26/09/2023
የተወደዳችሁና እጅግ የተከበራችሁ ልማት ወዳድ የራግዲና ማዞሪያ ከተማ ባለሀብቶች ፣ ወጣቶች ፣ሴቶች ፣ ሺማግሌዎች ፣የግንበታ ተቋራጮች ፣አንደንድ ከከተማዋ ውጭ የሆኑ በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች የሚገኙ ባለሀብቶች ፣የህብረተሰብ ተሳትፎ አስተባባሪ ኮሚቴዎች እና መለው የከተማው ነዋሪዎች ለከተማዋ ልማት እንደ አቅማቹ መጣን በወጣቹት ብር የጠየቃቹትን ፈጽመናል ለሌላ ልማት ተዘጋጁ እንኳን ደስ አለቹ !!!
ከተማችን የህብረተሰብ ተሳትፎ ስራዎችን በማጠናከር ዘላቂ የሆነ ዕድገቷን ተረጋግጣለች !!!
ከተሞች የወረዳችን ኢኮኖሚ ዋና መናህሪያ በመሆናቸው እድገታቸው በተባለው ልክ ሊረጋገጥ ወይም ሊሳካ የሚችለው በመንግስት ጥረት ብቻ አለመሆኑ ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ ነው፡፡
በመሆኑም የከተማችን እድገት ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማረጋገጥ የህብረተሰብ ተሳትፎ ስራዎችን በማጠናከር ህብረተሰቡን የልማቱ አካል ከማድረግ ባለፈ ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ተከታታይነት ያላቸው ስራዎችን በመስራት ላይ እንገኛለን፡፡
ነዋሪዎች በከተማችን የሚያነሷቸውን ዘርፈ ብዙ ጉዳዮችንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው እያሰሩ ነው !!!በ2014ዓ/ም ከህብረተሰቡ የተሰበሰበው ብር ለከተማው የውሃ ተቋም የትራንስፎርመር ግዢ እንዲውል ህብረተሰቡ በመስማማቱ የትራንስፎርመር ፣የመስመር ዝርጋታ እና የቆጦሪ ክፊያ የተከፈለ ብሆንም መብራት ሀይል እንደ ሀገር ገጠመኝ በለው የትራንስፎርመር እጥረት የተነሳ ሰይመጣ በመቆየቱ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መቆየቱ ይተወቃል ።ይህንን ችግር ለመፍታት የሳንኩራ ወረዳ አስተዳደር ፣የወረደው ፓርቲ እናት የአስተዳደር ጽ/ቤት የኢትዮጵያ መብራት ሀይል ሆሳዕና ዲስትሪክት እና ሀዋሳ ቅርንጫፍ ድረስ በመንቀሳቀስ ችግሩ እንዲፈታ በማድረጋቸው ዞሬ ችግሩ ተቀርፎ የተጠየቀው አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መግኛት ተችሏል ።ለዚህ ምስጋናችን የላቀ ነው ።
በድጋሚ እንኳን ደስ አለቹ እንኳን ደስ አለን !!!