Enebsie communication affairs Office

Enebsie communication affairs  Office to see a society with rich information and all rounded active particpation for a better understanding on fundamental regional and country level affair for

Playing a great role in government communication information for a successful information exchange with in a society, to enhance the awareness of the people on the fundamental policies, strategies, plans and programs for a better step of succession our vision by strong collaboration.

የመንግስት ተቋማትን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ ለወረዳ የመንግስት ተቋማት የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ባለሙያዎች የማነቃቂያ ስልጠና ለ2 ተከታታይ ቀናት ሰሞኑን በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ...
19/03/2021

የመንግስት ተቋማትን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ ለወረዳ የመንግስት ተቋማት የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ባለሙያዎች የማነቃቂያ ስልጠና ለ2 ተከታታይ ቀናት ሰሞኑን በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት አማካኝነት ተሰጠ፡-
በጽ/ቤቱ የልማት እቅድ ክትትልና ግምገማ የስራ ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ውብአዝመራ ወርቁ እንዳሉት የዚህ ስልጠና ዋነኛ አላማ የመንግስት ተቋማትን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ የመረጃ ልውወጥ እና የሪፖርት ግንኙነትን በማጠናከር የዘርፉን ባለሙያዎች ብቃትና ክህሎት በስልጠና ማሳደግ ታስቦ ነው ብለዋል፡፡
የስራ ቡድን መሪዋ ከዚሁ ጋር አያይዘው እንዳሉት የተቋማትን የመረጃ አሰጣጥ ስርአት በማዘመን ተግባራትን በእቅድ መሰረት አካተው እንዲሰሩና የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ወቅቱን ጠብቀው ለሚመለከተው አካል እንዲያደርሱና የተሻለ አሰራርን ለማምጣት ይህ ስልጠና ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል፡፡
በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የመንግስት ተቋማት የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ባለሙያዎች በበኩላቸው ስልጠናው መሰጠቱ ለስራችን ውጤታማነት ግብአት ሊሆን ስለሚችል እና በተቋማት ላይ የሚያጋጥሙ የአሰራር ክፍተቶችን ለማስተካከል እና ለማረም አጋዥ ስለሆነ በቀጣይነት ስልጠናው ወቅቱን ጠብቆ ሊሰጥ ይገባል ብለዋል፡፡
ሰልጣኞች አክለውም እንዳሉት ይህ ስልጠና በበጀት አመቱ መጀመሪያ ላይ መሰጠት ቢችል ለስራችን የበለጠ አቅም ይሠጠናል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የሚዲያ ልማትና አብዝሃነት ቡድን
መጋቢት 2013 ዓ.ም

በኮቪድ-19  በሽታ ምክንያት ለ1 አመት ተራዝሞ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቁን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አስታወቀ:-የጽ/ቤቱ ሃላፊ...
19/03/2021

በኮቪድ-19 በሽታ ምክንያት ለ1 አመት ተራዝሞ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቁን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አስታወቀ:-
የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ አጥናፉ አባተ እንዳሉት በ2012 የትምህርት ዘመን ይሰጥ የነበረው ሃገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ላይ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ ለ1ሺህ 296 ተማሪዎች ፈተናውን ለመስጠት አቅደን 1ሺህ 291 ተማሪዎች ፈተናውን በሰላማዊ መንገድ መውሰድ መቻላቸውን አስረድተዋል::
በፈተና ጣቢያው ላይ የጸጥታ ማስከበር ስራን ሲመሩና ሲያስተባብሩ ያገኘናቸው የመርጡለማሪያም ከተማ አስተዳደር የፖሊስ ጽቤት ሃላፊ ኢንስፔክተር ወንዱ በላይ እና የሚሊሻ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዋለልኝ አረጋ በበኩላቸው ተፈታኝ ተማሪዎች በኮቪድ-19 በሽታ ምክንያት ለ1 አመት ያክል ከትምህርት ገበታቸው ተለይተው ቢቆዩም አስፈላጊውን ጥናትና ዝግጅት በማድረግ ያጋጠማቸውን የስነልቦናጫና ተቋቁመው ዛሬ ላይ ፈተናውን ሰላማዊ በሆነ እና ዲሲፕሊን በተሞላበት መልኩ ማጠናቀቅ ችለዋል ብለዋል::
ፈተናቸውን አጠናቀው ሲወጡ ያነጋገርናቸው ተፈታኝ ተማሪዎችም ለ1 አመት ያክል ከትምህርት ገበታ ብንለይም የፈጠረብንን የሞራል ጫና በመቋቋምና ለፈተናው የምንችለውን ዝግጅትና ጥናት በማድረግ ለማጠናቀቅ ችለናል በማለት ፈተና አወጣጡም በተማርነው እና በተዘጋጀንበት ልክ የቀረበልን ስለሆነ የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለመግባት በተስፋ እንጠብቃለን ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል::

