የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

  • Home
  • Ethiopia
  • Lalibela
  • የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት  የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት, Public & Government Service, Lalibela.

የወረዳ ደረጃ ማህበረሰብ ተኮር የጥበቃና የዕቅድ ዝግጅት ስብሰባ በቡታጅራ ከተማ ተከናወነ።                             ሰኔ  6/2018                        ...
13/06/2026

የወረዳ ደረጃ ማህበረሰብ ተኮር የጥበቃና የዕቅድ ዝግጅት ስብሰባ በቡታጅራ ከተማ ተከናወነ።
ሰኔ 6/2018
ሀላባ
የክልሉ ሰራተኛና ማህበራዊ፣ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ እንዲሁም የአለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት ተወካዮች የተገኙበት ስብሰባ ተከናውኗል።

ስብሰባውን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሉምባ ደምሴ እንደገለፁት ሁሉም ባለድርሻ አካል በተሰጠው ሀላፊነት ስራዎችን በቅንጅትና በትብብር ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።

የመድረኩ ዋና ዓላማ ከመኖሪያቸው ለተፈናቀሉ፣ ከፍልሰት ለተመለሱ ወገኖቻችንና ለአከባቢው ተቀባይ ማህበረሰቦች ዘላቂ ጥበቃን፣ መልሶ መቋቋምን፣ ማህበራዊ ውህደትንና በሰላም አብሮ መኖርን በጋራ ለማጠናከር ያለመ መሆኑን አንስተዋል።

ይህ ዕቅድ ሰው ላይ ያተኮረ፣ ችግር ላይ ሳይሆንበአከባቢያችን ያሉ ጠንካራ ጎኖችና መልካም ዕድሎች ላይ መሰረት ያደረገ እንዲሆን እንደሚፈለግና ማህበረሰቡ የዕቅድ ዝግጅቱን የእኔ ነው ብሎ እንዲቀበል፣ ጥገኝነትን በመቀነስ ራሱን ችሎ መብቱን እንዲጠይቅና ሀላፊነቱን እንዲወጣ የማስቻል ታላቅ ግብ እንዳለ ታውቆ ሁሉም ባለድርሻ ሊረባረብ እንደሚገባ ተገልጿል።

ዘገባው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

ቀሪ ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜያት እንዲጠናቀቁ ቅንጅታዊ አሰራር ላይ ልናተኩር እንደሚገባ ተገለፀ።             ግንቦት 27/2018 ዓ.ም                         ሀላባየማ...
04/06/2026

ቀሪ ስራዎች በተያዘላቸው ጊዜያት እንዲጠናቀቁ ቅንጅታዊ አሰራር ላይ ልናተኩር እንደሚገባ ተገለፀ።
ግንቦት 27/2018 ዓ.ም
ሀላባ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ዘርፍ በተደረገ ድጋፍና ክትትል መሰረት የተሰሩ ስራዎችን ገመገመ።

ድጋፍና ክትትሉ በተደረገባቸው መዋቅሮች የነበሩ ጠንካራ ጎኖች የሚቀጥሉበት እና የታዩ ውስንነቶችን በቀሪ ጊዜያት በቅንጅት ማሳካት እንደሚገባ ተነስቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዘርፉ ባሉ በሁለቱም ዳይሬክተሮች በቀጣይ በቀሪ ወቅት በልዩ ትኩረት ሊሰሩ በሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ ልዩ ዕቅድ ወቶለት ሊሰራ እንደሚገባ ከመግባባት ተደርሷል።

ዘገባው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የማኔጅመንት ውይይት አደረገ።                         ግንቦት 05/2018 ዓ.ም                         ...
13/05/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የማኔጅመንት ውይይት አደረገ።

ግንቦት 05/2018 ዓ.ም
ሀላባ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አዲስ በሚቀየረው የሰራተኛ መደብ መለያ ቁጥር ዙሪያ የማኔጅመንት አባሉ ሰፊ ውይይት አደረገ።

የቢሮው ሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘውዴ ዩሀንስ በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ አማካኝነት የሰለጠኑትን ስልጠና እና ከቢሮው የተላከውን ሰርኩላር መነሻ ስለሚሰራው ስራ ለማኔጅመንቱ ማብራሪያ የሰጡበትና ከዛን ባሻገር ከአባላቱ በተነሱ ግልፀኝነትን በሚጠይቁ ሀሳቦች ላይ በቂ ማብራሪያ ሰተዋል።

