ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት

ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት 📍የግብር ስወራና ማጭበርበር በጋራ እንከላከል
📍ግብርን መክፈል የዜግነት ግዴታ ነው
📍ግብር ከፋይነቴ ያኮራኛል
📍ታማኝ ግብር ከፋይ የሃገር አለኝታ
📍ግብር ለሀገር ክብር revenue authority

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የ10 ወራት የገቢ አፈጻጸም ከጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ጋር ገመገመ​ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 በ...
21/05/2026

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የ10 ወራት የገቢ አፈጻጸም ከጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ጋር ገመገመ

​ሆሳዕና፤ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም
​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ በዛሬው ዕለት አካሂዷል።

በግምገማ መድረኩ ላይ የጽ/ቤቱ ማናጅመንት አባላት፣ የቡድን መሪዎች እና መላው ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን፣ መድረኩን የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አውላቸው ዮሐንስ መርተውታል።

​በመድረኩ መጀመሪያ ላይ የጽ/ቤቱ የልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪ አቶ አለማየሁ ኤልያስ የ10 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል።

በሪፖርቱም የከተማዋን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት በመፍጠር ረገድ የታዩ ስኬቶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በሰፊው ተገምግመዋል።

​📊 የገቢ አፈጻጸም
​በአጠቃላይ በ10 ወራት ውስጥ 1 ቢሊዮን 9 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል። ይህም ከባለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ዕድገት የታየበት መሆኑ ተመላክቷል።
​የተሰበሰበው ገቢ ዝርዝር ስብጥር፦
• ​መደበኛ ገቢ: ከ1.35ቢሊዮን ብር በላይ
• ​ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ: ከ541 ሚሊዮን ብር በላይ
• ​ከውዝፍ ዕዳ: ከ22.5 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል።

​⚖️ ሕግን ከማስከበርና ታክስ ኦዲት አኳያ የተከናወኑ ሥራዎች
​የሕግ ማስከበር ሥራውን አጠናክሮ ከመቀጠል አኳያ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ሪፖርቱ ያመላከተ ሲሆን ዋና ዋናዎቹ፦
1. ​የደረሰኝ ቁጥጥር: ያለ ደረሰኝ ግብይት ሲፈጽሙ እጅ ከፍንጅ በተያዙ 118 ግብር ከፋዮች ላይ ሕጋዊ እርምጃ በመውሰድ 11 ሚሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል።
2. ​የታክስ ኦዲት ምርመራ:133 ፋይሎችን በታክስ ኦዲት በመመርመር 55.3 ሚሊዮን ብር ተጨማሪ ግኝት ማስመዝገብ ተችሏል።

​⚠️ ያጋጠሙ ዋና ዋና ተግዳሮቶች
​በግምገማው ወቅት የታክስ ማጭበርበር፣ ያለ ንግድ ፈቃድ መነገድ እና የሊዝ መሬት አቅርቦት ማነስ እንደ ዋና ማነቆዎች የተነሱ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ በቀጣይ የሚከተሉት የትኩረት አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፦
• ​📌 ያለ ደረሰኝ ግብይት በሚፈጽሙ አካላት ላይ የጀመረውን ጠንካራ ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ መቀጠል።
• ​📌 ውዝፍ ዕዳ ባለባቸው ላይ የንብረትና የባንክ ዕገዳ ሥራዎችን በቁርጠኝነት መተግበር።
• ​📌 የሊዝ መሬት አቅርቦትን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በማመቻቸት ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢን ይበልጥ ማሳደግ።

​🎯 በመጨረሻም የ/ቤቱ ማናጅመንትና ቡድን መሪዎች እንዲሁም ባለሙያዎች ባደረጉት ርብርብ የተመዘገበው ውጤት የሚበረታታ መሆኑ ተገልጿል።

"የከተማችንን ወጪ በራስ ገቢ ለመሸፈን" የሚለውን ታላቅ መርህ ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ ባለሙያዎችና የከተማዋ ግብር ከፋዮች በቅንጅትና በታማኝነት እንዲሠሩ ጥሪ ቀርቧል።
​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት

21/05/2026

“የክልሉን ብሎም የሀገርን የመልማት ጥያቄ ለመመለስ ገቢን በተገቢው ልክ ለመሰብሰብ እንሰራለን”
- ወ/ሮ ቀመሪያ ረሻድ (የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ)

ግንቦት 13/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ባለፉት ዓመታት በተቋሙ ባከናወነው የሪፎርም እና አገልግሎት አሰጣጥን የማዘመን ስራ ገቢ የመሰብሰብ አቅሙ እያደገ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ቀመሪያ ረሻድ ገለጹ።

