የገ/ጉ/ወ/ወረዳ የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Kokir
  • የገ/ጉ/ወ/ወረዳ የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወረዳ የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት Governmental institution at Central Erhiopia-Guraghe Zone- G/G/W/W/- Mehal Amba.

It is governmental organization at SNNP,Guraghe zone,Gedebano Gutazer Wolene Woreda,Mehal Amba town.

ግንቦት 28/2018 ዓ/ምየጉራጌ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት ወቅታዊና መደበኛ ስራዎችን በመገምገም የበጀት አመቱ ቀሪ ስራዎች በሚቀጥሉት 20 ቀናት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ አስቀመጠ!!፨፨፨፨፨//...
05/06/2026

ግንቦት 28/2018 ዓ/ም
የጉራጌ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት ወቅታዊና መደበኛ ስራዎችን በመገምገም የበጀት አመቱ ቀሪ ስራዎች በሚቀጥሉት 20 ቀናት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ አስቀመጠ!!
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ እንዲሁም የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን የመስተዳደሩ ምክር ቤት አባላት በተገኙበት ወቅታዊና መደበኛ የንቅናቄ ስራዎች በወልቂጤ ከተማ ገምግመዋል።

ምክትል አስተዳዳሪው የገጠርና የከተማ ኮሪደር ልማት ስራዎች፣የገቢ ፣ የፋይዳ መታወቂያ ስርጭት፣የኢቲዮ ኮደርስ ስልጠና፣የንግድ፣የስራ እድል ፈጠራና የነዳጅ ስርጭት ሁኔታ የደረሱበት አፈፃፀም ገምግመው በቀጣይ 20 ቀናት ታቅደው መሰራት ባለባቸው ተግባራት ላይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

አቶ አበራ ወንድሙ እንደገለፁት የህብረተሰባችን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ በገበያ ዋጋ ማረጋጋት ላይ የምንሰራው ስራ ልዩ ትኩረት ልንሰጠው ይገባል::
በነዳጅ አቅርቦት ስጭትና ህገወጥነቶች ላይ እየተሰሩ ያሉት ስራዎች ውጤት እያስገኙ ቢሆንም አሁንም ቀሪ ስራዎች ስላሉ አቅዶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በተለይም ህገ ወጥ የነዳጅ ክምችት በሚያደርጉና በአላስፈላጊ መንገድ ነዳጅ እየሸጡ የሚገኙ አካላት ላይ ልዩ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በሚቀጥሉት 20 ቀናት ያላሳካናቸው ቀሪ የአመቱ እቅዶቻችንን ሙሉ በሙሉ ልናሳካ ይገባል ያሉት አቶ አበራ በተለይም የገቢ ስራችን ያሉንን እድል ሁሉ ተጠቅመን ገቢን አሟጣን ልንሰበስብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በገቢ አሰባሰብ ላይ አፈፃፀማቸው ከዞን አማካይ በታች የሆኑ መዋቅሮች በሚቀጥሉት 20 ቀናት በልዩ ሁኔታ እቅዳቸውን ሊያሳኩ እንደሚገባም አፅንዎት ሰጥተዋል።
በዞኑ የተከለሰውን የገቢ እቅድ ጨምሮ እስካሁን ለመሰብሰብ ከታቀደው ከ83 በመቶ በላይ መሰብሰብ መቻሉን የጠቀሱት ምክትል አስተዳዳሪው እስከ ሰኔ 30 ድረስ ከ810 ሚሊየን ብር በላይ ለመሰብሰብ መስራት ይገባል ብለዋል።

ካለ ፋይዳ መታወቂያ ምንም አገልግሎት ማግኘት የማይቻልበት ደረጃ እየደረስን እንደሆነ ልናውቅና ህዝቡንም ልናሳውቅ ይገባል ያሉት አቶ አበራ በተያዘው በጀት አመት 100% ለማሳካት መስራት እንደሚገባ በማመላከት አሁን ከደረስንበት አፈፃፀም አንፃር ሰፊ ውስንነት እንዳለ ጠቁመዋል
የከተማ ኮሪደር ልማት በአምስቱም ከተሞች በተጀመረው መልኩ ተጠናክሮ በፍጥነትና በጥራት ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የገጠር ኮሪደር በተመለከት ከሌማት ትሩፋትና ከፅዱ መንደር ጋር ማያያዝ ያስፈልጋል በማለት
ሞዴል የገጠር መንደር መፍጠ ላይ ታዳጊ ማዘጋጃዎች ላይ ቦታ መርጠን ወደ ተግባር ልንገባ ይገባል።
ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር ያሉ ስራዎች እድገት ቢያሳዩም በelmis ከመመዝገብ አንፃር ግን ያሉ ውስንነቶች እንዲታረሙና የተለዩ ስራ አጥ ዜጎችም ከአጋሮች ጋር በመሆን ወደ ስራ የሚገቡበት መንገድ ለማመቻቸት እየተደረገ ያለው ጥረት መጠናከር ይገባዋል ብለዋል።

የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የነገይቱን ኢትዮጵያን ከአለም ጋር ተፎካካሪ ለማድረግ ያለመና ለቴክኖሎጂ ቅርብ የሆነ ትውልድ ለመፍጠር የተለመ ፕሮግራም እንደሆነ በመረዳት ስራው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

ስልጠናው ከመስጠት ባሻገር ስልጠናውን ተጠቅመው ገቢ ማግኘትና ፈጠራ የጀመሩ ልጆችን ማበራከትና ለሚዲያ ማቅረብ ይገባል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን በበኩላቸው የተቀመጡት አቅጣጫዎች በ20 ቀናት ውስጥ መፈፀም እንደሚገባና አመራሩ ሌሎች ትላልቅ ተግባራት በመራበት አግባብ ስራዎቹን እንዲመራ አሳስበዋል።
ወቅታዊ የግብርና የትምህርትና የጤና ስራዎችም አቀናጅቶ መምራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
መረጃው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

ግነቦት 27/2018 ዓ/ምበአስገድዶ መድፈር  ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ17 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ተከሳሽ መሃመድአሚን አረብ የተባለው ግለሰብ በቀን 12/08/20...
04/06/2026

ግነቦት 27/2018 ዓ/ም
በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ17 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨

ተከሳሽ መሃመድአሚን አረብ የተባለው ግለሰብ በቀን 12/08/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 አካባቢ ላይ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰፋቶ ቀበሌ ልዩ ስሙ አዳር ገበያ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የግል ተባዳይ የሆነችውን ነዚፋ ሸምሱን ዕድሜዋ 5 ሲሆን እናትሽ እየጠራችሽ ነው በማለት ከምትጫወትበት ስፍራ አታሎ በመውሰድ ቤት ውስጥ በማስጋባት የግብር ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ፈፅሞባታል በሚል በወረዳው ዓ/ህግ ክስ የተመረተበት ሲሆን ተከሳሽም ድርጊቱ አልፈፀምኩም በማለት ክዶ ተከራክሯል።

ዓ/ህግ አሉኝ የሚላቸው የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን በማቅረብ ካሰማ በኃላ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ይከላከል በማለት ብይን ቢሰጥም ተከሳሽ በተከሰሰበት ድንጋጌ ሊከላከል ባለመቻሉ ተከሳሽ ጥፋተኛ ሲል ፍርድ ሰጥቷል ።
በመቀጠልም ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት የተቀበለ ሲሆን በዚህም ተከሳሽ ጥፋተኛ የተባለበት የወንጀል ህግ ድንጋጌ በተሻሻለው የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2016 መሰረት ደረጃ 5 እና እርከን 42 የሚያርፍ ነው ።
ዓ/ህግ ድርጊቱ የተፈፀመው በእድሜዋ ምክንያት እራሷን መከላከል በማትችል ህፃን ልጅ ላይ ነው በማለት በወንጀል ህጉ አንቀጽ 84(1)(ሠ) መሰረት አንድ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ያቀረበ በመሆኑ ከእርከን 42 ወደ እርከን 43 ከፍ ይላል በመቀጠልም ተከሳሽ ሶስት የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶችን ጠቅሶ አቅርቧል 1ኛ የወንጀል ሪከርድ የለብኝም 2ኛ ታማሚ የሆኑ ቤተሰቦቼን የምንከባከበው እኔ ነኝ 3ኛ ያለኝ የትምህርት ደረጃ ዝቅተኛ ነው በማለት ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ሶስቱን የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶችን በመቀበል ከእርከን 43 ወደ 40 ዝቅ አድርጎታል ።

ፍርድ ቤቱም እርከን 40 ከሚያስቀምጠው ከ17 ዓመት እስከ 19 ዓመት ፅኑ እስራት ውስጥ ተከሳሽን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል ያለውን የ17 ዓመት ፅኑ እስራትን ወስኗል ።
መፈጃው የወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት ነው።

ከድምፅ መስጫ እስከ ውጤት ማፅደቅ ያለው ዑደት
04/06/2026

ከድምፅ መስጫ እስከ ውጤት ማፅደቅ ያለው ዑደት

ሰላም! እንደምን አደራችሁ?ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የ...
03/06/2026

ሰላም! እንደምን አደራችሁ?

ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።

በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።

በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።

በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።

የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።

በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።

በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።

ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።

በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።

በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።

የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።

ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!

ግንቦት 25/2018 ዓ/ም7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቅቋል - ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቅቋል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ። 7ኛው...
02/06/2026

ግንቦት 25/2018 ዓ/ም
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቅቋል - ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቅቋል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ።

7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ በግንቦት 24 ቀን ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ድምጽ ሲሰጥ የዋለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቅቋል ብለዋል።

በድምጽ ምስጫ ሂደቱ በአዲስ አበባ ከተማ በጣም ረጃጅም ሰልፎች እንደነበሩ አንስተው÷ በሲዳማ፣ ጋምቤላ፣ አማራ፣ ሶማሌ ክልሎች የድምጽ ቆጠራ አለመጠናቀቁን ገልጸዋል።

በዚህም የመራጮች ቁጥር እስካሁን ተጠቃሎ አለመግባቱን ተናገረዋል።

ቦርዱ የተለያዩ ቅሬታዎች በተለያየ መንገድ ሲያስተናግድ መቆየቱን አንስተው÷ በሕግ ክፍል በኩል በቀጥታ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲ የስራ ክፍል አማካይኝነት በቅድመ ማስጠንቀቂያ 6412 ስልክ ቁጥር የመጡ ጥቆማና ቅረታዎች እንደነበሩ አመልክተዋል።

በዚህም ጥቆማውን በመከተል ከስር ከስር አስፈላጊውን የእርምት ርምጃ ቦርዱ ሲሰጥ መቆየቱን እንዲሁም የማጣራት፣ የማረጋገጥና ማስረጃ ማጠናቀር በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

FMC

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የውጤት አሰጣጥ የጊዜ ሰሌዳ
02/06/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የውጤት አሰጣጥ የጊዜ ሰሌዳ

በድህረ ምርጫ ወቅት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ምንድናቸው?7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትናንትናው ዕለት በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ሀገራችን በአሁኑ ወቅት አዲስ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖ...
02/06/2026

በድህረ ምርጫ ወቅት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ምንድናቸው?

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትናንትናው ዕለት በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ሀገራችን በአሁኑ ወቅት አዲስ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አቅጣጫ የሚቀረጽበት ወሳኝ የድህረ ምርጫ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ይህ ወቅት የምርጫ ሂደት የመጨረሻው ምዕራፍና የሕዝብ ድምፅ ወደ ተግባራዊ መንግሥታዊ ሥራ የሚቀየርበት ወሳኝ ድልድይ ነው፡፡

በዚህ ወሳኝ የድህረ ምርጫ ምዕራፍ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፦

በየምርጫ ጣቢያው የተሰጡ ድምፆች በግልጽነት ተቆጥረውና ተረጋግጠው በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኩል ጊዜያዊ እና የመጨረሻ ውጤቶች ለሕዝብ ይፋ ይደረጋሉ፡፡

በተያያዥም የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በሂደቱ ላይ ያስተዋሏቸውን ጠንካራና ደካማ ጎኖች የያዘ ይፋዊ መግለጫ እና ምክረ-ሀሳብ ያቀርባሉ፡፡

በሂደቱ ወይም በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወይም የግል እጩዎች ያቀረቧቸውን አቤቱታዎች የምርጫ ቦርድ እና ፍርድ ቤቶች መርምረው ሕጋዊ ውሳኔ የሚሰጡበት ወቅት በመሆኑ፣ ማንኛውም ውዝግብ በሰላማዊና በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲፈታ ይደረጋል፡፡

በተጨማሪም የምርጫ አስፈጻሚው አካል የሰው ኃይል፣ የቴክኖሎጂ እና የበጀት አጠቃቀሙን የሚገመግምበት ሲሆን፣ ሂደቱ በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካ ሥልጣን ሽግግር የሚከናወንበት የሕግ የበላይነት መገለጫ ነው፡፡
(EBC)

ግንቦት 25/2018 ዓ/ምየገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በትላንትናው ዕለት የተካሄደውን የ7ተኛ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በወረዳው ካለምንም የፀጥታ...
02/06/2026