በማጠቃለያውም የቢሮው ሀላፊ ሲያጠቃልሉ ተግባሩን በሰፊው ለመረዳትና ለማስረዳት የተደረገው ጥረት ሚበረታታ ነው። በቀጣይ ባሉን ቀናት ተግባሩ በሰው ሀብት አስተዳደር መሪነት ሌሎች አባላት ተጨምረው በኮሚቴ ታይቶ ለማኔጅመንቱ እንዲቀርብ ተወስኖ የእለቱ ውይይት አብቅቷል።

ዘገባው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሚዲያና ኮሚሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

የማ/ኢትዮ ክልል የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ  የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ የዞንና የልዩ ወረዳ መዋቅሮች ጋር በዙም ወይይት አካሄደ                   ግንቦት 02/2018 ዓ.ም   ...
11/05/2026

የማ/ኢትዮ ክልል የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ የዞንና የልዩ ወረዳ መዋቅሮች ጋር በዙም ወይይት አካሄደ
ግንቦት 02/2018 ዓ.ም
ሀላባ
ዉይይቱን የመሩት የቢሮዉ ም/ሀላፊና የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ በይዳ ሙንዲኖ ሲሆኑ ዉይይቱ በዘርፉ የአዲሱ እሳቤዎች; የኢንደስትሪዎች ምርትና ምርታማነት ምክክር እንዲሁም ኢንደስትሪዎች የስራ ሁኔታ ቁጥጥር መመሪያዎች ላይ ነዉ።
ሁሉም የክልል እና የታችኛዉ መዋቅሮች የምርታማነት ምክክሩ ከፍ ያለ የሰዉ ሀይል ባለባቸዉ ድርጅቶች ላይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተነስቷል።
እንደ ሀላፊዋ ገለጻ አዲሱ እሳቤ፣ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ከኢንዱስትሪ ግንኙነት በላይ መሆኑን አንስተዉ ምርትና ምርታማነትን መሰረት ያደረገ ዉይይት እንዲኖር ፣ ከክርክር ይልቅ ምክክር ማድረግ እንደሚገባና አሰሪዉና ሰራተኛዉ ሁለቱም ወሳኝ በመሆናቸዉ አሰሪው የሰራተኛዉን የሙያ ደህንነት ጤንነት እንዲጠብቅ በትኩረት ተነስቷል ።
በዉይይቱ ሁሉም የዞን መምሪያና ልዩ ወረዳ ጽ/ቤቶች የሰላማዊ ኢንደስትሪ ዳይሬክተር ተወካይ; የስራ ስምሪት አገልግሎት ማስፋፊያ ዳይሬተር ተወካይ እንዲሁም የቁጥጥር ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።
ዘገባዉ የማ/ኢ/ክ/ሰ/ማ/ጉዳይ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው

"አካል ጉዳተኝነትን የሚያካትት ማህበረሰብ መገንባት ለተሻለ ማህበራዊ ዕድገት በሚል መሪ ቃል የአካል ጉዳተኞች ቀን ተከበረ ።                            ሚያዝያ 20/2018 ...
28/04/2026

"አካል ጉዳተኝነትን የሚያካትት ማህበረሰብ መገንባት ለተሻለ ማህበራዊ ዕድገት በሚል መሪ ቃል የአካል ጉዳተኞች ቀን ተከበረ ።
ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም
ሀላባ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከክልሉ አካል ጉዳተኞች ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ34ኛ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ፣ በክልላችን ደግሞ ለ3ኛ ጊዜ ነው።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሠራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሎምባ ደምሴ እንደገለፁት አካል ጉዳተኞች በማሕበረሰቡ ውስጥ ስር ሰዶ በቆየው የተዛባ አመለካከት በቂ ትኩረት ሳይሰጣቸው መቆየቱን አስታውሰዋል።

በዚህም በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ልማቶች አካል ጉዳተኞች ከሌሎች ዜጎች እኩል ተሳታፊ ሳይሆኑ መቆየታቸውን አቶ ሎምባ ተናግረዋል።

