመንት በፅኑ መሰረት ላይ ለማቆም አስተማማኝ ፀጥታ መኖሩ ወሳኝ በመሆኑ፣ ከአዲሱ ማዕረጋችሁ ጋር የሚመጣውን ከባድ ኃላፊነት በቅንነትና በቁርጠኝነት እንድትወጡ አሳስባለሁ ብለዋል።

ማዕረግ በቆይታ ብቻ ሳይሆን በላቀ ዲሲፕሊን የሚገኝ ክብር ነው ያሉት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ በበኩላቸው የማዕረግ ዕድገት ዝም ብሎ በጊዜ ሂደት የሚሰጥ ስጦታ አለመሆኑን አስገንዝበዋል።

ኮሚሽነሩ አክለውም ዛሬ ለዚህ ክብር የበቁ የአመራርና የአባላት ከማዕረጉ ጀርባ ያለውን የህዝብ አገልጋይነት ስሜትና ከባድ ኃላፊነት በመረዳት፣ በየተሰማሩበት የስራ መስክ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በግንባር ቀደምትነት ሊሰለፉ እንደሚገባ ጥብቅ መመሪያ አስተላልፈዋል።

በዚህ መርሃ-ግብር ላይ የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት የሰራዊቱን አቅም በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና ለነበራቸው አካላት እውቅና የተሰጠ ሲሆን በስልጠና ሂደት ላይ ለነበሩ አመራሮችና አባላት ስልጠናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ላበረከተው ለሁርሶ ኮንተንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የምስጋና እና የላቀ የእውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል።

በአጠቃላይ በዚህ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ 796 የሚሆኑ የፖሊስ አባላትና አመራሮች የማዕረግ ሽግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በከተማዋ አስተማማኝ ሰላምን ለማስፈን ቃላቸውን በማደስ ስነ-ስርዓቱ በድል ተጠናቋል።

የፖሊስ አባላት የንግድ ሱቅና የመኖሪያ ቤት እድሳት አደረጉ።‎‎የቤንች ሸኮ ዞን ፖሊስ መምሪያ እና የሚዛን አማን ከተማ  አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አመራሮችና አባላት ለአብሮነትና ለወገን...
28/05/2026

የፖሊስ አባላት የንግድ ሱቅና የመኖሪያ ቤት እድሳት አደረጉ።

‎የቤንች ሸኮ ዞን ፖሊስ መምሪያ እና የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አመራሮችና አባላት ለአብሮነትና ለወገን ደራሽነት ያላቸውን አጋርነት በተግባር አሳይተዋል።

‎የፖሊስ አመራርና አባላት ለ11 ዓመታት በፖሊስነት ሕዝብንና አገሩን በታማኝነት አገልግሎ በድንገተኛ ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ለተለየው ለቀድሞው ባልደረባቸው ዋና ሳጅን ጥላሁን ዳይመራ ቤተሰቦች ታላቅ የበጎ አድራጎት ሥራ አከናውነዋል።

‎ለቤተሰቡ ዘላቂ የገቢ ምንጭ የሚሆን የ3 በ 3 ሜትር ስፋት ያለው ሱቅ በመስራት እና ሸቀጣ ሸቀጦችን በማሟላት ለልጆቹ እናት ስራ እድል ተፈጥሮ የኩሽና እና የአንድ ሰርቪስ ቤት የማደስ ሥራ ተከናውኗል።

‎የፖሊስ አባላት አቅማቸው የፈቀደውን በማዋጣት ወደ 100 ሺህ ብር የሚጠጋ ገንዘብ እጅ በእጅ በመሰብሰብ ለሥራው አውለዋል።

‎ይህ የፖሊስ አባላት ተግባር የአንድነት፣ የሙያዊ አጋርነትና የወገንተኝነት ታላቅ ማሳያ ከመሆኑም በላይ ለሁሉም አርአያ የሚሆን ተግባር ነው።

👉የፖሊስ እውነተኛ ጥንካሬ በሕዝቡ መካከል ባለው እምነትና ክብር ላይ ይመረኮዛል።"​"👉ህግ አስከባሪ ማለት የሰላም ዘበኛ፣ የፍትህ ጋሻ እና የህብረተሰቡ የደህንነት ዋስትና ነው።"​"👉እውነተ...
27/05/2026

👉የፖሊስ እውነተኛ ጥንካሬ በሕዝቡ መካከል ባለው እምነትና ክብር ላይ ይመረኮዛል።"
​"👉ህግ አስከባሪ ማለት የሰላም ዘበኛ፣ የፍትህ ጋሻ እና የህብረተሰቡ የደህንነት ዋስትና ነው።"
​"👉እውነተኛ ፖሊስ ወንጀልን ከመከላከል ባለፈ፣ በህዝቡ ልብ ውስጥ የሰላም ተስፋን ይዘራል።"
​"👉የህዝብ ደህንነት የጋራ ስራ ነው፤ ፖሊስ ደግሞ የዚህ ታላቅ ትብብር መሪ ምሰሶ ነው።"

በሚዛን አማን ከተማ በተከናወነ የተቀናጀ ኦፕሬሽን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ንብረቶች ከተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ግንቦት 16 ቀን 20...
27/05/2026

