13/06/2026
የወረዳ ደረጃ ማህበረሰብ ተኮር የጥበቃና የዕቅድ ዝግጅት ስብሰባ በቡታጅራ ከተማ ተከናወነ።
ሰኔ 6/2018
ሀላባ
የክልሉ ሰራተኛና ማህበራዊ፣ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ እንዲሁም የአለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት ተወካዮች የተገኙበት ስብሰባ ተከናውኗል።
ስብሰባውን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሉምባ ደምሴ እንደገለፁት ሁሉም ባለድርሻ አካል በተሰጠው ሀላፊነት ስራዎችን በቅንጅትና በትብብር ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።
የመድረኩ ዋና ዓላማ ከመኖሪያቸው ለተፈናቀሉ፣ ከፍልሰት ለተመለሱ ወገኖቻችንና ለአከባቢው ተቀባይ ማህበረሰቦች ዘላቂ ጥበቃን፣ መልሶ መቋቋምን፣ ማህበራዊ ውህደትንና በሰላም አብሮ መኖርን በጋራ ለማጠናከር ያለመ መሆኑን አንስተዋል።
ይህ ዕቅድ ሰው ላይ ያተኮረ፣ ችግር ላይ ሳይሆንበአከባቢያችን ያሉ ጠንካራ ጎኖችና መልካም ዕድሎች ላይ መሰረት ያደረገ እንዲሆን እንደሚፈለግና ማህበረሰቡ የዕቅድ ዝግጅቱን የእኔ ነው ብሎ እንዲቀበል፣ ጥገኝነትን በመቀነስ ራሱን ችሎ መብቱን እንዲጠይቅና ሀላፊነቱን እንዲወጣ የማስቻል ታላቅ ግብ እንዳለ ታውቆ ሁሉም ባለድርሻ ሊረባረብ እንደሚገባ ተገልጿል።
ዘገባው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።