04/06/2026
በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ አስተዳድ ከንቲባ ጽ/ቤት የ9ወር እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የቀጣይ ስራዎች አቅጣጫ ዙሪያ ከጠቅላላ ሰራተኛው ጋር ውይይት አካሄደ።
በመድረኩ የቆቦ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ንጉስ አብርሃ እንዳሉት በበጀት አመቱ እንዲፈፀሙ በእቅድ ከተያዙ ስራዎች በዘጠኝ ወራት የተሻለ ውጤቶች የተመዘገበ ቢሆንም መድረስ በሚገባን የስራ አፈፃፀም ያልደረስንባቸው ተግባራት እንዳሉ አስገንዝበዋል።
በቀሪ ወራትም ሁሉም የስራ ቡድን የተጀመሩ ስራዎች በማጠናቀቅ ወደ ስራ በመግባት በተለያያ መንገድ የሚጓተቱ ስራዎችን ካሉም በአጭር ጊዜ ወደ ወደስራ ተገብቶ ተጨባጭ የሆነ ወጤት እንዲያመጡ ኃላፊው በአፅንኦት ገልጸዋል።