ቢሮ ኃላፊዋ ቢሮው እንደአዲስ ስራ ከጀመረበት 2016 ዓ.ም ጀምሮ ገቢን የመሰብብ አቅሙ እያደገ መምጣቱን ገልጸው በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያ ታቅዶ የነበረውን 23.7 ቢሊየን ብር የመሰብሰብ እቅድ በመከለስ እና 27 ቢሊየን ለመሰብሰብ በማቀድ በ10 ወራት ውስጥ 21 ቢሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል።

አፈጻጸሙ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም የ8 ቢሊየን ብር ብልጫ አለው ብለዋል።

ለክልሉ የገቢ እድገት የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር፣ በየደረጃው ያለ አመራር፣ የሴክተሩ አመራር እና ሰራተኛ እንዲሁም የግብር ከፋዩ ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

የተገኘው ውጤጥ ጥሩ ቢሆንም የክልሉን የልማት ጥያቄ ብሎም የሀገርን የመልማት እና የመበልጸግ ፍላጎት ለማሳካት ከዚህም በላይ ገቢን በተገቢው ልክ ለመሰብሰብ እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

ግብር ከፋዩ ወደተቋሙ መምጣት ሳያስፈልገው ባለበት ሆኖ የሚስተናገድበት የታክስ የመረጃ ቴክኖሎጂን የማሳደግ ስራ እንዲሁም የሰው ኃይሉን ክሕሎት የማሳደግ ስራ መከናወኑን የገለጹት ወ/ሮ ቀመሪያ በቀጣይም አገልግሎት አሰጣጥን የበለጠ ቀልጣፋ እና ተደራሽ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

ኃላፊዋ አያይዘውም የገቢ መሰረትን ለማስፋት ብሎም የቢሮውን ገቢ የመሰበሰብ አቅምን በቀጣይነት ለማሳደግ ቢሮው ከክልሉ የፋይናንስ ቢሮ፣ በክልሉ ካሉ ዩንቨርሲቲዎች እና ከዘርፉ ባለሙያዎች ጋር በጋራ የክልሉን የገቢ አቅም ለማጥናት ቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ሲሆን በጥናት ላይ በመመርኮዝ የግብር ከፋዮችን ደረጃ የማሻሻል ስራ ይሰራል ብለዋል።

በተጨማሪም ቢሮው ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በጋራ እያከናወናቸው ያሉትን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቀው የሚደረገው ድጋፍም ይበልጥ እንደሚጠናከር ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ቢሮ ኃላፊዋ ለግብር ከፋዮች ባስተላለፉት መልእክትም ታክስን በታማኝነት እና በወቅቱ የመክፈል እንዲሁም በግብይት ወቅት ደረሰኝ የመስጠት እና የመቀበል ባህልን በማሳደግ የክልሉን ገቢ በተገቢው ልክ ለመሰብሰብ የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል።

ፎቶ :- የትናየት እንዳያፍሩ

፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

19/05/2026
በቀሪዎቹ ሁለት ወራት የገቢ ዕቅዱን 100% ለማሳካት የሚያስችል የጋራ መድረክ ተካሄደ​ሆሳዕና :- ግንቦት 10/2018 ​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በቀሪዎቹ ሁለት ወራት የዕ...
18/05/2026

በቀሪዎቹ ሁለት ወራት የገቢ ዕቅዱን 100% ለማሳካት የሚያስችል የጋራ መድረክ ተካሄደ

​ሆሳዕና :- ግንቦት 10/2018
​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በቀሪዎቹ ሁለት ወራት የዕቅዱን መቶ ፐርሰንት ለማድረስ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለጸ።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ የሚመራው የድጋፍ ቡድን በሆሳዕና ከተማ በመገኘት፣ ከዞኑ እና ከከተማው ማናጅመንት አካላት ጋር የጋራ የምክክርና ውይይት አካሂዷል።

​የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በቀሪዎቹ ወራት ውስጥ ያሉትን አቅሞች በሙሉ በአግባቡ መጠቀም ይገባል።

ለዚህም ጠንካራ የታክስ ሠራዊት በመፍጠር፣ መረጃን መሠረት ያደረገ የሕግ ማስከበር እና የገቢ አሰባሰብ ሥራዎችን በማጠናከር የተያዘውን ዕቅድ 100% ማሳካት እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

​በመድረኩ ላይ በቀሪ ወራት ሊከናወኑ የሚገባቸው ዝርዝር ተግባራት የቀረቡ ሲሆን፣ ለእያንዳንዱ ተግባር ስኬታማነት የመረጃ ማደራጀት ሥራ ቀዳሚ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

