Harari Regional Health Bureau የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Harar
  • Harari Regional Health Bureau የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ

Harari Regional Health Bureau የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ This is official page of Harari Regional Health Bureau. this page delivers News, Health related information and vacancy announcements on daily basis.

የተቀናጀ የትምህርት ቤት አቀፍ የጤና አገልግሎት ዘመቻ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ። በዘመቻው ከ77 ሺህ በላይ ህፃናት ተማሪዎች የጤና አገልግሎት መስጠት ተችሏ...
18/06/2026

የተቀናጀ የትምህርት ቤት አቀፍ የጤና አገልግሎት ዘመቻ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

በዘመቻው ከ77 ሺህ በላይ ህፃናት ተማሪዎች የጤና አገልግሎት መስጠት ተችሏል።

የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን እንደገለጹት በክልሉ ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው ዘመቻው የትምህርት ማህበረሰቡን ጤና ከመጠበቅ አንፃር በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።

በዘመቻውም ከ77 ሺህ በላይ ህፃናት ተማሪዎችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረግ ችለናል ብለዋል።

ይህን አፈፃፀም መሰረት በማድረግ መልካም ውጤቶችን ማስቀጠል ውስንነቾች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ይገባል ብለዋል።

በቀጣይም በትምህር ቤቶች የሚሰጡ ዘመቻዎች ግብዓት በመሰብሰብ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ መስራት ይገባል ብለዋል።

የቢሮ ኃላፊው ለስራው ስኬት አስተዋጻ ያበረከቱ በተለይም የጤና ባለሙያዎች ፣የትምህርት ቤት አመራሮች፣ መምህራን እና ወላጆች ላደረጉት የተቀናጀ ውጤት ምስጋና አቅርበዋል።

የተቀናጀ የትምህርት ቤት አቀፍ የጤና አገልግሎት ዘመቻ አጠቃላይ ስራ አፈጻጸም በክልሉ ጤና ቢሮ የወባና የተዘነጉ ሀሩራማ በሽታዎች አስተባባሪ አቶ አብዲ አሊዪ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የክልሉ ጤና ቢሮ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል ዳይሬክተር በበኩላቸው በዘመቻው የተለያዩ የጤና አገልግሎቶች መሰጠታቸውን ገልጸው በተለይም የአይን ምርመራ ፣ የቲቢ በሽታ፣ የስርዓተ ምግብ ልየታ እና ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን እንዲሁም የአንጀት ጥገኛ ትላትል ኪኒን እደላ ተደርጎል ብለዋል።

የጤና አገልግሎት ዘመቻው የጤና እክሎችን ቀድሞ በመለየት ተገቢውን ህክምና ከመስጠት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደነበረው ጠቁመዋል።

17/06/2026
16/06/2026
በ PHEM-DHIS2 ዙሪያ  ለጤና ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው መሠረታዊ ስልጠና ተጠናቀቀ።የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲ...
14/06/2026

በ PHEM-DHIS2 ዙሪያ ለጤና ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው መሠረታዊ ስልጠና ተጠናቀቀ።
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከክልሉ ወረዳዎችና የጤና ተቋማት ለተውጣጡ ባለሙያዎች በ PHEM-DHIS2 ዙሪያ ሲሰጥ የነበረውን መሠረታዊ ስልጠና አጠናቀቀ።

ከሰኔ 3 እስከ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በድሬደዋ ከተማ በተካሄደው በዚህ ስልጠና ላይ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

በስልጠናው መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ፎዚህ ሳሊህ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስልጠናው በአገር ደረጃ ዘርፉን ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። በተለይም የህብረተሰብ ጤና ቁጥጥር የቅኝት መረጃዎችን በወቅቱና በተሟላ መልኩ ከጤና ኬላ ጀምሮ እሰከ ላይኛው የጤና እርከን ለመላክ፣ ለመተንተንና ለውሳኔ አሰጣጥ ተግባር እንዲውሉ በማድረግ ረገድ ሥርዓቱ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ጠቁመዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም ወቅቱን የጠበቀና የተሟላ የቅኝት መረጃ በየደረጃው ለሚከሰቱና ሊከሰቱ ለሚችሉ የጤና ስጋቶችና የበሽታ ወረርሽኞችን አስቀድሞ ለመተንበይና ለመለየት የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።

ይህም አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጁነትና የምላሽ ሥራዎች ውጤታማና በተቀላጠፈ መልኩ ለመስራት ወሳኝ መሆኑን በማስታወቅ፣ ሁሉም የጤና ተቋማትና የወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤት ባለሙያዎች መረጃዎችን በወቅቱ ወደ መረጃ ቋቱ በማስገባትና በመተንተን የበኩላቸውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህ በሐረሪ ጤና ቢሮና በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ትብብር የተሰጠው ስልጠና የክልሉን የጤና መረጃ አያያዝ ወደ ላቀ የዲጂታል ምዕራፍ የሚያሸጋግር ስትራቴጂካዊ እርምጃ ሲሆን፣ ባለሙያዎች በቴክኖሎጂ የታገዘ የቅኝት መረጃ ሥርዓትን በመዘርጋት ሊከሰቱ የሚችሉ የወረርሽኝ ስጋቶችን በፈጣን ምላሽ ለመግታት ያላቸውን ዝግጁነት የሚያጠናክርና ጥራቱን የጠበቀ የተቀናጀ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ሥራን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ትልቅ መሠረት እንደሚጥል ይታመናል።

