Lalibela Government Communication Affairs Office

Lalibela Government Communication Affairs Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Lalibela Government Communication Affairs Office, Government Official, Lalibela.

የጤና ሚኒስትሯ ዶ.ር መቅደስ ዳባና የአፍሪካና ኢንዲያ ቢልጌትስ ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት አንኩር ቮራ የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ጎብኝተዋል።ላሊበላ፦ሰኔ ፣7፣2018 (የላሊበላ...
14/06/2026

የጤና ሚኒስትሯ ዶ.ር መቅደስ ዳባና የአፍሪካና ኢንዲያ ቢልጌትስ ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት አንኩር ቮራ የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ጎብኝተዋል።

ላሊበላ፦ሰኔ ፣7፣2018 (የላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የጤና ሚኒስትሯ ዶ.ር መቅደስ ዳባ፣ የአፍሪካና ኢንዲያ የቢልጌትስ ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት አንኩር ቮራ እና ሌሎች የፋውንዴሽኑ የስራ ሃላፊዎችን የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች ናቸው አቀባበል ያደረጉላቸው።

የጤና ሚኒስትሯ ዶ.ር መቅደስ ዳባና የቢልጌትስ ፋውንዴሽን የአፍሪካና ኢንዲያ ፕሬዝዳንት አንኩር ቮራና እና ሌሎች የፋውንዴሽኑ የስራ ሃላፊዎች የቅዱስ ላሊበላን ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ጎብኝተዋል።

የስራ ሃላፊዎቹ ቅዱስ ላሊበላ በ12 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከዓለት ላይ ያነፃቸውን ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ነው የተመለከቱት።

ከ700 በላይ እንቁላል ጣይ ደሮዎች ለእናቶች ተሰራጭተዋል።ላሊበላ፦ሰኔ 3፣2018(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን)የህፃናትን መቀንጨር ለመከላከል የሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮጀክት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛ...
10/06/2026

ከ700 በላይ እንቁላል ጣይ ደሮዎች ለእናቶች ተሰራጭተዋል።

ላሊበላ፦ሰኔ 3፣2018(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን)የህፃናትን መቀንጨር ለመከላከል የሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮጀክት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።

ፕሮጀክቱ የህፃናት መቀንጨርን ለመከላከልና ነብሰ ጡር እና አጥቢ እናቶች የተመጣጠነ ምግብን ለልጆቻቸው እንዲመግቡ ለማስቻል ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ እየሰራ ነው።

በከተማ አስተዳደሩ የህፃናትን መቀንጨር ለመከላከል የሚያስችሉ ለ60 እናቶች ለእያንዳንዳቸው 12 ደሮዎች 720 እንቁላል ጣይ ደሮዎች ተሰራጭተዋል።

በፕሮጀክቱ ድጋፍ ከተደረገላቸው የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አሰገደች ወዳጀ አንዷ ናት፦የተደረገላቸው የእንቁላል ጣይ ደሮዎች ድጋፍ ለልጆቿ የተመጣጠነ ምግብ ለማቅረብ እንደሚያስችላት ነው የገለፀችው።

አስራ ሁለት ደሮዎች እንደተሰጧት የገለፀችው አሰገደች ፣ደሮዎችን በአግባቡ በመንከባከብ ለታለመላቸው አለማ ለማዋል እሰራለሁ ነው ያለችው።

ሌላኛዋ ድጋፍ የተደረገላት አዲና ሲሳይ፦ከዚህ ቀደም ለልጆቿ የተመጣጠነ ምግብ ለማቅረብ ትቸገር እንደነበር በማስታወስ የተደረገላቸው ድጋፍ በህፃናት እድገት ላይ አስተዋፅኦው የጎላ ስለመሆኑ ነው የገለፀቸው።

አካባቢውን የተላመዱ ደሮዎችን በመግዛት ለእናቶች ተደራሽ ማድረግ መቻሉን የገለፁት የላሊበላ ከተማ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ባየ ሽፈራው ናቸው።

ፕሮጀክቱ የህፃናት መቀንጨርን ለመከላከል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ያነሱት ሃላፊዉ 9መቶ ሺህ ብር ወጭ የሆነባቸው እንቁላል ጣይና አውራ ደሮዎች ተገዝተው መሰራጨታቸውን ነው ያነሱት።

