18/06/2026
የተቀናጀ የትምህርት ቤት አቀፍ የጤና አገልግሎት ዘመቻ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።
በዘመቻው ከ77 ሺህ በላይ ህፃናት ተማሪዎች የጤና አገልግሎት መስጠት ተችሏል።
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን እንደገለጹት በክልሉ ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው ዘመቻው የትምህርት ማህበረሰቡን ጤና ከመጠበቅ አንፃር በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።
በዘመቻውም ከ77 ሺህ በላይ ህፃናት ተማሪዎችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረግ ችለናል ብለዋል።
ይህን አፈፃፀም መሰረት በማድረግ መልካም ውጤቶችን ማስቀጠል ውስንነቾች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ይገባል ብለዋል።
በቀጣይም በትምህር ቤቶች የሚሰጡ ዘመቻዎች ግብዓት በመሰብሰብ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ መስራት ይገባል ብለዋል።
የቢሮ ኃላፊው ለስራው ስኬት አስተዋጻ ያበረከቱ በተለይም የጤና ባለሙያዎች ፣የትምህርት ቤት አመራሮች፣ መምህራን እና ወላጆች ላደረጉት የተቀናጀ ውጤት ምስጋና አቅርበዋል።
የተቀናጀ የትምህርት ቤት አቀፍ የጤና አገልግሎት ዘመቻ አጠቃላይ ስራ አፈጻጸም በክልሉ ጤና ቢሮ የወባና የተዘነጉ ሀሩራማ በሽታዎች አስተባባሪ አቶ አብዲ አሊዪ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የክልሉ ጤና ቢሮ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል ዳይሬክተር በበኩላቸው በዘመቻው የተለያዩ የጤና አገልግሎቶች መሰጠታቸውን ገልጸው በተለይም የአይን ምርመራ ፣ የቲቢ በሽታ፣ የስርዓተ ምግብ ልየታ እና ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን እንዲሁም የአንጀት ጥገኛ ትላትል ኪኒን እደላ ተደርጎል ብለዋል።
የጤና አገልግሎት ዘመቻው የጤና እክሎችን ቀድሞ በመለየት ተገቢውን ህክምና ከመስጠት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደነበረው ጠቁመዋል።