ህብረተሰቡን በጤና አገልግሎት  አሰጣጥ  ለማሳተፍ  በቱክረት ይሰራል:- አቶ መሀመድ ሱሌይማን። የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ በHuman Centered Design (HCD) ዙሪያ ለጤና ባለሞያዎች ...
13/06/2026

ህብረተሰቡን በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ለማሳተፍ በቱክረት ይሰራል:- አቶ መሀመድ ሱሌይማን።

የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ በHuman Centered Design (HCD) ዙሪያ ለጤና ባለሞያዎች የግንዛቤ ማዳበሪያ ስልጠና ሰቷል።

በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፋት በክልሉ ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከል ጤና ማበልጸግ ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ሱለይማን እደተናገሩት ህብረተሰቡን በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ለማሳታፍ የግንዛቤ ስራዎች ለይ ቱክረት ተደርጎ ልሰራ ይገባል ብለዋል።

በተለይ በHuman Centered Design (HCD) ዙሪያ ለጤና ባለሞያዎች የሚሰጠው የግንዛቤ ማዳበሪያ ስልጠና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ባለሞያዎች በትክክል ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስበዋል ።

በክልሉ ጤና ቢሮ የክትባት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ሰይፉዲን አሚን በበኩላቸው ስልጠናው በቀጣይ እስከ በማህበረሰብ ድረስ እንደሚሰጥ ገልጸዋል ።

በዛሬው መድረክ የክልሉ ጤና ቢሮ ባለሞያዎች፣ጤና ጣቢያ ሀላፊዎች፣የወረዳ ጤና ኤስፐርቶች እና የዘርፉ ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።

13/06/2026

የሀዘን መግለጫ

በጤና ሚኒስቴር እና በተጠሪ ተቋም ለረጅም አመታት በተለያዩ የሙያ እና አመራርነት ያገለገሉት፣ አሁን ላይ የሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ አቶ መሓሪ ተከስተ ባደረባቸዉ ህመም በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ተለይተዋል።

በስራ ባልደረባችን አቶ መሃሪ ተከስተ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቹ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን እንመኛለን።

በሐረሪ ክልል ለጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው የ‘IUCD’ ስልጠና ተጠናቀቀሐረር (ሰኔ 6/2018 ዓ.ም)፦ በሐረሪ ክልል ለሚገኙ የደረጃ አራት የጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች ለ11...
13/06/2026

በሐረሪ ክልል ለጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው የ‘IUCD’ ስልጠና ተጠናቀቀ
ሐረር (ሰኔ 6/2018 ዓ.ም)፦ በሐረሪ ክልል ለሚገኙ የደረጃ አራት የጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች ለ11 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የማኅፀን ውስጥ የእርግዝና መከላከያ ዘዴ (IUCD Scale Up) ስልጠና በዛሬው ዕለት በስኬት መጠናቀቁ ተገለጠ።

ይህ ስልጠና የተዘጋጀው በጤና ሚኒስቴር፣ በሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ እና በኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማኅበር (FGAE) በጋራ በመሆን ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በክልሉ በሚገኙ የጤና ኬላዎች የሚሰጠውን የስነ-ተዋልዶ እና የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ይበልጥ ማጠናከርና ማስፋፋት ነው።

ባለሙያዎቹ በስልጠናው ያገኙትን ቲዎሪያዊ እውቀት በተግባር እንዲያዳብሩ ለማድረግ፣ ለአምስት ቀናት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ወረዳዎች እና በሐረሪ ክልል በሚገኙ የተለያዩ የጤና ተቋማት ውስጥ የተግባር ልምምድ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል።

የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አብዲ አሚን በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ እንደገለጹት፣ በጤና ኬላ ደረጃ የሚሰጠውን የረጅም ጊዜ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት (IUCD)ለማኅበረሰቡ ተደራሽ ማድረግ የእናቶችን እንግልትና የኑሮ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል። ኃላፊው አክለውም ይህ አገልግሎት እስከ ታችኛው የጤና መዋቅር ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም ዶ/ር አብዲ አሚን ለሰልጣኞች የስራ አቅጣጫ የሰጡ ሲሆን፣ ባለሙያዎቹ የወሰዱትን ስልጠና ወደ ተግባር በመለወጥ በተመደቡበት የጤና ተቋም ማኅበረሰቡን በታማኝነት፣ በቅንነት እና በጥራት የማገልገል ታላቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ወረዳን መሰረት ያደረገ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት መድረክ እያካሄደ ነው።ሐረር — የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ወረዳዎችን ማዕከል ያደረገ የ2019 በጀት ዓመት ዕ...
10/06/2026

የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ወረዳን መሰረት ያደረገ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት መድረክ እያካሄደ ነው።

