Hossana City Administration Communication affairs Office Media

Hossana City Administration Communication affairs Office Media Giving constructive ideas about the city

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፤ ታዛቢዎች ያለምንም ገደብ በነጻነት መታዘባቸውን ገለጹ!!!የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ህብረት ለምርጫ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ ቀን 7 ሰዓት ድረስ ያለውን ...
01/06/2026

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፤ ታዛቢዎች ያለምንም ገደብ በነጻነት መታዘባቸውን ገለጹ!!!

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ህብረት ለምርጫ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ ቀን 7 ሰዓት ድረስ ያለውን የትዝብት ሂደት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ ካሰማራቸው አጠቃላይ 3 ሺህ 149 (2,258 ተቀማጭ እና 891 ተንቀሳቃሽ) ታዛቢዎች መካከል 99 በመቶ ያህሉ ያለምንም ገደብ ወደ ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች በመግባት ስራቸውን በነጻነት ማከናወናቸውን አስታውቋል።

ህብረቱ በ2 ሺህ 258 ጣቢያዎች ላይ ባደረገው የክትትል ግኝት መሰረት፤ በ97 በመቶዎቹ (2,183 ጣቢያዎች) ታዛቢዎች በደረሱበት ወቅት የምርጫ አስፈጻሚዎች በቦታው ተገኝተው የነበረ ሲሆን፣ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱም በ99 በመቶዎቹ ጣቢያዎች ከጠዋቱ 1 ሰዓት በፊት መጀመሩን (42 በመቶው ከማለዳው 12 ሰዓት በፊት፣ 57 በመቶው ደግሞ ከ12 እስከ 1 ሰዓት ባለው ጊዜ) አረጋግጧል። በአንጻሩ 1 በመቶ (32 ጣቢያዎች) የሚሆኑት ከጠዋቱ 1 ሰዓት በኋላ ሂደቱን የጀመሩ ሲሆን፣ በ3 ጣቢያዎች ላይ ግን መግለጫው እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የድምፅ አሰጣጥ ስራው አለመጀመሩን በማመልከት የምርጫውን ቀደምት ሂደት አጠቃላይ ገጽታ በስኬትና በተግዳሮት ሚዛን አስፍሯል።

FDREGovermentCommunication

01/06/2026
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ...
01/06/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል።

ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ 12:00 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እንደሚቀጥል ያሳውቃል።

ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።

ድምፅ የመስጠት ሂደቱ ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ይቀጥላል -የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድሆሳዕና፦ ግንቦት 24/2018(ሀድያ ቴሌቪዥን) የኢትዮጵያ ብሔራ...
01/06/2026

ድምፅ የመስጠት ሂደቱ ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ይቀጥላል -የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሆሳዕና፦ ግንቦት 24/2018(ሀድያ ቴሌቪዥን) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል።

ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ 12:00 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስ...
01/06/2026

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።
#የክልሉ ኮሙንኬሽን #

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አጠቃላይ ሂደት ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሌለ ገለጸ፡፡የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ7ኛው ጠቅላላ ...
01/06/2026

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አጠቃላይ ሂደት ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሌለ ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አጠቃላይ ሂደት ላይ ባደረገው ሰፊ ምልከታ፣ እስካሁን ባለው ሂደት ምንም ዓይነት ያልተገባ የሰብዓዊ መብት አያያዝ እንዳልተመለከተ አስታወቀ።

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ የተመራ የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በአርባ ምንጭ እና በጅማ ከተሞች የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን በአካል ተገኝቶ በመዘዋወር የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን በቅርበት ታዝቧል።

ዋና ኮሚሽነሩ በምልከታቸው ወቅት እንዳረጋገጡት፤ የምርጫ ጣቢያዎች ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ ተደርገው የተዘጋጁ ከመሆናቸውም በላይ፣ አጠቃላይ ሂደቱ ሙሉ በሙሉ የምርጫ መስፈርቶችን ያሟላ መሆኑን መታዘብ እንደቻሉ አረጋግጠዋል። ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊና ምንም ዓይነት መስተጓጉል ያልታየበት መሆኑንም ገልጸዋል።

