21/05/2026
በጸና እና በተደራጀ የሴቶች ድምፅ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እናሻግራለን በሚል መሪ ቃል በደዋ ጨፋ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት የሴቶች የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በሸክላ ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የደዋ ጨፋ ወረዳ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጌታቸው ሲሆኑ የሰልፉ አላማ ሴቶች እስከ ዛሬ ያሳዩትን ቁርጠኝነት ግንቦት 24/2018 በሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ላይ እንዲደግሙ ማስቻልና ሴቶች የብልፅግና ተምሳሌትነታቸውን አጠናክረው እንዲሄዱ ማስቻል ነው ብለዋል።
የኦሮሞ ብ/ሰብ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፋጡማ የሱፍ ብልፅግና የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀው በዚህም የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በተግባር እየተረጋገጠ ነው ብለዋል።
በሰልፉ የተሳተፉ የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እኛ ሴቶች ለምርጫው ሰላም ባለቤቶች በመሆን በድምፃችን ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር ተግተን እንሰራለን ብለዋል።