የሚዲያ ልማትና አብዝሃነት ቡድን
መጋቢት 2013 ዓ.ም

በ2012 ለ2013 የምርት ዘመን 870 ሺህ 879 ኩንታል የሚሆን  ምርት ለማምረት ታቅዶ 614 ሺህ 469 ኩንታል ምርት መሰብሰቡን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት አስታወቀ...
19/03/2021

በ2012 ለ2013 የምርት ዘመን 870 ሺህ 879 ኩንታል የሚሆን ምርት ለማምረት ታቅዶ 614 ሺህ 469 ኩንታል ምርት መሰብሰቡን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት አስታወቀ፡-

በ2012 ለ2013 የምርት ዘመን 870 ሺህ 879 ኩንታል የሚሆን ምርት ለማምረት ታቅዶ 614 ሺህ 469 ኩንታል ምርት መሰብሰቡን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት አስታወቀ፡...
19/03/2021

በ2012 ለ2013 የምርት ዘመን 870 ሺህ 879 ኩንታል የሚሆን ምርት ለማምረት ታቅዶ 614 ሺህ 469 ኩንታል ምርት መሰብሰቡን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት አስታወቀ፡-
በጽቤቱ የሰብል ልማት ጥበቃ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙሉአለም አንተነህ እንደገለጹት በምርት ዘመኑ 870 ሺህ 879 ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ 614 ሺህ 469 ኩንታል ምርት መሰብሰቡን ገልጸው በምርት ዘመኑ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር በ2 ፐርሰንት ብልጫ ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
እንደ ባለሙያው ገለጻ በምርት ዘመኑ በቆሎ፤ጤፍ እና ባቄላ የተሻለ የምርት ጭማሬ ያሳዩ የሰብል አይነቶች መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ በየምርት ዘመንም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ጽ/ቤቱ የ2013 ዓ.ም አጠቃላይ የሰብል ልማት እቅዶችን በየደረጃው ለሚሰሩ የዘርፉ ባለሙያዎች በማውረድ እየሰራን ነው ብለዋል፡፡
አቶ ሙሉአለም ከዚሁ ጋር አያይዘው እንዳሉት በቀጣይ የምርት ዘመን የሰብል ምርትን በሚፈለገው እቅድ ልክ ለማሳካት አርሶ አደሩ የእርሻ ስራውን ደጋግሞ በማረስ አደገኛና መጤ አረሞችን በግልና በወል መሬቶች ላይ የማጽዳት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የሚዲያ ልማትና አብዝሃነት ቡድን
መጋቢት 2013 ዓ.ም

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ በ2012 ዓ.ም ይሰጥ የነበረው ሃገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተሰጠ መሆኑን በምስራቅ ጎጃም ዞን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ...
08/03/2021

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ በ2012 ዓ.ም ይሰጥ የነበረው ሃገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተሰጠ መሆኑን በምስራቅ ጎጃም ዞን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አስታወቀ፡-
በሃገር አቀፍ ደረጃ ከዛሬ የካቲት 29/2013 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናው መሰጠት መጀመሩን እና በታቀደው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እየተሰጠ መሆኑን እና ተፈታኞች የኮቪድ ወረርሽኝን ለመከላከል የአፍ መሸፈኛ ማስክ በመጠቀም በዛሬው እለት ፈተናውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየወሰዱ መሆኑን የፈተና ጣቢያውን እየመሩና እያስተባበሩ ያገኘናቸው አቶ ብርሃኑ በላይ ተናግረዋል፡፡