ኢሰመኮ በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ በ175 የምርጫ ክልሎችና ከ2 ሺህ 700 በላይ በሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ታዛቢዎቹን በስፋት በማሰማራት የክትትል ሥራ እያከናወነ ይገኛል። ከዚህም በተጨማሪ፣ በምርጫ ሂደቱ ላይ ሊነሱ የሚችሉ ቅሬታዎችን በወቅቱ ለማስተናገድ የተዘረጋውን የቅሬታ መከታተያ ሥርዓት በመጠቀም ሂደቱን በንቃት እየተከታተለ መሆኑ ተብራርቷል።

ኮሚሽኑ በምርጫው ወቅት ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ከመታዘብ ባለፈ፣ በድህረ-ምርጫ የሚኖረውንም ሂደት በአግባቡ በመምራትና በመከታተል ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
#የክልሉ ኮሙንኬሽን #

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ...
01/06/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ 12:00 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እንደሚቀጥል ያሳውቃል።

ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።

የኢትዮጵያ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እና በተዓማኒነት እየተካሄደ ነው፡- ኡሁሩ ኬንያታ የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ እና የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ...
01/06/2026

የኢትዮጵያ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እና በተዓማኒነት እየተካሄደ ነው፡- ኡሁሩ ኬንያታ

የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ እና የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ መግለጫ ሰጥተዋል።

ኡሁሩ ኬንያታ እንደገለጹት፣ የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢዎች ከጠዋት ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን በመከታተል ላይ ሲሆኑ፣ አብዛኞቹ ጣቢያዎች በተያዘላቸው ሰዓት መከፈታቸውን እና የምርጫ ሂደቱም በተያዘለት ቅደም ተከተል እየተከናወነ መሆኑን አረጋግጠናል ብለዋል።

ታዛቢዎቹ ባደረጉት ምልከታ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነፃነት እና በሙሉ ፈቃዳቸው እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ መመልከታቸውን ገልጸው፣ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በተግባር እያሳዩ ነው ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

“በታዘብነው መሠረት ዜጎች ያለምንም ጫና የሚፈልጉትን ፓርቲ እየመረጡ ነው” ያሉት ኡሁሩ ኬንያታ፣ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ እና በተዓማኒነት የተሞላ ሂደት መሆኑን ገልጸዋል።

አክለውም በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች የተመደቡ የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢዎች የምርጫውን ሂደት በቀጣይነት እየተከታተሉ ሲሆን፣ በቀጣይ ቀናትም ዝርዝር ግምገማቸውን እንደሚያቀርቡ ጠቁመዋል።

በአጠቃላይ የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ቡድን እስካሁን ባለው ምልከታ፣ ምርጫው በሰላማዊ እና በምቹ ሁኔታ በመቀጠል ላይ እንደሚገኝ፣ የጸጥታ ሁኔታውም የተረጋጋ መሆኑን ገልጿል።
#የክልሉ ኮሙንኬሽን ቢሮ #

እጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ ሮማን ሰዶሮ በሌሞ 02 ምርጫ ክልል ድምፅ ሰጥተዋል።በሀዲያ ዞን የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ ሮማን ሰዶሮ በሌሞ 02 ምርጫ ክልል በተመዘገቡበት የምርጫ ጣቢያ ...
01/06/2026

እጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ ሮማን ሰዶሮ በሌሞ 02 ምርጫ ክልል ድምፅ ሰጥተዋል።

በሀዲያ ዞን የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ ሮማን ሰዶሮ በሌሞ 02 ምርጫ ክልል በተመዘገቡበት የምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

በዚሁ የምርጫ ክልል የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ በሰላማዊ ድባብ እየተከናወነ ይገኛል።

Htv
ለትክክለኛ መረጃ ከታች ሊኩን በመጫን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ያገኙናል ።
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063559671902&mibextid=ZbWKwL
Telegram
https://t.me/hossanacommunicatin
Twitter
https://x.com/gov_city86471?t=_HpdGUXInnC_gtHHDh_yRw&s=09

Tiktok
http://tiktok.com/.city.govt
YouTube ሀ
https://youtube.com/?si=ps9RX4IRgOpxjF_D
Instagram
https://www.instagram.com/hossanacity?igsh=aTBiY2JwdTlzN3Vl
WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/GoZK5IRGk1B5gxAqHqnFeU11

Address

Hossana

Telephone

+251465550930

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hossana City Administration Communication affairs Office Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share