የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

  • Home
  • Ethiopia
  • Lalibela
  • የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት  የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት, Public & Government Service, Lalibela.

,,,የበጎነት ተግባር በሁሉም መስክ  ተጠናቅሮ ቀጥሏል።ጳጉሜ 4/2018 የት/ቁሳቁስ ድጋፍ ሥርጭት ለአቅመ ደካመ ቤተሰብ ተማሪዎች፣ ቤት ማስጀመርና አጠናቆ ለተጠቃሚዎች ማስረከብ፣ የማእድ ማ...
09/09/2026

,,,የበጎነት ተግባር በሁሉም መስክ ተጠናቅሮ ቀጥሏል።
ጳጉሜ 4/2018
የት/ቁሳቁስ ድጋፍ ሥርጭት ለአቅመ ደካመ ቤተሰብ ተማሪዎች፣ ቤት ማስጀመርና አጠናቆ ለተጠቃሚዎች ማስረከብ፣ የማእድ ማጋራት፣ የአልባሳት ድጋፍ፣ ለአካል ጉዳተኞች የዊልቸር ስርጭት ስራዎች በመዋቅሮቻችን በሰፊው ቀጥሏል።

የምስጋና መልዕክት፦*በክቡር አቶ ሉምባ ደምሴ የሰራተኛና ማህበራዊ ቢሮ ሀላፊ የተላለፈ የምስጋና መልዕክት፦የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ  ባለፉት ሶስት ዓመታት በጥቅ...
03/09/2026

የምስጋና መልዕክት፦
*
በክቡር አቶ ሉምባ ደምሴ የሰራተኛና ማህበራዊ ቢሮ ሀላፊ የተላለፈ የምስጋና መልዕክት፦

የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ባለፉት ሶስት ዓመታት በጥቅሉ በ2018 በጀት አመት ደግሞ በተለየ የዋና ዋና ስትራቴጂክ ግቦች አፈጻጸም እና በተቋም ግንባታ ስራዎች ላይ የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገቡ ከኢፌዴሪ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር እውቅናና ሽልማት ተበርክቶልናል። ለዚህ ውጤት በትጋት፣ በቁርጠኝነትና በተቀናጀ መንገድ ለፈጸማችሁና ላስተባበራችሁ አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ አመራሮችና ባለሙያዎች ልባዊ ምስጋና ይድረሳችሁ።

ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ክቡር የክልላችን ፕሬዚዳንት እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አመራሮች በሰጡት ልዩ ትኩረትና በየወቅቱ በሚያስቀምጡት አቅጣጫዎች እና ክትትልና ድጋፍ ስለሆነ ከልብ አናመሠግናለን።

በየደረጃው የሚገኙ የዞን/ልዩ ወረዳ የከተማ አስተዳደር እና የወረዳ የሴክተሮቹ አመራሮችና ባለሙያዎች ለዚህ ውጤት መምጣት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋልና እናመሠግናለን።

ከሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የተሰጠን እውቅና በቀጣይም በሴክተሩ ለጀመርነው ጠንካራ ስራ አቅም ስለሚሆነን ትልቅ መነሳሳትና ተጨማሪ ሀላፊነት ሰጥቶናል። ይህንንም የበለጠ ለመስራት ቃል እንገባለን።
ለዚህ ስኬት ስለበቃን እንኳን ደስ አላችሁ፣
ላደረጋችሁት አስተዋፅኦ ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን!

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ በክልሉ ባሉ መዋቅሮች በርካታ የበጎ ተግባራትን እየመራና እያስተባበረ ይገኛል። በተግባሩም  በርካታ ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍ...
02/09/2026

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ በክልሉ ባሉ መዋቅሮች በርካታ የበጎ ተግባራትን እየመራና እያስተባበረ ይገኛል። በተግባሩም በርካታ ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን መደገፍ እንደተቻለ ይታወቃል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ቢሮው በሀዲያ ዞን ጊንቢቹ ከተማ አስተዳደር እያስገነባ የሚገኘው የአቅመ ደካማ ቤት ስራው በቅንጅትና በትብብር እየተሰራ ያለና ዛሬ ላይ ቆርቆሮ የማልበስ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

የሥራ ስምሪት ማዕከላትን ለማጠናከር የሁለት ቀናት አውደ ጥናት ተጀመረ።           ነሀሴ 22 /2018 ዓ ም ሀላባ  በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና በዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (...
28/08/2026