በሚዛን አማን ከተማ በተከናወነ የተቀናጀ ኦፕሬሽን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ንብረቶች ከተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ

በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወነ የተቀናጀና ስኬታማ የኦፕሬሽን ስራ፣ የወንጀል ድርጊት ፈጽመዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ከተለያዩ የቴክኖሎጂ ንብረቶች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የከተማው ፖሊስ አስታወቀ።

በጥብቅ ክትትል ከተያዙት ንብረቶች መካከል ሶስት ዘመናዊ ስማርት ቲቪዎች (Smart TVs) እና አንድ ስማርት ስልክ ይገኙበታል።

ፖሊስ እንደገለጸው፣ ይህ መጠነ-ሰፊ ኦፕሬሽን ሊከናወን የቻለው ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥራት ያለው ጥቆማ እና የወንጀል መከላከል ክፍሉ ባደረገው ተከታታይ ጥብቅ ክትትል ነው። የሌባ ቡድን አባላት ናቸው ተብለው የተጠረጠሩት ግለሰቦች፣ ማህበረሰቡን በማስመረር በተለያዩ መኖሪያ ቤቶችና ግለሰቦች ላይ የሰረቋቸውን እነዚህን ውድ የኤሌክትሮኒክስ ንብረቶች ለመሸጥ በድርድር ላይ እያሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ምናሉ ታደሰ በበኩላቸው በወቅታዊው የጸጥታ ሁኔታና በህዝብ ተሳትፎ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ጥሪ አስተላልፈዋል።

ኮማንደሩ እንዳሉት የከተማችንን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ማስጠበቅ የሚቻለው በፖሊስና በህብረተሰቡ መካከል ጠንካራና የማይበገረ የጋራ ትብብር ሲኖር ብቻ ነው። ዛሬ የተመዘገበው ስኬት የዚሁ ህዝባዊ አጋርነት ማሳያ ነው። ወንጀልን ለመከላከልና የህዝባችንን የሀብትና የንብረት ዋስትና ለማረጋገጥ ሌሊትና ቀን እየሰራን እንገኛለን።

ህብረተሰቡ በየአካባቢው የሚያያቸውን ማናቸውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎች፣ እንግዳ የሆኑ ሰዎችንና ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ወዲያውኑ ለፖሊስ በመጠቆም እያደረገ ያለውን አኩሪ ተሳትፎ ይበልጥ ሊያጠናክር ይገባልም ብለዋል።"*

ኮማንደር ምናሉ አክለውም፣ ፖሊስ የከተማዋን ሰላምና ፀጥታ ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ ምንም ዓይነት ምህረት እንደማያደርግና ህግ የማስከበር ስራው ወደኋላ እንደማይል አስምረውበታል።

የሚ/አ/ከ/አ/ፖ/ማ/አ/ወ/መ/ማስተባበሪያ ኃላፊ ዋና ሳጅን ማርቆስ አለማዬው በጉዳዩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ የከተማዋን ሰላምና ጸጥታ አስተማማኝ ለማድረግና የህዝብን ንብረት ከሌቦች ለመጠበቅ የተጀመረው ይኸው የተቀናጀ የኦፕሬሽን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

ወንጀለኞች በማንኛውም ሰዓትና ቦታ ተደብቀው ሊሰሩ እንደማይችሉና ፖሊስ ስምሪቱን ይበልጥ እያሰፋ እንደሚሄድም ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር በዋሉት ተጠርጣሪዎች ላይ ፖሊስ ጥልቅ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝና የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን በማደራጀት በቀጣይም ጉዳያቸው በህግ አግባብ ታይቶ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ለፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ከፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የአፍሪካ እና 3ኛዋ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነቸውን  አዲስ አበባን የሚያገለግለዉ  የፖሊስ ሰራዊት ከዘመኑ ጋር የዘመነ  እንዲሆን ውጤታማ ስራ እየተሰራ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ ...
27/05/2026

የአፍሪካ እና 3ኛዋ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነቸውን አዲስ አበባን የሚያገለግለዉ የፖሊስ ሰራዊት ከዘመኑ ጋር የዘመነ እንዲሆን ውጤታማ ስራ እየተሰራ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

AMN ግንቦት 19/2018 ዓ.ም

የአፍሪካ እና 3ኛዋ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነቸውን አዲስ አበባን የሚያገለግለዉ የፖሊስ ሰራዊት ከዘመኑ ጋር የዘመነ እንዲሆን ውጤታማ ስራ እየተሰራ ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት ዛሬ በየደረጃው የሚገኙ የከተማችን የፖሊስ አመራሮች እና አባላት ያካሄዱት በ100 ቀናት እቅድ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች ማጠቃለያ ግምገማ ላይ ተገኝቼ በርቱ ብያለሁ ብለዋል፡፡

