የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውበት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  ውበት This is all about central Ethiopian information

ርዕሰ መስተዳድር  እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር) የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን አስመልክቶ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች  ም...
19/11/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰው (ዶ/ር) የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን አስመልክቶ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ምልከታ አደረጉ ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በክልሉ አስተናጋጅነት የሚካሄደዉን የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን አስመልክቶ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዛሬ ምልከታ አድርገዋል ።

‎በዓሉን ለመሳተፍ ወደ ከተማዋ የሚገቡ እንግዶች ለመቀበል እየተሰሩ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ያሉበት ደረጃ ተዘዋዉረው የጎበኙት ክብር ፕሬዝዳንቱ የተሰሩ ስራዎቹም በመልካም አፈፃፀም ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

የብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ‎በዓል ትልቅ ሀገራዊ በዓል በመሆኑ ህብረ ብሔራዊነት በማጠናከር የተጀመሩ ቀሪ ተግባራት በአጭር ጊዜ በፍጥነትና በጥራት ማጠናቀቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል ።

የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ  የአመራሮች ስልጠና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  መካሄድ  ጀምሯል።ስልጠናው  የአመራሩን የምናብ እይታ ከፍ የሚያደርግ የመፈፀምና የማስፈፀም...
19/11/2025

የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራሮች ስልጠና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መካሄድ ጀምሯል።

ስልጠናው የአመራሩን የምናብ እይታ ከፍ የሚያደርግ የመፈፀምና የማስፈፀም ብቃትና ጥራት በማሳደግ የተጀመሩ ለውጦች ቀጣይነት ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር ነው።

ስልጠናው "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬን ጨምሮ ለሚቀጥሉት 9 ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።

ስልጠናውን ያስጀመሩት በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)ስልጠናው የአመራሩን የምናብ እይታ ከፍ የሚያደርግ የመፈፀምና የማስፈፀም ብቃትና ጥራት በማሳደግ የተጀመሩ ለውጦች ቀጣይነት ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል።

ስልጠናው የአመራሩን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነቡ ልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚዳሰሱበት መሆኑንም ተናግረዋል።

ስልጠናው በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣የገጠርና የመዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ፣የኢንዱስትሪ ዘርፍ ፣የከተማ ልማት እንዲሁም የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ በሚል ርዕሶች ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።

ስልጠናው በክልል ማዕከልና በሁሉም ዞንና ልዩ ወረዳ ደረጃ በተመሳሳይ እየተሰጠ ሲሆን 5ሺ በላይ አመራሮች እንደሚሳተፉ ያስታወቁት ኃላፊው ከስልጠናው በተጓዳኝ የተግባር የመስክ የልማት ስራ ጉብኝቶች እንደሚካሄድ ተጠቁሟል።

Address

Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውበት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share