አክለውም ችግሩን ለመቅረፍ ማለትም አካል ጉዳተኞች ሀገሪቱ ከምታመነጨው ሀብት እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑና በድህነት ቅነሳ ላይ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ለማድረግ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በመሆኑም አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ የተደነገጉ ሕጎችንና መመሪያዎችን በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ ፍትሓዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥና ብሔራዊ መብቶቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሃጂ ኑርዬ እንደገለፁት የሠላም የፍቅር፣ የብሔር ብሔረሰቦች መገኛ ወደሆነችው ሀላባ ዞን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።

አክለውም መንግስት የአካል ጉደተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የማሕበራዊ ጥበቃ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አቶ ሃጂ ኑርዬ አብራርተዋል።

በአካል ጉዳተኞች ዙሪያ የወጡ ሕጎችን ከመፈጸም አንፃር ግን ክፍተት እንደሚታይ ጠቁመው በተለይም በህንፃ ግንባታ በመንገድ ግንባታ፣ በመረጃ ስርጭትና በሌሎች ዘርፎች የአፈፃፀም ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ አስረድተዋል።

እንደ ሀላባ ዞን አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመው ለአብነት ያህል የብሬል ማዕከልን በማቋቋም ከትምህርት ገበታ ርቀው ለሚገኙ ማየት ለተሳናቸው ልጆች የትምህርት ዕድል በማመቻቸቱ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የደረሱ ተማሪዎች ማብቃቱን ገልፀዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአካል ጉዳተኞች ማሕበራት ፌዴሬሽን ፕረዚዳንት አቶ መሐመድ ሻይቾ በበኩላቸው አካል ጉዳተኝነት ታቅዶ የማይመጣ በመሆኑ የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሕግጋትን ለማሻሻልና በአግባቡ ተግባራዊ ለማድረግ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

አክለውም የሀገሪቷን 15 በመቶ ወይም 800,000 የአካል ጉዳተኞችን ፍትሓዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመሆኑም ሁላችንም በሁሉም ዘርፍ የአካቶ ትግበራ አፈጻጸምን በሚፈለገው ደረጃ ተግባራዊ ለማድረግ በቅንጅት መስራት አለብን ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ቢሮ ማኔጅመንት አባላት፣ የዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሠራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያና ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የክልሉ አካል ጉዳተኞች ማሕበራት አመራሮችና አባላት፣ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።

ዘገባው፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

27/04/2026
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በሀላባ ክላስተር ሲሰጥ የነበረው የአካል ጉዳተኛ ዊልቸር በዛሬው እለትም ከስልጤና ከሀድያ ዞኖች ለተመለመሉ አካል ጉዳተኞች  የማሰራጨ...
04/04/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በሀላባ ክላስተር ሲሰጥ የነበረው የአካል ጉዳተኛ ዊልቸር በዛሬው እለትም ከስልጤና ከሀድያ ዞኖች ለተመለመሉ አካል ጉዳተኞች የማሰራጨት ስራው ቀጥሏል።
መጋቢት 26/2018ዓ.ም
ሀላባ
ዘገባው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።                    መጋቢት 25/2018                              ሀላባ ...
03/04/2026

የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
መጋቢት 25/2018
ሀላባ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ''አጋፔ ሞቢሊቲ ኢትዮጵያ'' ከተባለ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ለአካል ጉዳተኞች የዊልቸር ድጋፍ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አደረገ።

የክልሉ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሉምባ ደምሴ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት የአካል ጉዳተኛ ወገኖች በማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ተጋላጭ ማህበረሰብን ማገልገል አካል ጉዳተኛ ዜጎች ትርጉም ያለው ህይወት እንዲኖራቸው ያደርጋል ያሉት ሀላፊው ድጋፉ አካል ጉዳተኞች ራሳቸውን ችለው በመንቀሳቀስና በመስራት ኑሯቸውን አሸንፈው ለሌሎች እንዲተርፉ አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል።

መንግስት ከአጋር አካል ጋር በመቀናጀት በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ የሚደርሱ ጉዳቶች ዜጎችን ከእንቅስቃሴ እንዳይገድባቸው የአካል ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል ብለዋል።

የቢሮው ምክትልና የማህበራዊ ጉዳዮች ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም ሳሙኤል በበኩላቸው ቢሮው ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን በመደገፍ በገቢ ማስገኛና በተለያዩ ዘርፎች ራሳቸውን እንዲችሉ እየሰራ ነው ብለዋል።

