Hola Media ሆላ ሚዲያ

Hola Media ሆላ ሚዲያ ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና! Hadiya Mass Media is the of voice of voiceless.

ሕግ በያዘዉ ጉዳይ ሕዝብ አይዳኝም! የክስ ሂደትንም ሆነ ፍርድን ያለፍ/ቤት ትዕዛዝ መግለጽ አይቻልም! (ጨርሰዉ ሳያነሱ አስተያየት አይስጡ!)ከወራት በፊት ወ/ሮ በረከት ወርቁ (ገበሬዋ) በሕ...
08/05/2026

ሕግ በያዘዉ ጉዳይ ሕዝብ አይዳኝም! የክስ ሂደትንም ሆነ ፍርድን ያለፍ/ቤት ትዕዛዝ መግለጽ አይቻልም!

(ጨርሰዉ ሳያነሱ አስተያየት አይስጡ!)
ከወራት በፊት ወ/ሮ በረከት ወርቁ (ገበሬዋ) በሕገወጥ የሰዎች ዝዉዉር፤ ሐሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት፤ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ተቋምን እንዲሁም የአገር መከላከያ ሠራዊትን መታወቂያ አዘጋጅታ በመገልገልና ሌሎችም ወንጀሎች በቁጥጥር ስር ዉላ በእስር ቆይታ በዋስትና መለቀቋ ይታወቃል። በዚያም ዋስትና ተፈቅዶ ከዉጭ ሆና እንድትከታተል በመደረጉ እንኳን ለቤትሽ አበቃሽ ብለን ብላችሁም ነበር።

በሂደት ጉዳዩ ከሌሎች ጋር በግብረ አበርነት የተፈጸሙ ከባባድና አገርን የሚጎዱ ወንጀሎች በመሆናቸዉ ክስ ቀርቦባት ከሰሞኑን ፍ/ቤት ስትጠራ ይህኑ በተመለከተ ትላንት ህዝብ ይስማልኝ ስትል መልክት አስተላልፋለች።

እንዲህ ባሉ ጉዳዮች ጥንቃቄ እያደረገች አይመስልም። ክስ አቅራቢዉን አካል ወይም መንግስትን መወንጀል ተገቢ አይደለም። ለምን በዋስ ተለቀኩም ይመስላል። በመንግስት በፀጥታና በፍትህ ተቋማት ዜጎች እምነት እንዳይኖራቸዉ ከሚያደርግ ንግግር መቆጠብ ተገቢ ይሆናል። ሕግ በያዘዉ ጉዳይ ሕዝብ አይዳኝም። ይሄ በራሱ ወንጀል ነዉ። ፀልዩልኝ ማለት አንድ ነገር ነዉ። ከወንጀሌ ጎን ቁሙ ማለት ግን ተገቢ አይደለም። ሕግ ትክክል የማይሆነዉ በግል ተጠያቂ ሲኮን አደለም።

ማንም ሰዉ በዋስ የሚወጣዉ ማስረጃ እንዲያጠፋ፤ የፍትህ ሥርዓቱን እንዲያቀል ሳይሆን ጉዳዩን ጥፋተኛ መሆኑ ሳይረጋገጥ በእስር ላይ ከሚቆይ ዉጭ ሆኖ እንዲከታተል ለማድረግ ነዉ።

በሚዲያ ላይ የክስ ሂደትንም ሆነ ፍርድን ያለ ፍ/ቤት ትዕዛዝ መግለጽ አይቻልም። በግልጽ ሂደቱንም ሆነ ፍርዱን በሚዲያ እንዲተላለፍ ትዕዛዝ ካልሰጠ በቀር ፖሊስም ሆነ አንዱ ወገን አይችልም። ፍርድ ተሰጥቶ ቢሆን እንኳ ፍ/ቤት በሚዲያ ይተላለፍ ብሎ ካላዘዘ አይቻልም! በፖሊስ በኩል ሌላም ጊዜያት በተግባር የሚታየዉ ግን ለየቅል ነዉ። ለተከሳሹም ይሆናል። (የሕጉን ድንጋጌ ከታች ይመልከቱ)