በተጨማሪም የፊዚካል ሥራዎች ላይ በልዩ ትኩረት በመረባረብ፣ ለፋይናንሻል ሥራዎች ግብዓት የሚሆን ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ በውይይቱ ላይ ተነስቷል።

​በቀሪዎቹ ቀናት ውስጥ ልዩ ትኩረት የሚሹና የተለዩ ዋና ዋና ተግባራት፦
• ​ከመደበኛ ገቢ አንጻር፦ የውዝፍ ዕዳዎች አሰባሰብ፣ የታክስ ኦዲት፣ የዴስክ ኦዲት፣ የቅድመ ክፍያ ቁጥጥር እና የደረሰኝ ቁጥጥር እና ሌሎች ሥራዎች፤

• ​ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አንጻር፦ የውዝፍ ዕዳዎች፣ የሊዝ፣ የኢንቨስትመንት፣ የሕንጻ ግብር፣ የታፔላ (የማስታወቂያ) እንዲሁም የገበያ ኪራይ ገቢዎች እና ሌሎች የገቢ ርዕሶች ላይ በልዩ ትኩረት መሥራት።

​በመጨረሻም፣ የቅንጅት ሥራ ለገቢ አሰባሰብ ስኬታማነት ወሳኝ መሆኑ በመድረኩ የተመላከተ ሲሆን፤ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራና በተቀናጀ መልኩ በመንቀሳቀስ በቀሪዎቹ ወራት ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የሚያስችል ግልጽ የአሠራር አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ በስኬት ተጠናቋል።

#​የሆሳዕና #ከተማ #አስተዳደር #ገቢዎች #ጽ/ቤት

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች እና የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤቶች የብልጽግና ህብረት የ3ኛ ሩብ ዓመት ኮንፈረንስ አካሄዱ​(ግንቦት 3 / 2018 ዓ.ም - ሆሳዕና)​የሆሳዕና ከተማ አስተ...
11/05/2026

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች እና የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤቶች የብልጽግና ህብረት የ3ኛ ሩብ ዓመት ኮንፈረንስ አካሄዱ
​(ግንቦት 3 / 2018 ዓ.ም - ሆሳዕና)
​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት እና የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የብልጽግና ህብረት የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ ዛሬ በደመቀ ሁኔታ አካሂዷል።

​የኮንፈረንሱ አበይት ነጥቦች፦
• ​ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ስራዎች፦ ኮንፈረንሱ ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ታሪካዊ ስራዎች ላይ ምክክር እየተደረገ ባለበት ወቅት መካሄዱ ልዩ ትርጉም እንደሚሰጠው ተገልጿል።

• ​የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ፦ በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ላይ ምርጫ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑ ተጠቅሶ፤ መጪው ምርጫ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ፓርቲው ግልጽ ግቦችን አስቀምጦ ወደ ዝግጅት ምዕራፍ መሸጋገሩ ተብራርቷል።

• ​የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማ፦ በህብረቱ ያለፉት 9 ወራት የሥራ ሪፖርትና ሌሎች ተያያዥ ሰነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተካሄዶባቸዋል።

​አባላቱ በእነዚህ አበይት ጉዳዮች ላይ በዝርዝር ከመከሩ በኋላ፣ በቀጣይ ተግባራት ላይ የጋራ አቋም በመያዝ እና የአቋም መግለጫ በማውጣት ኮንፈረንሱ በስኬት ተጠናቋል።

​"ጠንካራ ህብረት ለላቀ ውጤት!"

"የከተማችንን ወጪ በራስ ገቢ ለመሸፈን እንተጋለን!"​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የ10 ወራት የገቢ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ​ሆሳዕና፣ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች...
08/05/2026

"የከተማችንን ወጪ በራስ ገቢ ለመሸፈን እንተጋለን!"
​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የ10 ወራት የገቢ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ

​ሆሳዕና፣ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም
​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽሕፈት ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ አካሄደ።

በመድረኩም የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን መድረኩን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ መርተውታል ።

የከተማዋን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት በመፍጠር ረገድ የታዩ ስኬቶችና ተግዳሮቶች ተገምግመዋል።

