27/10/2020
የላስታ ወረዳ ዐ/ህግ ሰራተኞች
በቢሮ ችግር ምክኒያት ስራ ለመስራት መቸገራቸውን ገለፁ!!!
የላስታ ወረዳ ዐ/ህግ ጽ/ቤት ሰራተኞች በ06/02/2012 ዓ.ም ስራ ለመገምገም በተሠበሠቡበት ወቅት በቢሮ ጥበት ምክኒያት የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት መቸገራቸውን በምሬት ገፀዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች እንደሚሉት የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት ከ10 ያላነሱ ክፍሎች ያሉት ቢሮ ያስፈልጋል፡፡ ነገር ግን አሁን በሁለት ክፍሎች ሁሉም ሰራተኛ ሠራተኛ ተቀምጦ ስራ እያከናወነ መሆኑ ተገልፆል፡፡
የቢሮ ጥበት ባስከተለው ችግር ሳቢያ፤
ሂደቶችን በቢሮ ነጥሎ ማሰራት አልተቻለም
ከኮቪድ 19 አንጻር መምሪያውን መሠረት አድረጎ ስራን ማከናወን አልተቻለም
ባለጉዳይ በአግባቡ ማስተናገድም ሆነ ሰነዶችን በአግባቡ ማስቀመጥ አልተቻለም
አንዳንድ ሚስጥራቸው ተጠብቆ መስተናገድ ያለባቸውን ባለጉዳዮች ማስተናገድ አልተቻለም
ሰራተኛው በአግባቡ ተሠማርቶ ሥራውን ሠርቶ ውጤት ማምጣት ተቸግሯል
ያለው ቢሮ በፋይል በመጨናነቁ መደርደሪጠዎች ተጣመው እየወደቁ በሠራተኛ ላያ ጉዳት እያደረሱ ነው ወዘተ የሚሉ አቤቱታዎችን አንሰተዋል፡፡
ከመድረኩ በተሠጠ ምላሽም ችግሩን ለመፍታት ለላስታ ወረዳ አስ/ም/ጽ/ቤት በተለያየ ጊዜ በደብዳቤ፤ በካቢኔ ስብሰባ ኢንፎርማል በሆኑ ውይይቶች በመጠየቅም ሆነ ቢሮውን በአካል የሚመለከተው አካል እነዳየው ቢደረግም እስካሁን ችግሩ እንዳልተፈታ ተገልፆል፡፡ በተጨማሪም አሁንም ችግሩ እንደቀረፍ በተለመደው አግባብ ካስተዳደር ምክር ቤቱ ጋር እንደሚሰራ እና እስከዚው ድረስ ሰራተኛው በትዕግስት ስራውን እንዳከናውን የሚል ምላሽ ተሰጥቷል፡፡