ይህ እንዳለ ሆኖ በዋስትና ከተወጣ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ጉዳዩን እንደ ማንኛዉም ዜጋ በመከታተል ፈንታ "በእስር በነበረችበት ጊዜ በጤናዋ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል። ከደም መርጋት ጋር የተያያዘና ለህይወቷም አስጊ ነው ዉጭ ሄዳ መታከም አለባት ተብሏል።" ሲሉ

ባንዳንድ ሚዲያዎች ፎቶ እንዲሰራጭና እንዲነገርላት በማድረግ በዚህም በዋስ ዉጭ ሆና እንድትከታተል ከተደረገዉ ወንጀል ተጠያቂነት ለማስቀረት የተደረገ መሆኑን የሚመለከታቸዉ በመረዳታቸዉ ሕክምና በሚል ከአገር የማምለጥ ፕሮግራሙ ሳይሆን ቀረ! ጤናዋም በዛዉ ተመለሰላት። እኛም ይህኑ ጠቅሰን ተናግረን ነበር።

ሌላዉ ከመጸለይ ጉዳዩን የሕዝብ አንደምታ ለመፍጠር መሞከርም ተገቢ አይደለም። ሐሰተኛ የአገር ደህንነትና የአገር መከላከያ ሠራዊት መታወቂያ አበጅቶ መገልገል በራሱ ለዚሁ ማሕበረሰብ ይሄንኑ ሕዝብ ለማስፈራራት፤ ከዚሁ ሕዝብ አላግባብ ተጠቃሚ ለመሆን የተሞከረ ከመሆን በዘለለ ምን ዓላማ ይኖረዋል? ታዲያ መልሶ ይሄን ሕዝብ ድረሱ እወቁልኝ ማለት ምን ማለት ነዉ?

መደገፍ በጌታ እንጂ በጌታ ነኝ እያሉ ባለስልጣናት ስር በመሸጎጥ በግለሰቦች ተቀባይነት ለማግኘት በጌታ ነኝ እየተባለ ኢሬቻና ሌላ ኃይማኖት የባዕድ አምልኮ በዓል ዋነኛ ካዳሚ ከመሆንና ስርዓት ከመፈጸም ኢየሱስ ላይ መደገፍ ነበር። እዚ ዉስጥም መግባት አይኖርም ነበር! ኢየሱስ የነፍስ ብቻ ሳይሆን የስጋም ነዉ! እንዲ ካለ ስጋትና ጥፋት ታዳጊ ነዉ። አሁንም ወደ እርሱ እንጂ ወደ ህዝብ ይቅርብሽ በሏት!

አገሬን ብዬ መጥቼም አይባልም። ከኔ በፊትም በኋላም አገሪቱ ሰዉ የላትም አልነበራትም እንደማለትም ነዉ። ከኔ በፊት ሰዉ አልነበረም ይመስል ሕዝባዊ ለማድረግ መሞከርም ተገቢ አደለም።

ሰው ሀገር ለፍቼ ያመጣሁትን.. በማለትም ሁሉም አገር ሰዉ ያለበት እንጂ እዚ ያለዉ እንስሳ ወይም ግዑዝ ነዉ ማለት እንዳይመስል መጠንቀቅና ወደ አገር የሚመጡ ሌሎች ዳያስፖራዉንም በአገሪቷ እንቅስቃሴ እንዳያረጉ መቀስቀስም እንዳይሆንባት ለምትናገረዉ በማስተዋል ቢሆን መልካም ነዉ።

ሲጀምር ሰዉየዉ (ጠቅላዩ) የበለጠ እንዳይሰራ ከዚያ ከዚህ ከተለያየ በኩል ካሉት ጥቃቅን ችግር ፈጣሪዎች የተለያዩ አካላትና ግለሰቦች በላይ እዚሁ በጉያዉ ያሉቱ ደጋፊና ወዳጅ መስለዉ የሚነግዱት ከተለዩት የአገሪቱ ጠላቶች የከፉ ናቸዉ።

ዉስጥ ያሉት ከነኛ ይከፋሉ። አጋጣሚን እየተጠቀሙ ያለ ጥይት ከተማን የሚያጮሁ፤ ሕዝቡን በኢኮኖሚ የሚጎዱና የሚያጯጩኹ የዉስጥ ሽብርተኞች ናቸዉ።
አገሪቱ በከፍተኛ ሁኔታ እንድትጎዳ መንግስት አልቻለም እንዲባል እያመቻቹ ካሉት ዋነኞቹ ከዉስጥ እንዲህ ያሉ ዉንብድና እየፈጸሙ ያሉቱ ናቸዉ። ሕዝብን የማደህየት እንጂ እነሱማ ምርጫ አላቸዉ።