መሬት የመንፏቀቅ ዘመን ያበቃል በሚል መሪ ቃል አጋፔ ሞቢሊቲ ኢትዮጵያ ዘመናዊ የሆኑ ዊልቸሮችን በማቅረብ የአካል ጉዳተኞችን ችግር እያቃለለ ይገኛል ያሉት ሀላፊዋ በተለያዩ ጊዜያት ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት 223 የዊልቸር ድጋፍ ድርጅቱ ለክልሉ ማድረጉን ተናግረዋል።

አካል ጉዳተኞች እንዲማሩ ፣ሰርተው ራሳቸውን እንዲችሉና ከማህበረሰቡ ጋር እንዲቀላቀሉ የዊልቸር ድጋፉ አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን የተናገሩት ወይዘሮ ሠርካለም የአካል ጉዳተኞች በመናኸሪያ ውስጥ በእንቅስቃሴ እንዳይቸገሩ ለ20 መናኸሪያዎች 20 የዊልቸር ድጋፍ መደረጉንም አስታውቀዋል።

በዛሬው ዕለት ለሀላባ፣ለከምባታ ዞኖችና ለጠምባሮ ልዩ ወረዳ ድጋፍ መደረጉንና በነገውም ለሀዲያና ለስልጤ ዞኖች ተመሳሳይ ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን የተናገሩት ወይዘሮ ሠርካለም ከዚህ ቀደም ለሦስት ዞኖችናና ለሁለት ልዩ ወረዳዎች ድጋፉ የተደረገ ስለመሆኑ አስታውቀዋል።

የአጋፔ ሞቢሊቲ ኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ አቶ ሚኪያስ ዘላለም አንደገለጹት ዛሬ የተደረገው ድጋፍም አካል ጉዳተኞች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው እንዲሰሩ እንዲሁም ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ምቹ እድል ይፈጥራልም ብለዋል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ለሴክተሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።           ...
02/04/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ለሴክተሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።
መጋቢት 24/2018 ዓ.ም
ሀላባ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ም/ሀላፊና የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ በይዳ ሙንዲኖ የእለቱን መድረክ በመክፈቻ ንግግር አስጀምረዋል።

በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት ምርታማነትን ማዕከል ያደረገ ችግሮችን በመለየት ለችግሮቻቸው መፍትሄ በማስቀመጥ ምርታማነት በማሳደግ የዜጎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሲባል የኢንዱስትሪ ማህበረሰብ ምክክር አስፈላጊ ሆኗል።

ወ/ሮ በይዳ በንግግራቸው አክለውም የኢንዱስትሪ ማህበረሰብ ምክክር ለምርታማነት በአግባቡና በሚፈለግበት ደረጃ በማካሄድ በአጭርና በረዥም ጊዜ አዎንታዊ ለውጥ እንዲያመጣ ይጠበቃል ብለዋል።

የአቅም ግንባታ ስልጠናው የተሰጠው በዘርፉ አዲስ እሳቤዎች፣ በኢንዱስትሪ ማህበረሰብ ምርታማነት ምክክር እና የስራ ሁኔታ ተቆጣጣሪዎች የትግበራ ማንዋል ላይ ሲሆን

የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ መሆን እንዳለበትና Win-Win የሆነ ግንኙነት መፍጠር እንደሚገባ በመድረኩ ተነስቷል።

የስራ ሁኔታዎች ቁጥጥር አገልግሎቶች ወጥ፣ ችግር ፈቺ፣ ቀጣይነት ያላቸው፣ ወጪ ቆጣቢና ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ማስቻል እንደሚጠይቅ ተነስቷል።
ዘገባው የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የማህበራዊ ዘርፍ በሀላባ ክላስተር ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች የሚሰራጭ  ከ110 በላይ የዊልቸር ገጠማ  ስራ እየተከናወነ ይገኛል።ዘገባው...
01/04/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የማህበራዊ ዘርፍ በሀላባ ክላስተር ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች የሚሰራጭ ከ110 በላይ የዊልቸር ገጠማ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

ዘገባው:- የክልሉ ሰራተኛና ማህበራዊ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

Address

Lalibela
62

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share