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ በ2012 ዓ.ም ይሰጥ የነበረው ሃገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተሰጠ መሆኑን በምስራቅ ጎጃም ዞን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ...
08/03/2021

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ በ2012 ዓ.ም ይሰጥ የነበረው ሃገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተሰጠ መሆኑን በምስራቅ ጎጃም ዞን የእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አስታወቀ፡-
በሃገር አቀፍ ደረጃ ከዛሬ የካቲት 29/2013 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናው መሰጠት መጀመሩን እና በታቀደው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እየተሰጠ መሆኑን እና ተፈታኞች የኮቪድ ወረርሽኝን ለመከላከል የአፍ መሸፈኛ ማስክ በመጠቀም በዛሬው እለት ፈተናውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየወሰዱ መሆኑን የፈተና ጣቢያውን እየመሩና እያስተባበሩ ያገኘናቸው አቶ ብርሃኑ በላይ ተናግረዋል፡፡
አስተባባሪው ከዚሁ ጋር አያይዘው እንዳሉት ፈተናውን በሚፈለገው ልክ ለመስጠት 33 ፈታኝ መምህራን፤በ33 ሴክሽን በመደልደል እና 11 ሱፐርቫይዘሮችን በማድረግ በአንድ የመፈተኛ ክፍል ውስጥ 40 ተማሪዎችን አስቀምጠን ፈተናውን እየሰጠን ነው ብለዋል፡፡
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አጥናፉ አባተ በበኩላቸው የፈተናው አሰጣጥ ቀደም በታብሌት ይሰጥ ተብሎ በትምህርት ሚኒስተር በኩል የተላለፈው መግለጫ ቀርቶ አሁን ላይ ፈተናው በተለመደው አግባብ በወረቀት እየተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የሚዲያ ልማትና አብዝሃነት ቡድን
ይካቲት 2013 ዓ.ም

ሞዛምቢክ የኮሮና ቫይረስ ክትባት ዘመቻ ዛሬ ትጀምራለችአዲስ አበባ፣ የካቲት 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሞዛምቢክ የኮሮና ቫይረስ ክትባትን በዘመቻ መልክ ዛሬ መስጠት ትጀምራለች፡፡በዚህም የ...
08/03/2021

ሞዛምቢክ የኮሮና ቫይረስ ክትባት ዘመቻ ዛሬ ትጀምራለች
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሞዛምቢክ የኮሮና ቫይረስ ክትባትን በዘመቻ መልክ ዛሬ መስጠት ትጀምራለች፡፡
በዚህም የጤና ባለሙያዎች በሥራ ወቅት ለቫይረሱ ከፍተኛ ተጋላጭ በመሆናቸው ክትባቱን በቅድሚያ ይወስዳሉ ነው ተባለው፡፡
የሞዛምቢክ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሃገሪቱ ባለፈው ወር ከቻይና ከተቀበለችው 200 ሺህ ዶዝ ውስጥ 121 ሺህ 530 ክትባቶችን ማሰራጨቱን ገልጿል፡፡
እንዲሁም ዛሬ ተጨማሪ 484 ሺህ ክትባቶችን ትቀበላለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ከእነዚህ ውስጥ 384 ሺህ ከኮቫክስ 100 ሺህ ደግሞ በህንድ የተሰጠ የኮቪሺልድ ክትባት እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡
በሞዛምቢክ እስካሁን 62 ሺህ 520 በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሲሆን 693 ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል፤ 46 ሺህ 421 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል ነው የተባለው፡፡

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀአዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድንና ነዳ...
08/03/2021