ከደሮዎቹ በተጨማሪ መኖ ማሰራጨት መቻሉንም ነው የተናገሩት።

ነብሰጡር እናቶችና ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ ማግኘት ስላለባቸው እንቁላል፣ስጋና የስጋ ውጤቶች እና አትክልትና ፍራ ፍሬ ውጤቶችን እንዲመገቡ ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑ ነው የተመላከተው።

በላሊበላ ከተማ ከ135 ሚሊየን ብር  በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ  አልሚዎች ፈቃድ ተሰጠ።ላሊበላ፦ሰኔ 2፣2018፣(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን)በላሊበላ ከተማ አስተዳደር ከ135 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታ...
09/06/2026

በላሊበላ ከተማ ከ135 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ አልሚዎች ፈቃድ ተሰጠ።

ላሊበላ፦ሰኔ 2፣2018፣(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን)በላሊበላ ከተማ አስተዳደር ከ135 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ አልሚዎች የኢንቨስትመንት ፈቃድ እንደተሰጣቸው ነው የተገለጸው።

በ2018 በጀት ዓመት ከ135 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ አልሚዎች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠታቸውን የላሊበላ ከተማ አስተዳዳር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወርቅየ አለነ ተናግረዋል።

ባለሃብቶቹ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው በማኑፍክቸሪንግ ዘርፎች፦በዘይት ማቀነባበሪያ፣በዱቄት ማምረቻና በፈሳሽ ሳሙናና ንፅህና መጠበቂያ ፋብሪካ ዘርፎች ለሚሰማሩ አልሚዎች መሆኑን ሃላፊው አብራርተዋል።

በሶስቱም ዘርፎች የተሰማሩት ባለሃብቶች በግልና በማህበር ለማልማት ፈቃድ ማግኘታቸውንና10275 ካሬ ሜትር መሬት መተላለፉ ነው የተመላከተው።

በከተማዋ ከዚህ ቀደም ከተለመደው ሆቴል ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተጨማሪ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለሚሰማሩ አልማዎች ትኩረት ስለመሰጠቱም ጠቅሰዋል።

የባለሀብቶቹ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ማግኘታቸው ለሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተስፋ የተጣለበት ሲሆን፤ወደ ሥራ ሲገቡ ለ1275 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ሊፈጥር እንደሚችል ሃላፊው አስረድተዋል።

አምራች ዘርፎችን ለማበረታታትም ትኩረት ስለመሰጠቱ ነው የተገለፀው።

በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም እንዲገነቡ ፍቃድ ከተሰጣቸው የነጅ ማደያ ፕሮጀክቶች ውስጥ ሁለቱን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ወደ ስራ በማስገባት ግንባታቸውን ማጠናቀቃቸው ነው የተገለፀው።

የነዳጅ ማደያዎቹ ግንባታ መጠናቀቅ በከተማዋ የሚስተዋለውን የነዳጅ እጥረት ከመቅረፉ ባለፈ የአጎራባች ወረዳዎችን ፍላጎት የሚያሟላ ስለመሆኑም ነው ሃላፊው የተናገሩት።

ከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፎች ተሰማርተው ለሚያለሙ ባለሃብቶች 9.5 ሄክታር መሬት ማዘጋጀቱንና ወደ ከተማዋ መጥተው የሚያለሙ ባለሃብቶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑንም ነው ሃላፊው ያብራሩት።

ባሳለፍናቸው አስራ አንድ ወራት ከ1ሺ400 በላይ እናቶች በጤና ተቋማት የወሊድ አገልግሎት አግኝተዋል፡፡ላሊበላ፦ግንቦት፣30፣2018 (ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የእናቶችንና ህጻናትን ጤና ለመጠበቅ ...
07/06/2026

ባሳለፍናቸው አስራ አንድ ወራት ከ1ሺ400 በላይ እናቶች በጤና ተቋማት የወሊድ አገልግሎት አግኝተዋል፡፡

ላሊበላ፦ግንቦት፣30፣2018 (ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የእናቶችንና ህጻናትን ጤና ለመጠበቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ስለመሆኑ የላሊበላ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡

ባሳለፍናቸው11ወራት እናቶችና ህጻናት ጤና አጠባበቅ እና በሌሎችም ዘርፎች የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው ጽ/ቤቱ ያስታወቀው፡፡

