04/09/2026
የምግብና የጤና ግብዓት ቁጥጥር የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃጸም ግምገማ መድረክ ተሳታፊዎች በአርባ ምንጭ ከተማ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በቦታው ተገኝተው በመጎብኘት የእግር ጉዞ አካሄዱ።
ነሐሴ 28 / 2018 ዓ.ም አርባ ምንጭ ከተማ — የጉባኤው ተሳታፊዎች ከአርባ ምንጭ ከተማ ባህል ማዕከል እስከ ሲቻ አደባባይ የእግር ጉዞ ያደረጉ ሲሆን፥ በዚሁ ወቅት በከተማው አስተዳደር የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን መመልከት ችለዋል፡፡
በተከናወነው የኮሪደር ልማት መደመማቸውን በተመለከተ አስተያየታቸውን የሰጡን የጉባኤው ተሳታፊዎች፥ ለቱሪስት መናኸሪያ ለሆነችው አርባ ምንጭ ከተማ የተገነባው የኮሪደር ልማት ልዩ ድምቀትና ውበት እንዳጎናጸፋት ተናግረዋል፡፡
ከዓመታት በፊት በዚሁ ከተማ ተመሳሳይ የምግብና የጤና ግብዓት ቁጥጥር እቅድ አፈፃጸም ግምገማ መድረክ መካሄዱን ያስታወሱት ተሳታፊዎቹ፥ የዘንድሮውን ልዩ የሚያደርገው ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎች ይበልጥ ምቹ የሚያደርጉ የመሰረተ-ልማት ዝርጋታዎች በጥራትና በስፋት የተከናወኑበት በመሆኑ የተለየ ስሜት እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል፡፡