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴሩ ይህንን ያለው ከተቋሙ፣ ከተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ጋር የዘርፉን የሰባት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት ነው፡፡
በዚሁ ወቅት ከባለፈው በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ከዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት መቻሉንም ገልጿል፡፡
በተደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ተግባራት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የማዕድን ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ወይዘሮ ስመኝ ገልጸዋል።
መንግስት ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት የሠጠው በመሆኑ አመራሩና ሠራተኛው በጋራ ተናቦ በመስራት የተጣለበትን ሃገራዊ ተልዕኮ መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የቀጣይ 5 ወራት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችም ቀርበዋል።
የሲቪል ሠርቪስ ፍኖተ ካርታም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ውስጥ በህዝብ በሚመረጥ መንግሥት የሚነድፋቸውን የልማት ዕቅዶች ማሳካት የሚችል፣ የህዝብ አገልጋይነትን መንፈስ የተላበሰና ነጻ፣ገለልተኛና ብቃት ያለው የመንግስት አገልግሎት ስርዓት መገንባት የፍኖተ ካርታው ዋናው ዓላማ መሆኑንም ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀአዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድንና ነዳ...
08/03/2021

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴሩ ይህንን ያለው ከተቋሙ፣ ከተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ጋር የዘርፉን የሰባት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት ነው፡፡
በዚሁ ወቅት ከባለፈው በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ከዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት መቻሉንም ገልጿል፡፡
በተደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ተግባራት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የማዕድን ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ወይዘሮ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከዘርፉ ከ17 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘትም ማቀዱን አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴሩ ይህንን ያለው ከተቋሙ፣ ከተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ጋር የዘርፉን የሰባት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት ነው፡፡
በዚሁ ወቅት ከባለፈው በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ከዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት መቻሉንም ገልጿል፡፡
በተደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ተግባራት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የማዕድን ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ወይዘሮ ስመኝ ገልጸዋል።
መንግስት ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት የሠጠው በመሆኑ አመራሩና ሠራተኛው በጋራ ተናቦ በመስራት የተጣለበትን ሃገራዊ ተልዕኮ መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የቀጣይ 5 ወራት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችም ቀርበዋል።
የሲቪል ሠርቪስ ፍኖተ ካርታም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ውስጥ በህዝብ በሚመረጥ መንግሥት የሚነድፋቸውን የልማት ዕቅዶች ማሳካት የሚችል፣ የህዝብ አገልጋይነትን መንፈስ የተላበሰና ነጻ፣ገለልተኛና ብቃት ያለው የመንግስት አገልግሎት ስርዓት መገንባት የፍኖተ ካርታው ዋናው ዓላማ መሆኑንም ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ጠ/ሚ ዐቢይ በባህር ዳር ከተማ በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን ድልድይ የግንባታ ሂደት ጎበኙአዲስ አበባ ፣ የካቲት 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በባህር...
08/03/2021

ጠ/ሚ ዐቢይ በባህር ዳር ከተማ በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን ድልድይ የግንባታ ሂደት ጎበኙ
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በባህር ዳር ከተማ በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን ድልድይ የግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ የፌደራልና የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
የድልድዩ ግንባታ ሂደት 25 በመቶ መድረሱም በዚህ ወቅት ተገልጿል፡፡
ድልድዩ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅም ይሰራል ተብሏል፡፡

 #ዘመቻ -ካሳ-ያስፈልገናል! ትህነግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ የረዥም ጊዜ እቅዱ መገንጠል ለመሆኑ በትህነግ ፀረ ኢትዮጵያዊ አቋም ተማረው ከመሰረቱት ድርጅት የወጡ ነባር አባሎቹ እና እልፍ ለሀቅ የ...
08/03/2021