ጽ/ቤቱ 2018 በጀት አመት የ11ወራት የስራ አፈጻጸሙን የጤና ባለሙያዎች በተገኙበት ገምግሟል፡፡

እናቶች በጤና ተቋማት እንዲወልዱ ሰፊ የግንዛቤ ስራ በመሰራቱ በጤና ተቋማት የሚወልዱ እናቶች ቁጥር መጨመሩን የገለፁት የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሃላፊ እሸቱ ገስጤ ናቸው፡፡

ነፍሰ ጡር እናቶች በጤና ተቋማት ክትትል እንዲያደርጉ ከማድረግ ጀምሮ የወሊድ አገልግሎቱን እንዲያገኙ ለማድረግ ግንዛቤ እየተፈጠረ መምጣቱንም ሃላፊው ገልፀዋል።

ባሳለፍናቸው 11ወራት 599 እናቶች በጤና ጣቢያ እንዲሁም 875 እናቶች ደግሞ በሆስፒታል በጥቅሉ 1474 እናቶች በጤና ተቋም የወሊድ አገልግሎት ማግኘታቸው ነው ከጤና ተቋሙ የተገኘው መረጃ የሚያመለክተው።

የህጻናትን ጤንነት ለመጠበቅ ህጻናት በወቅቱ የሚያስፈልጋቸውን ክትባት እንዲያገኙ በማድረግ በኩልም የተሻለ አፈጻጸም መኖሩም ነው የተገለፀው፡፡

የምግብ ዕጥረት ያለባቸውን ህፃናት አልሚ ምግብ እንዲያገኙ በማድረግ በኩል ሰፊ ስራ መሰራቱንም ነው የፅህፈት ቤት ሃላፊው ያብራሩት።

የጤና መሰረተ ልማትን በማሟላት በኩል ሰፊ ስራ መሰራቱን የገለፁት የፅህፈት ቤት ሃላፊው እሸቱ ገስጤ የድንገተኛ ክፍል፣የመድሃኒትና፣ካርድ ክፍልን በመገንባት ለተገልጋይ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ነው ያነሱት።

የጤና ተቋማትን ፅዱና ውብ በማድረግ በኩል ሰፊ ስራ መሰራቱንና ለተገልጋይ ምቹ ሁኔታ ስለመፈጠሩ ነው ሃላፊው የተናገሩት።

የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆችን ለማሟላት በ5ቱም ቀበሌዎች እየተሰራ መሆኑንና የማህበረሰቡን ጤና ለመጠበቅ ትኩረት ስለመሰጠቱም ነው የተናገሩት።

በዚህ አመት የመድሃኒት ዕጥረትን ለመቅረፍ የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት በመገንባት ማህበረሰቡ መድሃኒት በቅርብ የሚያገኝበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩም ተመላክቷል።

በጤና ተቋማት እየተሰጠ ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ እየተሻሻለ በመምጣቱ ጤንነቱን ለመጠበቅ ወደ ተቋሙ የሚመጣው የማህበረሰብ ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ነው እሸቱ ገስጤ ያብራሩት።

የጤና መድን አገልግሎትን ተደራሽ ከማድረግ አኳያ በቤተሰብ ደረጃ ከ23 ሺህ በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉም ነው የተመላከተው።

እናቶች ለልጆቻቸው የተመጣጠነ ምግብን እንዲመግቡ ለማድረግ በተግባር  የተደገፈ ትምህርት እየተሰጡ ነው።ላሊበላ፦ግንቦት፣28፣2018(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የህፃናት መቀንጨርን ለመከላከል የሰቆጣ...
05/06/2026

እናቶች ለልጆቻቸው የተመጣጠነ ምግብን እንዲመግቡ ለማድረግ በተግባር የተደገፈ ትምህርት እየተሰጡ ነው።

ላሊበላ፦ግንቦት፣28፣2018(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የህፃናት መቀንጨርን ለመከላከል የሰቆጣ ቃል ኪደን ፕሮጀክት በላሊበላ ከተማ በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው።

በከተማው ባሉ ቀበሌዎች በእናቶችና ህፃናት የተመጣጠነ ምግብን በሚያገኙበት ዙሪያ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው።