ስለዚህ ይቺን በረከት ወርቁ የተባለች እህትን ከሰሞኑን ክስ መቅረቡን ተከትሎ ጥፋት የለኝም ካለች አለ ካለዉ አካል ጋር እዛዉ በአግባብ መከታተል እንጂ ዋስትናዋን ከልክለዉ መልሰዉ ወደ እስር ቤት እንዳያስገቧትና ወደ ሌላ ተጨማሪ ወንጀል እንዳትገባ ጥንቃቄ እንድታደርግ ምከሯት!

የፍርድ ሂደትን፤ በቀጠሮ ላይ ያለ ጉዳይን መግለጽ.. በራሱ ወንጀል ነዉ። ከፍርድ በኋላም ሚዲያ ላይ ያለ ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ በፎቶም ሆነ በጽሑፍ መግለጽ ይህም ወንጀል ነዉ። (የሕጉን ድንጋጌና ክልከላዎች በተግባር ካለዉጋ ለግንዛቤም ከታች አስቀምጠናል ይመልከቱ)

ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ደሞ እንዲህ ባሉ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተለጠፉ በሚመዘብሩ ግለሰቦች ላይ መንግስት በሚወስዳቸዉ እርምጃዎች እንደ አገር እንደ ሕዝብ ከጎኑ በመቆም አብረዉ ሊያግዙት በጋራ የመጠበቅ ኃላፊነት የራሱም ነዉ። ከራስ ፈቃድ ባለፈ በሕግም አስገዳጅ ነዉ። ከሚጎዱት ሳይሆን ከእዉነት ጋር መተባበር አገርን ራስን መጠበቅ ኃጢአት አደለም!! በቀጣይም እንዲህ ባሉት ላይ በመላ አገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ ባለሥልጣናትና መሰል ግንኙነት ፈጥረዉ በሚመዘብሩት ላይ መንግስት በሚወስደዉ እርምጃዎች ከጎኑ መቆም አግባብ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። ሻሎም!

የአርቲስት ገነት ንጋቱን ክስ በተመለከተ በካዉንስሉ በኩል ስለሆነዉና በዚህ ላይ ስለጠቅላላዉ ጉዳይ መረጃዉን ይዘናል። ይጠብቁን!

በአሜሪካ ጆርጂያ ግዛት ውስጥ በተካሄደ የኢትዮጵያውያን ግብረሰዶማውያን ሰርግ ላይ ተገኝቶ የተነሳው ፎቶ፣ ቴዲ አፍሮ በጭንብል የሸሸገውን ግብረሰዶማዊ ማንነቱን የሚያጋልጥ ትልቅ ማስረጃ ነው❗...
17/04/2026

በአሜሪካ ጆርጂያ ግዛት ውስጥ በተካሄደ የኢትዮጵያውያን ግብረሰዶማውያን ሰርግ ላይ ተገኝቶ የተነሳው ፎቶ፣ ቴዲ አፍሮ በጭንብል የሸሸገውን ግብረሰዶማዊ ማንነቱን የሚያጋልጥ ትልቅ ማስረጃ ነው❗️

የሙት መንፈስ አዝማሪ ‼️የዘፈነለት አባይ ሲመረቅ ሄዶ ያላየ " የዘፈነለት የባህር በርን ለማግኘት ጥረት ሲደረግ ያልደገፈ'' የጮኸለት አድዋ በድንቅ ሁኔታ ተገንብቶ የዓለም መሪዎች መጥተው ...
17/04/2026

የሙት መንፈስ አዝማሪ ‼️
የዘፈነለት አባይ ሲመረቅ ሄዶ ያላየ " የዘፈነለት የባህር በርን ለማግኘት ጥረት ሲደረግ ያልደገፈ'' የጮኸለት አድዋ በድንቅ ሁኔታ ተገንብቶ የዓለም መሪዎች መጥተው ሲጎበኙ ትንፍሽ ያላለ ተራ አዝማሪ ነዉ። ኢትዮጵያን ያሽመደመዱ ነገስታትን እየደገፈ የሚያስለቅስ አሉባልተኛ ነዉ። ወያኔ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ያዙኝ ልቀቁኝ ስትል እንደነ ፍቅር አዲስ ነቀአ ጥበብ የሰራዊታችን የሞራል ደጀን ሁነው ወደ ጦር ግንባር ሲተሙ ትንፍሽ ያላለ ፈሪ ዛሬ ምን ተግኝቶ ነው ከፋፋይ ትርክት ለመፍጠር የሚጮሀው።

