በሀዲያ ዞን የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Hossana
  • በሀዲያ ዞን የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

በሀዲያ ዞን የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና  ፓርቲ ጽ/ቤት አንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርት /ቅ/ ጽ/ቤት

የአንሌሞ ወረዳ ም/አስተዳደርና የት/መ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደገፈ ሉብሶ ''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በከቤቶቾ ክላ...
23/06/2026

የአንሌሞ ወረዳ ም/አስተዳደርና የት/መ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደገፈ ሉብሶ ''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በከቤቶቾ ክላስተር አስጀመሩ

(ፎንቆ ፣ሰኔ 16/2018) የአንሌሞ ወረዳ ም/አስተዳደርና የት/መ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደገፈ ሉብሶ ለአንድ ተፈናቃይ ቤት አድስ ግንባታ አስጀምረዋል።

በወረዳው ዛሬ በሚጀመረው የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በ15 የስምሪት መስኮች ተግባራዊ እንደሚደረግም ተመላክቷል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ በቀበሌያት ላይ የፈይዳ ዲጅታል መታወቂያ ምዝገባ  እየተካሄደ ሲሆን ሂደቱም በተሳካ ሁኔታ እንደቀጠለ ነው።ፎንቆ:- ሰኔ 16/2018 ዓ...
23/06/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ በቀበሌያት ላይ የፈይዳ ዲጅታል መታወቂያ ምዝገባ እየተካሄደ ሲሆን ሂደቱም በተሳካ ሁኔታ እንደቀጠለ ነው።

ፎንቆ:- ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ ት/ቤቶች ላይ የፈይዳ ዲጅታል መታወቂያ ምዝገባ  እየተካሄደ ሲሆን ሂደቱም በተሳካ ሁኔታ እንደቀጠለ ነው።ፎንቆ:- ሰኔ 15/2018 ዓ....
22/06/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ ት/ቤቶች ላይ የፈይዳ ዲጅታል መታወቂያ ምዝገባ እየተካሄደ ሲሆን ሂደቱም በተሳካ ሁኔታ እንደቀጠለ ነው።

ፎንቆ:- ሰኔ 15/2018 ዓ.ም የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

20/06/2026
የመሬት ሊዝ ጨረታ ማስታወቂያፎንቆ:-ሰኔ12/2018 ዓ.ም(የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ )በአንሌሞ ወረዳ የአጫሞ ከተማ ታዳጊ  ማዘጋጃ ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ሰለመያዝ በተደነገገው አዋጅ...
20/06/2026

የመሬት ሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ

ፎንቆ:-ሰኔ12/2018 ዓ.ም(የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ )

በአንሌሞ ወረዳ የአጫሞ ከተማ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ሰለመያዝ በተደነገገው አዋጅ ቁጥር 𝟟𝟚𝟙/𝟚𝟘𝟘𝟜 አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 በፍደል ተራ ከ'ሀ' እስከ 'ሠ' መሠረት ለመኖሪያ አገልግሎቶች የሚውሉ ቦታዎችን በመደበኛ የጨረታ አይነት ማስተላለፍ ይፈልጋል።

በመሆኑም መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ግለሰብ/ድርጅት ጨረታው ከ12/10/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአሥር(10) ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚቆይ መሆኑን እየገለጽን የቦታውን ዝርዝር መረጃና የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 500 ብር(አምስት መቶ ብር) በመክፈል በአጫሞ ከተማ ማ/ቤት ለጨረታ ኮሚቴ በማቅረብ በሥራ ሰዓት መግዛት የሚትችሉ መሆኑንእናሳውቃለን።

የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ከ15/10/2018 ዓ.ም. እስከ 26/10/2018 ዓ.ም.ከቀኑ 11:00 ሰዓት ብቻ ይሆናል።

የጨረታው ሳጥን የሚዘገው በ26/102018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ይሆናል።

የጨረታው ሰጥን የሚከፈተው በ27/10/2018 ዓ.ም. ከጧቱ 3:00 ሰዓት ላይ በአጫሞ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ግቢ ውስጥ ሁሉም ተጨራቾችና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል።

ማዘጋጃ ቤቱ ጨረታውን ሙሉበሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

መልካም ዕድል !!