ግንቦት 25/2018 ዓ/ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በትላንትናው ዕለት የተካሄደውን የ7ተኛ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በወረዳው ካለምንም የፀጥታ ችግር በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ አስተዋፅዎ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቀረቡ።
፨፨፨፨፨////፨፨፨፨፨
ሀገራችን ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመገንባትና የህዝቧን የሉዓላዊነት ስልጣን ለማረጋገጥ በከፍተኛ ቁርጠኝነት በጀመረችው ጉዞ ውስጥ፣ የወረዳችን ህዝብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ያሳየው ከፍተኛ ተሳትፎና የሰለጠነ ዲሞክራሲያዊ ባህል አዲስ ታሪክ የጻፈ ስኬት ሆኖ መመዝገቡን አቶ ሚፋታ ሁሴን አስታውቀዋል።

አቶ ሚፋታ በመልእክታቸው ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻችሁን ለተወጣችሁ በሙሉ በተለይም በከተማና በገጠር ለሚገኘው ህዝባችን ምርጫው በሁሉም አካባቢ ተመሳሳይ ድጋፍ በመስጠት ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ላደረገው አስተዋጾ በወረዳው አስተዳደር እና በራሳቸው ስም የላቀ ምስጋና አቀርበዋል።

የወረዳው ህዝብ ከለሊቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ምርጫ ቦርድ የምርጫው ሂደት መጠናቀቁን እስኪያሳውቅ ጊዜ ድረስ ብርድ፣ውርጩ፣ዝናቡ፣ህመሙ፣ ፀሃይና ሀሩሩ ሳይበግረው እንደዚሁም የሙስሊሙ ህብረተሰባችን ሀገር ስትቀጥል ነው በዓልን ተረጋግቶ ማክበር የሚቻለው በማለት ምርጫውን በሰላማዊ መንገድ ሲያካሄድ በመዋሉ ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።

የወረዳችን የፀጥታ አካላት ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ የምርጫ ቁሳቁስ በመጠበቅ፣በማጓጓዝ፣ እንደዚሁም በየምርጫ ጣቢያው የፀሃዩ ሙቀት፣ብርድና ውርጩን ችለው መኝታና ምግብ ሳይመቻችላቸው ከሁሉም ነገር ሀገር ትበልጣለች በማለት ካለምንም የፀጥታ ስጋትና ችግር ህዝቡ በሰላም መርጦ እንዲመለስ በማድረግ ላደረጉት አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን ችረዋል!!

በዘንድሮ የምርጫ ስራችን ላይ የታየው ሁለንተናዊ ድጋፍ፣ ጠንካራ ትብብርና መተጋገዝ የወረዳችን ሕዝብ ታላቅነትና አንድነት ዳግም ያስመሰከረ ሆኗል በመሆኑም በተደረገው ዘርፈ-ብዙ ድጋፍ የተሰማቸውን ታላቅ ክብርና ምስጋና በድጋሚ አቅርበዋል።

ምርጫው በሰላም መጠናቀቁ የትግላችን መጀመሪያ እንጂ መድረሻችን አይደለም በቀጣይ ጊዜያትም ይህንን የሰላም አየር ተጠቅመን፣ በአሁኑ ወቅት ትኩረት በተሰጣቸውና እየተከናወኑ ባሉ ወቅታዊ የልማት አጀንዳዎቻችን ላይ ይበልጥ በማተኮር፣ ለውዷ ሀገራችን ብልፅግናና ለአካባቢያችን ዕድገት በጋራና በቁርጠኝነት እንድንተጋ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

ግንቦት 24/2018 ዓ/ምየ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል - ቦርዱ የድምፅ መስጠት ሒደቱ ከ12 ሰዓት በፊት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮ...
01/06/2026

ግንቦት 24/2018 ዓ/ም
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል - ቦርዱ

የድምፅ መስጠት ሒደቱ ከ12 ሰዓት በፊት ሰልፍ ይዘው የቆዩ መራጮች እስኪመርጡ ይቀጥላል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡

በዛሬው ዕለት ከጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝቡ በነቂስ በመውጣት ድምጹን እየሰጠ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሒደት ላይ መሆኑ ይታወቃል።

ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሒደቱ እስከ 12 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሒደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!! 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርአት ከማለደው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በጉራጌ ዞን ኮኪር ምርጫ ክልል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሚገኙ የተለያዩ የ...
01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!!

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርአት ከማለደው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በጉራጌ ዞን ኮኪር ምርጫ ክልል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በይፋ እየተካሄደ ይገኛል።

በርካታ ዜጎች በወሰዱትን ካርድ የሚመራቸውን ፓርቲ ለመምረጥ ማልደው በምርጫ ጣቢያዎቹ ተገኝተዋል።

Address

Kokir

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የገ/ጉ/ወ/ወረዳ የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የገ/ጉ/ወ/ወረዳ የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት:

Share