በአማራ ክልል የጽንፈኞች መንጋ የአማራን ህዝብ ሲገድል፣ ሲዘርፍ እና የክልሉን ህዝብ መውጫ መግቢያ ያሳጣን የሻቢያ ተላላኪ የጽንፈኛ ፋኖ ተግባር ለማውገዝ አንድ ስንኝ ግጥም መተንፈስ አቃተውና ምቹ ከተማ፣ ምቹ ኢትዮጵያን ለመፍጠር እየተጋ ያለን መንግስት በአሽሙር ለመሸንቆጥ ምነው ያዙኝ ልቀቁኝ አለ። የመጣን ሁሉ በአሽሙር ለመናገር የመንደር ውስጥ ወሬ አድማቂ መሆን በቂ ነዉ። የሙት ነገስታት አምላኪ።

የኔ አገር ተስፋ አላት!የሞተችው የእሱ ናት **********እንኳን ልትሞትና ድንኳን ሊጣልላት÷የመሀሉ ወጥቶ ዳር ሊገተርባት÷መራመጃ ያጣች ቀኑ ጨልሞባት÷ገና ትጓዛለች አገሬ ተስፋ አላት።አገ...
17/04/2026

የኔ አገር ተስፋ አላት!
የሞተችው የእሱ ናት
**********
እንኳን ልትሞትና ድንኳን ሊጣልላት÷
የመሀሉ ወጥቶ ዳር ሊገተርባት÷
መራመጃ ያጣች ቀኑ ጨልሞባት÷
ገና ትጓዛለች አገሬ ተስፋ አላት።
አገሬን አትስፈር በአፄዎቹ ቁና÷
በጨለመ አንደበት በቆመ ህሊና÷
ገና ትጓዛለች የኔ አገር ተስፋ አላት÷
ጉዞዋ የማይቆም ደስታ የሞላባት÷
ፍቅርና አንድነት ውለው የሚያድሩባት÷
ገጠር ከተማዋን ልማት ያደመቃት።
ተስፋዋ ብሩህ ነው ቅርብ የሚታይባት÷
አባይ ተገድቦ ውሎ ያደረባት÷
መሀል ዳሯ ሁሉ የሚገነባባት።
አገሬ ተስፋ አላት ገና ትጓዛለች÷
በዘመን ጉዞዋ ጋራ ትዞራለች÷
ታሪክ እያደሰች ታሪክ ትፅፋለች።
የኔ አገር ተስፋ አላት ትጓዛለች ገና÷
ዕድገት የሞላባት የሁሉ እናት ሆና÷
ምድሯ ተሸፍኖ በልማት ደመና።
ምን ተስፋ ብትቆርጥ ተውጠህ በቅዠት÷
ሁሉን አጨልመህ ክፉ ብታሟርት÷
ከንፈር ለማስመጠጥ ጧት ማታ ብትዋትት÷
አማረልኝ ብለህ ብትዘምር ብሶት÷
ጉዞዋ አይገታም አገሬ ተስፋ አላት።
የኔ አገር ተስፋ አላት ሀራሟ ነው ድንኳን÷
የጨለመ አዕምሮ አይጎበኝም ምድሯን።
ህሊናህ ቢታመም ቢሆን ጨለምተኛ÷
አዕምሮህ ቢመታ በክህደት መጋኛ÷
በመቃብሯ ላይ ምኞትህ ቢተኛ÷
የኔ አገር ተስፋ አላት ድንኳን አትተክልም÷
ልጇን ውጭ አውጥታ ዳር አትገትርም።
እሱ ያንተ ነበር የአፄዎችህ ዘመን÷
"አሽከር"ዳር አቁሞ በመሀል መበዬን÷
ያልከው ዕውነት ነበር ባንተ ምናብ ዘመን÷
መሀል የአንተ ሆኖ ሌላው ውጭ እሚሆን÷
አንተ ፈራጅ ቀዳጅ ሌላው የሚባዝን።
ቁስል አትነካካ በነተበ አዕምሮህ÷
ዲናር ለማጋበስ ባገር ሞት አውጀህ።
ተውልኝ አገሬን ይልቅ ልለምንህ÷
ባፄ ነገስታቶች ናፋቂ ምናብህ÷