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወጣቶች  በመራጭነትም ሆነ በተመራጭነት በንቃት እንዲሳተፉና የምርጫው ሂደቶች ሰላማዊ ሆነው እንዲጠናቀቁ የተደረጉ ጥረቶች ስኬታማ እንደነበሩ ተገለፀ። በሀዲያ ዞን በአን...
19/06/2026

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወጣቶች በመራጭነትም ሆነ በተመራጭነት በንቃት እንዲሳተፉና የምርጫው ሂደቶች ሰላማዊ ሆነው እንዲጠናቀቁ የተደረጉ ጥረቶች ስኬታማ እንደነበሩ ተገለፀ።

በሀዲያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ በከቤቾ ክላስተር ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አባላት የ4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት መድረክ አካሄደ።

በሀዲያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ በከቤቾ ክላስተር ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አባላት የ4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት መድረክ አካሂዷል።

የግምገማ መድረኩን የወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢያሱ ኤረዳዶ መርተዋል።

በመድረኩም ለውይይት መነሻ የሚሆን በወጣቶች ክንፍ አማካኝነት የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት የእስካሁን አፈጻጸም ሪፖርት ከክንፍ ኃላፊ በኩል ቀርቦ በጥልቀት ውይይትና ግምገማ ተደረጓል።

የተለያዩ ወጣቶች አደረጃጀቶችን በማጠናከር ከመንግሥት ኢንሼቲቭ አንዱ አካል የሆነውን ብሔራዊ የፋይደ መታወቂያ ምዝገባ ሂደትን ወጣቶች አጠናክሮ በየመዋቅሩ እንዲያስቀጥሉ በተለያዩ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ተግባቦት በመፍጠር ዘርፈብዙ ጠቃሜታ ያለው የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ማድረጋቸውን ከቀረበ ሪፖርት ማረጋገጥ ተችሏል።

በተለይም በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ዙሪያ ማለትም በምዝገባ ሂደት፣ ቤት ለቤት ቅስቀሳ ሥራዎች ፣የምርጫ ምልከትና እጩዎችን ከማስተዋወቅ አኳያ እንዲሁም በምርጫ ዕለት የነበረው ወጣቶች ሚና በጣም ከፍተኛ እንደሆነ ሪፖርቱ ላይ እንደ ጠንካራ ጎን ማየት ተችሏል።

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሂደት ግብ ስኬታማና በፓርቲው አሸናፊነት ውጤታማ ሆኖ በሠላም እንዲጠናቀቅ ወጣቶች ንቁ ተሳትፎና የአስተሳሰብ ቁርጠኝነት ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል።

በምርጫ ሂደት ያሳየውን የአስተሳሰብ አንድነትና ቅንጅታዊ አሠራርን በመከተል ወጣቶች በልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎች እንዲሁም በልዩ ትኩረት በሚመሩ ወቅታዊ ተግባራት የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መረባረብ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

በብሔራዊ ፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ፣ በኢትዮ -ኮደርስ ስልጠና፣ገቢ አሰባሰብ፣በሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ በትምህርት ሥራዎች፣ በግብርና ሥራዎች፣ በጤና፣በሠላምና ፀጥታ ሥራዎች እንዲሁም በሌሎችም ወቅታዊ ተግባራት ላይ ወጣቶች በግንባር ቀደምትነት የበኩላቸውን ድርሻ በቁርጠኝነት እንዲወጡ አቅጣጫ ተቀምጧል።

የመድረክ በኩል የቀረበውን የአፈፃፀም ግምገማ ሪፖርት መነሻ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የተለያዩ ሀሳብ አስተያየቶች ያነሱት ሲሆን መንግሥት ለሥራ ፈላጊ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለማመቻቸት የያዘ አቅጣጫ ምን አለ ብሎ ላነሱት ጥያቄዎች ከመድረክ በኩል ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶበት ተግባቦት ተፈጥሯል።