የሥራ ስምሪት ማዕከላትን ለማጠናከር የሁለት ቀናት አውደ ጥናት ተጀመረ።

ነሀሴ 22 /2018 ዓ ም ሀላባ

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና በዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ትብብር በተሻሻለው የፍልሰት አስተዳደር (BRMM) መርሃ ግብር ስር፣ በሆሳዕና ከተማ የሥራ ስምሪት ማዕከላት ማረጋገጫ አውደ ጥናትና የባለድርሻ አካላት ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር ተጀምሯል።

በሻምበላላ ሆቴል እየተካሄደ ያለው የሁለት ቀናት መርሃ ግብር የሥራ ስምሪት ማዕከላትን አቅምና የአገልግሎት ክፍተት ለመለየት፣ የማዕከላቱን አገልግሎት ለማሻሻል እና በተለያዩ ባለድርሻ አካላት መካከል ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው።

በመርሃ ግብሩ የተደረገው የፈጣን የፍላጎት ግምገማ (Rapid Needs Assessment) እና የሥራ ገበያ ባለድርሻ አካላት ካርታ ግኝቶች ይገመገማሉ። በተጨማሪም የማዕከላቱ ተልዕኮ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ሞዴሎችና የማጣቀሻ መንገዶች ላይ ግንዛቤ ይሰጣል።

በተለይም በሀላባ፣ ዱራሜ፣ ሆሳዕና፣ ወራቤ እና ቡታጂራ ከተሞች የታዩ መልካም ተሞክሮዎች በመቀመር ከተለያዩ ደረጃዎች አስተባባሪዎች ጋር ልምድ ለመለዋወጥ መድረኩ ዕድል ይፈጥራል።

መርሃ ግብሩ ከመንግሥት አካላት፣ ከማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት፣ ከግል ሴክተር ቀጣሪዎችና ከልማት አጋሮች ጋር ትብብርን በማጠናከር ለወደፊቱ የሚያገለግል ጠንካራ የድርጊት መርሃ ግብር ለማዘጋጀት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ IOM፣ ATI (አደይ ፕሮግራም)፣ MESMER እና ደስታ ጋርመንት የመሳሰሉ የልማትና የኢንዱስትሪ አጋሮች ተሳትፎ እያደረጉ ሲሆን፣ የሥራ ስምሪት ማዕከላት ወጣቶች የሥራ ገበያ መረጃ እንዲያገኙና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥራ ስምሪት እንዲያገኙ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቁሟል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎች ልምዶቻቸውን በማካፈል፣ ግልጽ ውይይት በማድረግና ገንቢ ግብረ-መልስ በመስጠት የሥራ ስምሪት ማዕከላትን ውጤታማነት ለማሳደግ እንደሚሰሩ ተገልጿል።

መዋቅሮቻችን በተቀናጀና ሁሉ አቀፍ በሆነ መልኩ በሰፊው እንደየ አከባቢው ተጨባጭ ሁኔታ በተለያዩ የትኩረት መስኮች እየተከናወኑ መሆኑ ይታወቃል። የተከናወኑ ስራዎች በምስል በከፊል:-
27/08/2026

መዋቅሮቻችን በተቀናጀና ሁሉ አቀፍ በሆነ መልኩ በሰፊው እንደየ አከባቢው ተጨባጭ ሁኔታ በተለያዩ የትኩረት መስኮች እየተከናወኑ መሆኑ ይታወቃል። የተከናወኑ ስራዎች በምስል በከፊል:-

25/08/2026
24/08/2026
ህገ-ወጥ ፍልሰትን በመከላከል ወጣቶች በአካባቢያቸው ሠርተው ራሳቸውንና ማህበረሰባቸውን  ሊለውጡ ይገባል ተባለ                       (ሀላባ፣ ነሃሴ 16/2018)የማዕከላዊ ኢትዮ...
22/08/2026

ህገ-ወጥ ፍልሰትን በመከላከል ወጣቶች በአካባቢያቸው ሠርተው ራሳቸውንና ማህበረሰባቸውን ሊለውጡ ይገባል ተባለ
(ሀላባ፣ ነሃሴ 16/2018)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከዓለም አቀፍ ፍልሰት ድርጅት (IOM) ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የማህበረሰብ አቀፍ የዕቅድ ዝግጅት ትግበራ ማብሰሪያ መርሃ ግብር በከምባታ ዞን ዳምቦያ ወረዳ ቦንጋ ቀበሌ ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የመሠረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ መዘረዲን ሁሴን፣ ህገ-ወጥ ፍልሰትን በመከላከል ወጣቶች በአካባቢያቸው ሠርተው ራሳቸውንና ማህበረሰባቸውን ሊለውጡ ይገባል ብለዋል።