ሐረር — የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ወረዳዎችን ማዕከል ያደረገ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ እና የሁለተኛውን የሦስት ዓመት የጤናው ዘርፍ የመካከለኛ ዘመን የልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ዝግጅት መድረክ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

በዕቅድ ዝግጅት መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢማን ዜይዳን፤ ወረዳዎች የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዳቸውን ሲያዘጋጁ ካለፈው በጀት ዓመት አፈጻጸም ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተገቢውን ተሞክሮ መውሰድ እንዳለባቸው አሳስበዋል። ዕቅዱ በጤናው ዘርፍ ላይ ተጨባጭ ለውጥ በሚያመጣ መልኩ በጥናት ላይ ተመስርቶ መዘጋጀት እንዳለበትም ገልጸዋል።

ዶክተር ኢማን አክለውም በወረዳዎች የሚታቀዱ ዕቅዶች የወረዳውን የመፈጸም አቅም ያገናዘቡ መሆን እንዳለባቸው ጠቁመው፤ በተለይም በጤና ተቋማት የሚገኙትን የሰው ኃይል፣ በጀት እና የህክምና ግብዓቶች ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በእቅድ ዝግጅት ወቅት ያለፉት ዓመታት ተሞክሮዎችን በመቀመር የ2019 ዓ.ም ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ውጤት ተኮር ማድረግ እንደሚገባ ያሳሰቡት ምክትል ቢሮ ኃላፊዋ፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የመጨረሻ አቅማቸውን በመጠቀም ለዕቅዱ ስኬታማነት በትኩረት እንዲሠሩ አሳስበዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ የዕቅድ፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክተር አቶ አብዱሰመድ አሊ በበኩላቸው፤ እያንዳንዱ ወረዳ በሥሩ የሚገኙ ከጤና ጣቢያ እስከ ጤና ኬላ ያሉ የጤና ተቋማትን ሁሉ ያማከለ እና ከኅብረተሰቡ የሚነሱ መሠረታዊ የጤና ጥያቄዎችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ዕቅድ ማዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በመድረኩም በአቶ አብዱሰመድ አማካኝነት የዕቅድ ዝግጅት ሂደቱንና አቅጣጫዎችን የሚያብራራ የመወያያ ጽሑፍ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

ለአምስት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ከወጣው መርሃግብር ለማወቅ የተቻለው በዚህ የዕቅድ ዝግጅት መድረክ ላይ የወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የጤና ጣቢያ ኃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችና አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ሞት ቅኝት እና ምላሽ አሰጣጥ ላይ ትክረት ተደርጎ መስራት እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር አሳሰበ።የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ሞት ቅኝት እና ምላሽ (MPDSR) ስርዓት ዙሪ...
10/06/2026

የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ሞት ቅኝት እና ምላሽ አሰጣጥ ላይ ትክረት ተደርጎ መስራት እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር አሳሰበ።

የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ሞት ቅኝት እና ምላሽ (MPDSR) ስርዓት ዙሪያ የጋራ ፎረም በሐረሪ ክክልል ተካሄደ።

በጋራ የውይይት ፎረሙ የሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ ክልሎች እና ምስራቅ ሀረር ጌይ እንዲሁም የድሬ ደዋ መስተዳድር የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ሞት ቅኝት እና ምላሽ አሰጣጥ የሚሰሩ አካላት ተሳትፈዋል።

በጤና ሚኒስቴር የእናቶች ህፃናትና ወጣቶች
መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ማራማዊት አስፋው እንደተናገሩት የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ለመቀነስ ዘርፈብዙ ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

የእናቶች ሞት ቅኝት እና ምላሽ ስርዓት የፎረም በእናቶችና ህጻናት ሞት ቅነሳ ላይ ዘርፈ ብዙ ለውጦችን አምጥቷል ብለዋል።

ሁሉም ተቋማት ተቀናጅተው መስራታቸው በዘርፉ የተያያዙ እቅዶችን ለማሳካት አስተዋጽኦ እንሚኖረው ጨምረው ገልጸዋል።

የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኢማን ዘይዳን በበኩላቸው በክልሉ እና አጎራባች ክልሎችን ጨምሮ በምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የእናቶችና ህጸናትን ሞት ለመቀነስ ተችሏል፤ብለዋል።

በተለይም በሆስፒታሎች መካከል ያለው ትስስር አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመው መሰል ፎረሞች በጋራ ለመስራት አስፈላጊ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

በጤና ሚኒስተር የእናቶች እና ህጻናት ስራ አስፈጻሚ የእናቶች ጤና ዴስክ ሃላፊ ሲስተር ዘምዘም መሃመድ በሆስፒታሎች መካከል የሪፈራል አግልግሎት ከተገቢው መረጃ ጋር በማጣመር የጤና አግልገሎትን በተገቢው መልኩ መስጠት የሚቻል ስርዓትን ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ፎረሙ የእናቶች ሞትን ለመቀነስ በሆስፒታሎች እና ክልሎች መካከል ግንኙነትን ማጠናከር እንደስቻለ ተናግረዋል።

Address

Harar

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Telephone

+251256661963

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Regional Health Bureau የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Harari Regional Health Bureau የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ:

Share