#ዘመቻ -ካሳ-ያስፈልገናል!
ትህነግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ የረዥም ጊዜ እቅዱ መገንጠል ለመሆኑ በትህነግ ፀረ ኢትዮጵያዊ አቋም ተማረው ከመሰረቱት ድርጅት የወጡ ነባር አባሎቹ እና እልፍ ለሀቅ የቆሙ የትግራይ ልጆች የመሰከሩትና የሚመሰክሩት እውነት ነው፡፡ በመጨረሻም የሆነው ይህ ነው፡፡ ህዝቡን ሳይሆን መሬቱን የሚሻው ትህነግ የግዛት ማስፋፋት አባዜው መገለጥ የጀመረው ገና አዲስ አበባን አንደተቆጣጠረ ነበር፡፡ በመሆኑም በአንድ ሀገር ላይ እንዳልኖረ ህዝብ ፤ የጠላት ኃይል እንደሚያደርገው የመሬት ወረራውን በማጧጧፍ ከተከዜ መለስ የሚገኙ የጎንደር አማራ የሚኖርባቸውን የወልቃይ ጠገዴና ሰቲት ሁመራ አካባቢዎች፣ የአገው ህዝብ የሚኖርባቸውን ወፍላ፣ ዛታና ኮረም አካባቢዎች፣ የራያ ህዝብ የሚኖርባቸው ራያ አለማጣና አካባቢውን በኃይልና በማን አለብኝነት በመቆጣጠር ያለ ህዝቡ ፍላጎት ወደ ትግራይ አካቶ መውሰዱ የሚታወቅ ነው፡፡ እነዚህ ህዝቦች ይህ ስሁት አስተዳደር በላያቸው ላይ ከተጫነ ጊዜ ጀምሮ ለአእምሮ የሚዘገንን፣ ለጆሮ የሚከብድ ወንጀሎች ሲፈጸምባቸው እንደኖረ ሀገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው የአደባባይ ሀቅ ነው፡፡ የዚህ አካባቢ ህዝብ የማንነት ጥያቄዎችን በማንሳት ትህነግን ትንፋሽ ሲያሳጣው እንደኖረም ይታወቃል፡፡ በዚህም ምክንያት ትህነግ የወሰደው እርምጃ ፍጹም አረመኒያዊነት የተሞላበትና ማንነቱን ለማሳጣት የተደረገ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው፡፡ በመሆኑም የዚህን አካባቢ ህዝብ ለስደት፣ ለጅምላ ግድያና ለዘር ማጽዳት መከራዎች ዳርገውት ቆይተዋል፡፡ ለዚህም እልፍ ምስክሮች በዙሪያችን ይገኛሉ፡፡ የጅምላ መካነ መቃብራት፣ የዋሻ ውስጥ የጅምላ አጽመ ቅሪቶች፣ የዘመናት የመሬት ውስጥ የጨለማ ማሰቃያ ወህኒ ቤቶች፣ ልጅና የልጅ ልጆቻቸውን በትህነግ የግፍ ጥይቶች ተነጥቀው በሀዘን እድሜያቸውን የሚገፉ ወላጆች ሁሉ ምስክሮቻችን ናቸው፡፡ በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እዳይማሩና እንዳይናገሩ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሰለባ የተደረጉ፤ ተወልደው በኖሩበት ሀገር ተቋማዊ ጥቃት እንዲደርስባቸው በማድረግ ከአስተዳደራዊ መዋቅር የማጽዳት ሥራ የተፈጸመባቸው እልፍ ወጣቶች ምስክሮቻችን ናቸው፡፡ እነዚህ ወገኖቻችን ለደረሰባቸው የዘር ማጥፋት ወንጀል የነብስ ካሳ ያስፈልጋቸዋል፡፡ በኢኮኖሚ መገለል የደረሰባቸው በመሆኑ የምጣኔ ኃብት ካሳ ተሰጥቷቸው አከባቢያቸው የሚለማበት መንገድ ሊፈጠር ይገባዋል፡፡ እነዚህ ህዝቦች በማይፈልጉት አስተዳደራዊ ወሰንና አመራር ውስጥ በኃይል ተጨፍልቀው የኖሩ በመሆናቸው ነጻነታቸው ተፈቅዶላቸው ከእነ ሙሉ ክብራቸው አስተዳደራዊ ወሰናቸውን በዘላቂነት የመመለስ ካሳ ያስፈልጋቸዋል፡፡
እዉነትን ይዘን ዝም አንልም!!
አማራ ኮሚዩኒኬሽን

 ትህነግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ የረዥም ጊዜ እቅዱ መገንጠል ለመሆኑ በትህነግ ፀረ ኢትዮጵያዊ አቋም ተማረው ከመሰረቱት ድርጅት የወጡ ነባር አባሎቹ እና እልፍ ለሀቅ የቆሙ የትግራይ ልጆች የመሰከሩ...
08/03/2021


ትህነግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ የረዥም ጊዜ እቅዱ መገንጠል ለመሆኑ በትህነግ ፀረ ኢትዮጵያዊ አቋም ተማረው ከመሰረቱት ድርጅት የወጡ ነባር አባሎቹ እና እልፍ ለሀቅ የቆሙ የትግራይ ልጆች የመሰከሩትና የሚመሰክሩት እውነት ነው፡፡ በመጨረሻም የሆነው ይህ ነው፡፡
ህዝቡን ሳይሆን መሬቱን የሚሻው ትህነግ የግዛት ማስፋፋት አባዜው መገለጥ የጀመረው ገና አዲስ አበባን አንደተቆጣጠረ ነበር፡፡ በመሆኑም በአንድ ሀገር ላይ እንዳልኖረ ህዝብ ፤ የጠላት ኃይል እንደሚያደርገው የመሬት ወረራውን በማጧጧፍ ከተከዜ መለስ የሚገኙ የጎንደር አማራ የሚኖርባቸውን የወልቃይ ጠገዴና ሰቲት ሁመራ አካባቢዎች፣ የአገው ህዝብ የሚኖርባቸውን ወፍላ፣ ዛታና ኮረም አካባቢዎች፣ የራያ ህዝብ የሚኖርባቸው ራያ አለማጣና አካባቢውን በኃይልና በማን አለብኝነት በመቆጣጠር ያለ ህዝቡ ፍላጎት ወደ ትግራይ አካቶ መውሰዱ የሚታወቅ ነው፡፡
እነዚህ ህዝቦች ይህ ስሁት አስተዳደር በላያቸው ላይ ከተጫነ ጊዜ ጀምሮ ለአእምሮ የሚዘገንን፣ ለጆሮ የሚከብድ ወንጀሎች ሲፈጸምባቸው እንደኖረ ሀገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው የአደባባይ ሀቅ ነው፡፡
የዚህ አካባቢ ህዝብ የማንነት ጥያቄዎችን በማንሳት ትህነግን ትንፋሽ ሲያሳጣው እንደኖረም ይታወቃል፡፡ በዚህም ምክንያት ትህነግ የወሰደው እርምጃ ፍጹም አረመኒያዊነት የተሞላበትና ማንነቱን ለማሳጣት የተደረገ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው፡፡
በመሆኑም የዚህን አካባቢ ህዝብ ለስደት፣ ለጅምላ ግድያና ለዘር ማጽዳት መከራዎች ዳርገውት ቆይተዋል፡፡ ለዚህም እልፍ ምስክሮች በዙሪያችን ይገኛሉ፡፡ የጅምላ መካነ መቃብራት፣ የዋሻ ውስጥ የጅምላ አጽመ ቅሪቶች፣ የዘመናት የመሬት ውስጥ የጨለማ ማሰቃያ ወህኒ ቤቶች፣ ልጅና የልጅ ልጆቻቸውን በትህነግ የግፍ ጥይቶች ተነጥቀው በሀዘን እድሜያቸውን የሚገፉ ወላጆች ሁሉ ምስክሮቻችን ናቸው፡፡
በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እዳይማሩና እንዳይናገሩ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሰለባ የተደረጉ፤ ተወልደው በኖሩበት ሀገር ተቋማዊ ጥቃት እንዲደርስባቸው በማድረግ ከአስተዳደራዊ መዋቅር የማጽዳት ሥራ የ

Address

Enebsie Sar Medir Goverment Communcation Office
Mertule Maryam

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Enebsie communication affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share