የምርታማነት ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወጣቶችና ተዛማጅ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉልበታቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ሀብታቸውን በመጠቀም የመኖሪያ አካባቢያቸውን ምቹ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

ተግባሩ ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ሳይሆን በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ አካላት የጋራ ትብብር የሚጠይቅ መሆኑንም አቶ መዘረዲን አመላክተዋል።

የህግ ወጥ ፍልሰት በዜጎች ላይ የሚያደርሰው ኢኮኖሚና ማህበራዊ ቀውስ ብሎም ሰብዓዊ መብት ጥሰት በእጅጉን የከፋ ስለመሆኑ ገልፀው፣ መንግስት ባመቻቸው የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት መንገድ በመሄድ ከዚህ አስከፊ ጉዳት ዜጎች እራሳቸውን እንዲጠብቁም አሳስበዋል።

ህገ ወጥ ፍልስት በዜጎች ላይ የሚያደርሰው የጉልበት ብዝበዛና እንግልት ከፍተኛ በመሆኑ በአካባቢያቸው በማልማት ምቹ አካባቢን ከመፍጠር ባሻገር ምርታማነትን ማሳደግ ይቻላል ብለዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሉምባ ደምሴ፣ የማህበረሰብ የድርጊት መርሃ-ግብሩ የቀበሌው ነዋሪዎች ከአካባቢው አመራሮች ጋር በመቀናጀት ችግሮቻቸውን በዝርዝር የለዩበት፣ አቅሞቻቸውን የገመገሙበት እና የወደፊት ተስፋቸውን በራሳቸው እጅ የጻፉበት እውነተኛ የማህበረሰብ ባለቤትነት ውጤት ነው ብለዋል፡፡

ማህበረሰቡ በራሱ ተሳትፎ ያዘጋጀውን የልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ እቅድ ማስተዋወቅ፣ አጋርነትን፣ ባለቤትነትንና ተጠያቂነትን ለማጠናከር ታልሞ የተዘጋጀ መድረክ ስለመሆኑ አቶ ሉምባ ገልፀዋል።

የታቀዱት የልማት፣ የሥራ ስምሪት እና የማህበራዊ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ከወረቀት ወጥተው የቦንጋ ቀበሌን ማህበረሰብ ህይወት የሚቀይሩት በሁሉም የተቀናጀ ጥረት መሆኑን አቶ ሉምባ ተናግረዋል።

የማህበረሰቡን ጥረት በመደገፍ፣ የሀብት አቅጣጫዎችን በማመቻቸት እና አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ የተለመደ አጋርነታችሁን እንድታጠናክሩ ሲሉም አቶ ሉምባ ለባለድርሻ አካላት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የቀበሌው ማህበረሰብም የተጀመረውን የባለቤትነት መንፈስ አጠናክሮ በማቀጠል ለዕቅዱ ስኬታማነት በግንባር ቀደምትነት የበኩላቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል።

የከምባታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተሾመ ሄራሞ በበኩላቸው፣ በህገወጥ ፍልሰት ወጣቶች ከሀገር ሲወጡ ለተለያዩ ሰብዓዊ ጥሰት እንደሚጋለጡ ጠቁመዋል።

ወጣቶች መንግስት በሚያመቸቸው የስራ ዕድል በሀገር ውስጥ ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉም ጠቁመው፣ ሀገ ወጥ ፍልሰትን ምርጫቸው ሊያደርጉ አይገባም ሲሉም አሳስበዋል።

በመድረኩ የማህበረሰብ የድርጊት መርሃ ግብር ማስፈፀሚያ የግብ ስምምነት ፊርማ ስነ ስርዓትም ተካሂዷል።

የ2018/19 የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በሁሉም የስምሪት መስኮች ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ለአረጋውያን ለአቅመ ደካማና ልዩ ልዩ ተጋላጭ ወገኖች በተለያዩ መስኮች በርካታ ስራዎች እየተሰሩ...
21/08/2026

የ2018/19 የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በሁሉም የስምሪት መስኮች ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ለአረጋውያን ለአቅመ ደካማና ልዩ ልዩ ተጋላጭ ወገኖች በተለያዩ መስኮች በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል። ከተሰሩ ስራዎች ከብዙ በጥቂቱ በምስል:-

20/08/2026

Address

Lalibela
62

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share