​በበጀት ዓመቱ 10 ወራት ውስጥ ተቋሙ በአጠቃላይ 1 ቢሊዮን 871 ሚሊዮን 863 ሺህ 943 ብር ከ02 ሳንቲም ገቢ መሰብሰብ ችሏል። ይህም ከባለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ዕድገት የታየበት መሆኑ ተመላክቷል።
​የገቢ ምንጮች ዝርዝር፡-
• ​መደበኛ ገቢ፡ ከ1.33 ቢሊዮን ብር በላይ
• ​ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ፡ 541 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል።
• ​ከውዝፍ ዕዳ፡ ከ22.5 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ የተሰበሰበ ሲሆን።
​የታክስ አስተዳደሩን ዘመናዊ ለማድረግ በተቀናጀ የታክስ አስተዳደር ሥርዓት (SIGTAS) ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸው ተገልጿል።
ሕግን ከማስከበር አኳያ፡-
• ​ያለ ደረሰኝ ግብይት ሲፈጽሙ እጅ ከፍንጅ በተያዙ 118 ግብር ከፋዮች ላይ እርምጃ በመውሰድ 11 ሚሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል።
• ​በታክስ ኦዲት ምርመራ 133 ፋይሎችን የታክስ ኦዲት በማድረግ 55.3 ሚሊዮን ብር ግኝት ተመዝግቧል።

​በግምገማው ወቅት የታክስ ማጭበርበር፣ ያለ ንግድ ፈቃድ መነገድና የሊዝ መሬት አቅርቦት ማነስ እንደ ዋና ተግዳሮት የተነሱ ሲሆን፣ በቀጣይ የሚከተሉት የትኩረት አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡-
• ​ያለ ደረሰኝ ግብይት በሚፈጽሙ ላይ ጠንካራ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ።
• ​ውዝፍ ዕዳ ባለባቸው ላይ የንብረትና የባንክ ዕገዳ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል።
• ​የሊዝ መሬት አቅርቦትን በማመቻቸት ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢን ማሳደግ።

​መድረኩን የመሩት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ እንደገለጹት፤ የገቢ ዕቅዱን 100% ለማድረስ አመራሩ በልዩ ትኩረት ሊመራ ይገባል በማለት የህግ ማስከበር ስራና የአስተምሮ ስራዎችን ጎን ለጎን በመስኬድ የግብር ከፍዮችን የህግ ተገዥነት ደረጃ ማሳደግ ይገባል በማለት አሳስበዋል ።

በመጨረሻም የከተማው ማናጅመንትና የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ባደረጉት የቅርብ ክትትል የተመዘገበው ውጤት ጥሩ መሆኑ ተገልጾ፣

"የከተማውን ወጪ በራስ ገቢ ለመሸፈን" በሚለው መርህ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።

​የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በሆሳዕና ከተማ የገቢ አሰባሰብ ስራዎች ላይ የግምገማና ድጋፍ መድረክ አካሄደ ሚያዝያ 29/2018 (ሆሳዕና)​የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ...
07/05/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በሆሳዕና ከተማ የገቢ አሰባሰብ ስራዎች ላይ የግምገማና ድጋፍ መድረክ አካሄደ
ሚያዝያ 29/2018 (ሆሳዕና)
​የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በምክትል ቢሮ ኃላፊው በአቶ ተስፋዬ አሰፋ የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በመገኘት የፋይናንሻል እና የፊዚካል ስራዎችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ገመገመ።

​በመድረኩ ላይ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ እንደገለጹት፤ ለገቢ ዕድገት ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት ሚና የማይተካ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተለይም የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አሰባሰብን ውጤታማ ለማድረግ፦
• ​ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው፤
• ​መረጃን መሠረት ያደረገ የአሰራር ስርዓት መከተል እንደሚገባ፤
• ​በሕግ መሰብሰብ ያለበትን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ ላይ ትኩረት እንዲደረግ አሳስበዋል።
​አሁን ላይ ያለው የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፣ ይህንን ለማሻሻል ከፍተኛ ርብርብ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ መሆኑን አስገንዝበዋል።

​ከግምገማ መድረኩ የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
• ​ለትራንስፖርት ጽ/ቤት፦ በአደራ የሚሰበሰቡ ገቢዎች በወቅቱ ወደ ፋይናንስ ፈሰስ መደረግ እንዳለባቸውና ከትራፊክ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን መደገፍ እንደሚገባ ተመልክቷል።
• ​ለንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት፦ ከሕገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ጀምሮ ያሉ ተግባራት ገቢን በሚያሳድግ መልኩ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተገልጿል።
• ​ለቅንጅታዊ አሰራር፦ በተለያዩ የገቢ ርዕሶች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላትና የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢን ለማሳደግ መረጃን መሠረት ያደረገ ጠንካራ የገቢ አሰባሰብ ላይ የጋራ ርብርብ እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀምጧል።

​በመጨረሻም የገቢ አቅም እንዲያድግና የታቀደው ግብ እንዲሳካ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በቁርጠኝነት እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።

(የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት)

Address

Hossana

Telephone

+251465554581

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት:

Share