እንስሳትን ገዝቶ በመስጠትና የአትክልትና ፍራ ፍሬ ውጤቶችን ለማልማት ያለመ ዘር የማሰራጨት ስራዎችም በመከናወን ላይ ናቸው።

ወ/ሮ መሰረት አዲሴ፦በጤና ባለሙያ በተግባር የተመጣጠነ ምግብ አዘገጃጀት ትምህርቱ ከተሰጣቸው እናቶች መካከል አንዷናት፦ከዚህ ቀደም ለልጇ ታዘጋጀው ከነበረው ምግብ በተለየ መልኩ በቀላሉ በቤት መዘጋጀት ያለባቸውን የተመጣጠኑ ምግቦች ለማዘጋጀት ፕሮጀክቱ እየሰጣቸው ያለው ስልጠና እንደጠቀማቸው ነው የገለፀችው።

ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ ወ/ሮ ዳሳሽ መንግስቴ የተሰጣቸው ትምህርት ለልጆቻቸው በቀላሉ የተመጣጠነ ምግብ ለማዘጋጀትና መቀንጨርን ለመከላከል እንደሚያስችላቸው ነው ያነሳችው።

ሙሉ ሲሳይና ቤተ ልሄም ግርማ በበኩላቸው የተመጣጠነ ምግብ አዘገጃጀት ተግባር ተኮር ትምህርቱ ለልጆቻቸው ጠቃሚ መሆኑን በማንሳት በፕሮጀክቱ እየተሰጠ ያለው ድጋፍና ስልጠና የተስተካከለ የህፃናት እድገት እንዲኖር ያስችላል ነው ያሉት።

ፕሮጀክቱ ህፃናት ከእናት ጡት በተጨማሪ መውሰድ ያለባቸውን የተመጣጠነ ምግብ አስመልክቶ ለእናቶች ድጋፍ እያደረገ ነው።

በላሊበላ ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶች ይፋ እየሆኑ ነው። ላሊበላ፦ግንቦት 25/2018 ዓ.ም(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) በላሊበላ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች...
02/06/2026

በላሊበላ ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶች ይፋ እየሆኑ ነው።

ላሊበላ፦ግንቦት 25/2018 ዓ.ም(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) በላሊበላ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የድምጽ ውጤቶችን ይፋ እያደረጉ ነው።

የከተማዋ ነዋሪዎች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የምርጫ ውጤቶችን እየተመለከቱ ነው።

ነዋሪዎቹ የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸውም ተናግረዋል።

የድምጽ ውጤቶቹ ለህዝብ ግልጽ በሆነ ቦታ ላይ መለጠፋቸውንም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ባለ ድርሻ አካላት የድርሻቸውን ተወጥተዋል።ላሊበላ፦ግንቦት 25፣2018(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን)7ኛው ሃገራዊ ምርጫ በላሊበላ ከተማ አስተዳደ...
02/06/2026

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ባለ ድርሻ አካላት የድርሻቸውን ተወጥተዋል።

ላሊበላ፦ግንቦት 25፣2018(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን)7ኛው ሃገራዊ ምርጫ በላሊበላ ከተማ አስተዳደር በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን የላሊበላ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።

የምርጫ ቁሳቁስን ወደ ምርጫ ጣቢያ ከማድረስ ጀምሮ፣ደህንነታቸው እንዲጠበቅ መሰራቱን የገለፁት የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ፅ/ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር ወርቅየ ነጋሽ ናቸው።

ከንጋቱ አስራ ሁለት ስዓት ጀምሮ እስከ ምሽት አስራ ሁለት ስዓት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን የሃገር መከላከያ ሰራዊት፣የከተማው ፖሊስና ሰላም አስከባሪዎች እና ህዝቡ የየድርሻቸውን ሃላፊነት መወጣታቸውን ነው የገለፁት።

ሁሉም አካላት በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ የምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው መርህ መሰረት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ መከናወኑን ነው ያነሱት።

ለሁሉም አካላት ላበረከቱት አስተዋፅኦ ኢንስፔክተር ወርቅየ ምስጋና አቅርበዋል።

የ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ በከተማው ድምፅ የመስጠት ሂደቱ ግልፅና ፍትሃዊ በመሆነ መልኩ መከናወኑን የገለፁት ደግሞ የላሊበላ ከንቲባ መሳይ ወዳጀ ናቸው።

በከተማው በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ማህበረሰቡ ከማለዳው 12 ስዓት ጀምሮ ይበጀኛል፣ያስተዳድረኛል ያለውን በነፃነት መርጧል ነው ያሉት ከንቲባው።