ሞታለች አትበለኝ ምኞት ተበድረህ÷
ሞት ከሚመኙላት ቃላትን ተውሰህ።
ሞታለች አትበላት ይህችን የኔን አገር÷
ፈጣሪ ያደላት ሁሉንም በመቼር።
ሞታለች አትበለኝ አገሬ ተስፋ አላት÷
ዳርና መሀሉ አብሮ የቆመላት÷
እኩል ተቀምጦ በአንድ እሚፈርድላት÷
ሳይንስ ቴክኖሎጂ የሚደባብሳት÷
ዕውቀት ቤቷ ገብቶ ብርሀን የሰጣት÷
አረንጓዴ አሻራ ምድሯን ያለበሳት።
ሂድ ለራስህ አልቅስ ድንኳን ትከልና÷
ዕርምህንም አውጣ መሰልክን ጥራና÷
በኔ አገር አይኖርም የበደል ደመና።
ብትፈልግ ኡኡ በል አስነካው ጩኸቱን÷
ብቻህን አትበላም ደግመህ የትናንቱን።
አገር ሞቷል አትበል አንተ ራስህ ሞተህ÷
ጥቅም በማጋበስ በስስት ተለክፈህ።
ሞታለች አትበለኝ በሞተ አንደበትህ÷
በነተበ አዕምሮ ባገሬ ሞት ፈርደህ÷
ዲናር የመሰብሰብ ሆድህን አስልተህ።
ሞት አትመኝላት ይህችን የኔን አገር÷
ፍቅር የሞላባት የደጋጎች ምድር።
ችግር ቢደራረብ ጠላት ቢበዛባት÷
ባንዳ እንዳሸን ፈልቶ ሰላሟን ቢያውካት÷
ንፁሐን በመግደል ሀዘን ቢልክባት÷
ሞትን እየጠራ ተስፋ ሊያስቆርጣት÷
አትነቃነቅም አገሬ ብርቱ ናት÷
ሞተው የሚያኖሯት አዕላፍ ጀግኖች አሏት።
ይልቅ ልብ ግዛ ተመከር ተዘከር÷
ሞት አታሟርትባት በ"ሰላሳ ዲናር"።
ቢሻህ ድንኳን ትከል ኡኡ በል ለራስህ÷
አገሬን ግን ተዋት አትንካት በሟርትህ÷
ገድለህ አትቅበራት በጨለመ አዕምሮህ።
ቢሻህ ድንኳን ትከል ተቀምጠህ አልቅስ÷
ከል ተጎናፀፍ ጥቁር ጨርቅ ልበስ÷
በሀገሬ ሞት ግን በጥቅም አትንገስ።
ክፉ አሳቢው በዝቶ ሞቷን ቢመኝላት÷
መንደርተኛው ሁሉ ቢረባረብባት÷
ጥላቻ ቢሰበክ ዘር ቢቆጠርባት÷
በደም የሚነግድ ባንዳ ቢፈላባት ÷
ጠላት ተጠራርቶ ሴራ ቢያደራባት÷
አትንበረከክም አገሬ ብርቱ ናት÷
ሞተው የሚያኖሯት አዕላፍ ጀግኖች አሏት።
እንኳን ልትሞትና ድንኳን ሊጣልላት÷
የመሀሉ ወጥቶ ዳር ሊገተርባት÷
ባንዳ ተጠራርቶ ዕዝን ሊበላባት÷
ጠላት ዕፈይ ብሎ ተዝካር ሊያወጣባት
ገና ትጓዛለች የኔ አገር ተስፋ አላት።

የኢትዮጵያ የቱሪዝም አዲስ ምዕራፍ፡ ከህልም ወደ እውነታ!​ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ጸጋዎቿ የታደለች ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የተከናወኑት ...
24/03/2026

የኢትዮጵያ የቱሪዝም አዲስ ምዕራፍ፡ ከህልም ወደ እውነታ!

​ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ጸጋዎቿ የታደለች ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት የተከናወኑት የቱሪዝም ልማቶች ዘርፉን ወደ አዲስ የብልጽግና ምዕራፍ አሸጋግረውታል። እንደ ወንጪ፣ ጎርጎራ እና ኮይሻ ያሉ በ"ገበታ ለሀገር" የተገነቡ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ድብቅ ጸጋዎች ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ በማድረግ፣ በአካባቢው ለሚገኙ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጥረዋል። በከተማ ደረጃም ቢሆን የአንድነት፣ ወዳጅነት እና የእንጦጦ ፓርኮች እንዲሁም የዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ ኢትዮጵያ ያላትን የታሪክና የተፈጥሮ ሀብት በዘመናዊ መንገድ የማልማት አቅሟን በተግባር አሳይተዋል። እነዚህ የተቀናጁ ስራዎች ቱሪዝም የኢኮኖሚው ዋነኛ ምሰሶ እንዲሆን በማድረግ፣ የዜጎችን የኑሮ ደረጃ በመቀየር ረገድ የማይተካ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።

ሰበር ዜና፦ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ እየተካሄደ ያለው “ጦርነት በድል ተጠናቋል” (War has been won) ሲሉ በይፋ አወጁ።ፕሬዝዳንቱ አክለውም “ጦርነቱን የምናቆመው ይመስለኛል።...
24/03/2026

ሰበር ዜና፦ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ እየተካሄደ ያለው “ጦርነት በድል ተጠናቋል” (War has been won) ሲሉ በይፋ አወጁ።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም “ጦርነቱን የምናቆመው ይመስለኛል። በእርግጠኝነት ግን አሁን መናገር አልችልም” ብለዋል።
BRICS News

01/03/2026
የተገደሉ የኢራን ከፍተኛ ወታደራዊና የደህንነት አመራሮች ዝርዝር​በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምር የአየር ጥቃት የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒን ጨምሮ የሚከተሉት ቁልፍ የሀገሪቱ አመ...
01/03/2026

የተገደሉ የኢራን ከፍተኛ ወታደራዊና የደህንነት አመራሮች ዝርዝር

​በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምር የአየር ጥቃት የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒን ጨምሮ የሚከተሉት ቁልፍ የሀገሪቱ አመራሮች መገደላቸው ተረጋግጧል፦

​1. አድሚራል አሊ ሻምካኒ (Ali Shamkhani)
​የመሪው የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ እና የመከላከያ ምክር ቤት ጸሐፊ። በኢራን የጦር እና የደህንነት ውሳኔዎች ላይ ቀዳሚው ሰው ነበሩ።

​2. ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ፓክፑር (Mohammad Pakpour)
​የኢራን እጅግ ሀያል የጦር ክፍል የሆነው የሀብረተሰብ ጥበቃ ሰራዊት (IRGC) ዋና አዛዥ። ሚሳኤልና የውጭ ኦፕሬሽኖችን የሚመሩ ነበሩ።

​3. ሳላህ አሳዲ (Saleh Asadi)
​የኻታም አል-አንቢያ ማዕከላዊ القيادة የደህንነት ኃላፊ። የጦር እቅዶችን እና ወታደራዊ መረጃዎችን የሚያቀናጁ ቁልፍ ሰው።

​4. ሆሴን ጃባል አሚሊያን (Hossein Jabal Amelian)
​የላቁ የጦር መሳሪያዎች እና የሚሳኤል ምርምር ድርጅት (SPND) ሊቀመንበር።

​ሌሎች የተገደሉ የቤተሰብ አባላት፦
​የአያቶላ አሊ ኻሜኒ ልጅ፣ አማች እና የልጅ ልጅ በመኖሪያ ግቢያቸው ላይ በተፈጸመው ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።


✅​ፎሎው በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
​ #ኢራን #ሰበርዜና

በእስራኤል እና በአሜሪካ ጥቃት የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ካሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ ሰዎች በኢንቅላብ አደባባይ (Enghelab Square) ተሰብስበው ስሜታቸውን ሲገልጹ።       ...
01/03/2026

በእስራኤል እና በአሜሪካ ጥቃት የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ካሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ ሰዎች በኢንቅላብ አደባባይ (Enghelab Square) ተሰብስበው ስሜታቸውን ሲገልጹ።

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hola Media ሆላ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share