በሪፎርም በተያዙት በመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ባለፉት 100 ቀናት እቅድ ትግበራዎች፣ እያደገችና እየዘመነች ከመጣችው የአፍሪካ እና 3ኛዋ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነቸው መዲናችን አዲሰ አበባን የሚያገለግል የፖሊስ ሰራዊት ገለልተኛ ሆኖ በህግ እና በህዝብ የተጣለበትን አደራ በአግባቡ የሚወጣ ተቋም ሆኖ እንዲጠናከር፤ በሥነምግባር ክብሩ የተጠበቀ፣ በሰው ሃይል አቋም ብቁ የሆነና በአሰራርም ከዘመኑ ጋር የዘመነ እየሆነ እንዲሄድ ውጤታማ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩና ነዋሪው ህዝብ አንዳንዶች የሚፈጽሙትን የተቋሙንና የሰራዊቱን ስም የሚያጠለሹ ስህተቶችን እያረማችሁ፤ ጥሩ የሚሰሩትን እያበረታታችሁ ለምትሰሩት መልካም ስራዎች በርቱ እያለ ይደግፋችኋል ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ላብ ደምን ያድናል
25/05/2026

ላብ ደምን ያድናል

24/05/2026

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት የተከናወነው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸው ዕጩ መኮንኖች ምረቃ ሥነ ሥርዓት በምስል
23/05/2026

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት የተከናወነው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸው ዕጩ መኮንኖች ምረቃ ሥነ ሥርዓት በምስል

"የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዓለም የደረሰበት የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመታጠቅ አቅሙን አሳድጓል" የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠​ አ...
22/05/2026

"የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዓለም የደረሰበት የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመታጠቅ አቅሙን አሳድጓል" የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
​ አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዓለም የደረሰበት የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመታጠቅ አቅሙን አሳድጓል ያሉት 117ኛው የኢትዮጵያ ፖሊስ ምስረታ ቀንን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የተካሄደ ባለው በፓናል ውይይት ላይ ነው።


117ኛው የኢትዮጵያ ፖሊስ ምስረታ ቀን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በፓናል ውይይት እየተከበረ ነው።

በዚህ ወቅት ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደምበላሽ ገ/ሚካኤል፤ የሀገር ድምበር ተከብሮ ዜጎች በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ ፖሊስ ትልቁን ሚና እየተወጣ ነው።

ተቋሙ በባሕላዊ አስተሳበብ የሚመላለስ አይደለም ያሉት ክቡር ኮሚሽነር ጀነራሉ ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል እና የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ ከአፍሪካ ብቁና አስተማማኝ ቁመና የገነባ ተቋም ሆኗል ብለዋል።

በሰው ኃብት ፣ በቴክኖሎጂ እና በተቋማዊ አደረጃጀት የሄደበት ርቀት ከለውጡ ወዲህ ከታዩ የሪፎርም ትግበራ ውጤቶች ተቋሙን አንዱ ማሳያ ያደርገዋል ሲሉም አንስተዋል።

በወንጀል መከላከል እና ተያያዥ ፖሊሳዊ ትግበራዎች የዲጂታል ሥርዓቶችን ወደ ሥራ በማስገባት የፖሊሳዊ ሥራዎችን ማዘመን መቻሉን የጠቆሙት ኮሚሽነር ጀነራል ስማርት ፖሊስ ጣቢያዎችን ጨምሮ ዲጂታል ፎረንሲክ ላባራቶሪዎችን አደራጅቷል ነው ያሉት።

የዲጂታል ማዘዣ ማዕከል ( CCC,) የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ( EFP app,) የድሮን ኃይል እና digital communications ወደ ትግበራው ከገቡት መካከል ናቸው።

በወንጀል ምርመራ፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ሽብርተኝነት ፣ የህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ውጤታማ ሥራ አከናውኗል ብለዋል።

ዛሬ የሳይበር ወንጀሎችን ፣ የፋይናንስ ማጭበርበሮችን እና የተወሳሰቡ ዲጂታል ዐሻራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ በመተንተንና በማስረጃነት በማቅረብ ረገድ ተቋሙ በአፍሪካ ውስጥ ግንባር ቀደም የቴክኖሎጂ ባለቤት መሆን ችሏል።

በዚህም የወንጀለኞችን መደበቂያ በማጥበቡ ረገድ የማይተካ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ጥቂት ያደጉ ሀገራት የታጠቁትን ትጥቅ በመታጠቅ ከዘመኑ ጋር ዕኩል እየተራመደ እንደሚገኝም አመልክተዋል።

ይህም በቴክኖሎጂ ሥርዓት የታገዘ የወንጀል መከላከል አቅምን የሚያሳድግለት ከመሆኑም በላይ የትኛውንም የፀጥታ ስጋት ለመቀልበስ የሚያስችለው ነው።

አሁናዊ ተቋማዊ ቁመናው ከለውጡ ማግስት ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ትኩረት የመጣ መሆኑን አንስተው፤ የአመራር ቁርጠኝነት እና የአባላቱ ትጋት ከፍተኛ ሚና እንደነበረውም አስገንዝበዋል።

በፓናል ውይይቱ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ፅሑፎች የሚቀርቡ ሲሆን የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ ፖሊሳዊ አመራሮችን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

Address

Mizan Teferi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጀግንነት መጠበቅ በስብዓዊነት ማገልገል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share