ድምፅ የመስጠት ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን የሃገር መከላከያ ሰራዊት፣የከተማው ፖሊስ፣ሰላም አስከባሪና የከተማው ማህበረሰብ ላደረጉት ስራ ምስጋና አቅርበዋል ከንቲባው።

"ለሚቀጥሉት አምስት አመታት ሰላምና ልማት ያረጋግጥልናል ለምንለው ድምፃችንን እየሰጠነ ነው" የላሊበላ ከተማ ነዋሪዎችበከተማዋ በሚገኙ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምፃቸውን እየሰጡ ነ...
01/06/2026

"ለሚቀጥሉት አምስት አመታት ሰላምና ልማት ያረጋግጥልናል ለምንለው ድምፃችንን እየሰጠነ ነው" የላሊበላ ከተማ ነዋሪዎች

በከተማዋ በሚገኙ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምፃቸውን እየሰጡ ነው።

ምርጫውን ስንጠብቀው የቆየ በመሆኑ በማለዳ ወጥተን መርጠናል ያሉት የከተማዋ ነዋሪ አለልኝ መልካም ናቸው።

ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ መቅደስ ምትኩ በበኩሏ የፈለግነውን ፣ይወክለናል ያልነውን መርጠናል ነው ያለችው።

በምርጫው የዜግነት ግዴታችን እየተወጣን ነው ያለው የዋግ ደሴ ለሚቀጥሉት አምስት አመታት ሰላምና ልማት ያረጋግጥልናል ያልነውን ፓርቲ መርጠናል ነው ያሉት።

የከተማዋ ነዋሪዎች አክለውም ይወክለናል፣ይመራናል ፣ያስተዳድረናል ለሚሉት ድምፃቸውን እየሰጡ እንደሚገኙ ነው ያነሱት።

ሀገርን ለማስቀጠል እንዲሁም ዕድገትን ለማረጋገጥ ምርጫ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑንም ተናግረዋል ።

በላሊበላ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች በማለዳ ወጥተው ድምፅ እየሰጡ ነው።ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችም በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።
01/06/2026

በላሊበላ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ዜጎች በማለዳ ወጥተው ድምፅ እየሰጡ ነው።

ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችም በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

በላሊበላ ከተማ  ለነገው ምርጫ ዝግጅት ተጠናቋል።ላሊበላ፦ግንቦት 23/2018 ዓ.ም(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) 7ኛው ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከስዓታት በኋላ ነገ ይካሄዳል። በላሊበላ ከተማም ለምርጫው...
31/05/2026

በላሊበላ ከተማ ለነገው ምርጫ ዝግጅት ተጠናቋል።

ላሊበላ፦ግንቦት 23/2018 ዓ.ም(ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) 7ኛው ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከስዓታት በኋላ ነገ ይካሄዳል።

በላሊበላ ከተማም ለምርጫው ሙሉ ዝግጅቶች ተጠናቅቀዋል።

በከተማዋ ለምርጫው ስኬታማነት አስፈላጊው ዝግጅቶች ሁሉ ተደርገዋል። የምርጫ ቁሳቁሶች በየምርጫ ጣቢያዎች ተሰራጭተዋል።

አስፈላጊ የሆኑ ድንኳኖች፣ የሚስጥር ድምጽ መስጫዎች፣ ወንበሮች እና ሌሎችም ተሰናድተዋል።

የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መሳይ ወዳጀ፦ የምርጫ ቁሳቁሶች በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መሰራጨታቸውን ነው የገለፁት።

የምርጫ ሂደቱን የተሳካ ለማድረግ ከምርጫ ካርድ ማውጣት ጀምሮ እስከ ድምፅ መስጫ ቅድመ ዝግጅቱን በስኬት ማጠናቀቅ መቻሉንም ነው የገለፁት።

የፀጥታ ተቋማትም በየምርጫ ጣቢያው ስራቸውን እየሰሩ ስለመሆኑ ነው ከንቲባው የተናገሩት።

ማህበረሰቡ ነፃና ገልተኛ ሆኖ ይበጀኛል፣ያስተዳድረኛል የሚለውን ለመምረጥ ዝግጅት መጠናቀቁን ነው የተገለፀው።

መራጮች ከጠዋቱ ጀምሮ ቀጠሯቸውን በየምርጫ ጣቢያቸው አድርገው ታሪካዊ አሻራቸውን ማሳረፍ እንደሚገባቸውም ነው የተመላከተው።

Address

Lalibela

Opening Hours

16:30 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lalibela Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share