በማጠቃለያ በተለያዩ ትኩረት መስኮች ላይ የወጣቶች በጎ ፈቃድ ተግባራት ከዚህ በፊት ከነበረው በላይ ተጠናክሮ መፈጸም እንደለበት ተገልጾ ለተግባር ውጤታማነት ጠንካራ የወጣቶች አደረጃጀት መቋቋምና የሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ማጠናከር ወሳኝ እንደሆነ ተብራርቷል።

18/06/2026
15/06/2026
"በምርጫው ሂደት ሰላማዊ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ ሁሉ ምስጋናዬን አቀርባለው" ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ
14/06/2026

"በምርጫው ሂደት ሰላማዊ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ ሁሉ ምስጋናዬን አቀርባለው"

ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

“የሕዝብ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ  ሥራዎች ላይ በትኩረት መሥራት ይገባል” - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ሆሳዕና፣ሰኔ 7/2018ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ...
14/06/2026

“የሕዝብ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ በትኩረት መሥራት ይገባል” - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

ሆሳዕና፣ሰኔ 7/2018ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች “ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግሥት” በሚል መሪ ቃል የ7ተኛውን ጠቅላላ የምርጫ ሥራዎች አፈጻጸም እና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ዕቅድ ላይ ሲያካሂዱት የነበረው ሰፊ ውይይት በተቀመጡ ቁልፍ አቅጣጫዎች ተጠናቋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )እንደገለጹት የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ክልሉ ሲመሰረት የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት በመደረጉ ክልሉ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ እንዲሆን ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።

የጋራ ትርክት ለመገንባት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የነበረው የቅድመ ዝግጅት ስራ ውጤታማ እንደነበር ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውሰዋል።

የልማት እና የምርጫ ስራ ተመጋጋቢ እንዲሆን መስራት በመቻሉ የህዝቡን ተሳትፎ ማረጋገጥ ስለመቻሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በክልሉ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ለቅድመ ዝግጅት ስራ አጋዥ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው ጠቅሰዋል።

በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት መሰራቱን ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

በክልሉ በፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ፣በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና፣በገቢ፣በስራ እድል ፈጠራ፣በገበያ ማረጋጋት፣ በከተማ እና በገጠር ኮሪደር ልማት ስራ ላይ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር ተገቢ ስለመሆኑም አሳስበዋል።

በወቅታዊ የግብርና ልማት ስራ ላይ የጋራ ጥረት ማድረግ ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የግሪን ኢኔሼቲቭ እና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ትኩረት የሚሹ ስለመሆኑም አመላክተዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር )እንደገለጹት ህዝቡ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ የነበረው አበርክቶ ከፍተኛ እንደነበር ተናግረዋል።

በምርጫው ሂደት ላይ የነበረው የሕዝብና ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበርም ኃላፊው አስረድተዋል።

አብዛኛው አመራርና አባል በተለያዩ የግል፣ የቤተሰብ፣ የጤናና የማኅበራዊ ሕይወት ፈተናዎች ውስጥ ሳይበገሩ፣ ከፍተኛ ቁርጠኝነት የታየበት ተሳትፎ በማሳየት ለምርጫው ስኬታማነት በግንባር ቀደምትነት መሳተፋቸውን ገልጸው እውቅና ሰጥተዋል።

በየጊዜው በሚሰጡ አገልግሎቶች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ያለው እምነት እንዳይሸረሸር አጠናክሮ ማስቀጠልና የተጀመሩ የልማትና የሰላም ሥራዎችን አቅጣጫ ይዞ መጓዝ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በቀጣይ የአደረጃጀት ሥራዎችን ለማጠናከር የአመቱን ተግባራት በአግባቡ መገምገም፣ በምርጫው የታዩ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎችን መፍታት እና እያንዳንዱ ሰው በየሚናው ልክ ደረጃና ፍረጃ የሚሰጥበት አሠራር ይዘረጋል።

በምርጫው ሂደት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ለመራጩ ህዝብ፣ለአባላት፣ለወጣቶችና ሴቶች፣ለፀጥታ ተቋማትና አካላት፣ለተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለመገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ለሕዝብ ወኪሎች፣ ታዛቢዎችና ለመላው የክልሉ ሕዝብ ምስጋና አቅርበው።

Address

ፎንቆ ከተማ
Hossana

Telephone

+462630091

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀዲያ ዞን የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share