Harari Finance & Economic Cooperation Bureau

Harari Finance & Economic Cooperation Bureau Government organization

የሀረሪ ክልል የCALM ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ለመገምገም የምክክር መድረክ አካሄደ።ሰኔ 6/2018*            *         *           *በሀረሪ ክልል የ...
13/06/2026

የሀረሪ ክልል የCALM ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ለመገምገም የምክክር መድረክ አካሄደ።

ሰኔ 6/2018

* * * *

በሀረሪ ክልል የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የቻናል አንድ ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ፣ በክልሉ እየተተገበረ የሚገኘውን "የአየር ንብረት አፈጻጸም እና የመሬት አያያዝ ፕሮግራም" (CALM) የ2018 በጀት ዓመት የፊዚካልና የፋይናንሻል አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በድሬዳዋ ከተማ የምክክር መድረክ አካሄደ።

በመድረኩ የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ አመራሮች፣ የሸንኮር፣ ሐኪም፣ ዲሬ ጠያራ፣ ኤሬር እና ሶፊ ወረዳዎች የዘርፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የውይይት መድረኩን የከፈቱት የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ አራርሶ፣ የፕሮግራሙ ዋና ዓላማ በአፈጻጸም የታዩ ክፍተቶችን በመለየት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሆነ ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የፊዚካል፣ የፋይናንስ፣ የተዘዋዋሪ ፈንድ እና የ"One Time Investment Fund" ዙሪያ ባለሙያዎች የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡት ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በግምገማውም የውሃ ተፋሰስ ልማት፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ የመሬት ማገሚያና የደን ልማት እንዲሁም የእርሻና ኑሮ ማሻሻያ ተግባራት ምን ያህል እንደተከናወኑና የበጀት አጠቃቀሙም ከፊዚካል ውጤት ጋር ያለው ተመጣጣኝነት የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ መሐመድ አብዱረህማን በዝርዝር አቅርበዋል።

የክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ያህያ አብዱራሂም በበኩላቸው፣ የCALM ፕሮግራም ለኅብረተሰቡ የኑሮ ማሻሻያ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፣ የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠልና የታዩ ድክመቶችን በማረም ለቀጣይ የሥራ ዘመን በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የቻናል አንድ ፕሮግራሞች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ኑረዲን መሐመድ የፕሮግራሙን የመጀመሪያ ምዕራፍ (CALM 1) በማጠቃለል ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ (CALM 2) ለመሸጋገር፣ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅዶቻቸውን እስከ ሰኔ 20 ቀን 2018 ማጠናቀቅ እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥቷል።

በመድረኩ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ምላሽ ተሰጥቶ የተመዘገቡ ስኬቶች የተወደሱ ሲሆን፣ የቀሩ ሥራዎችን ለመጨረስ አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ በመስማማት ተጠናቋል።

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የክልሉን የሀረሪ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ከሪፎርሙ አብይና ቴክኒክ ኮሚቴ ጋር የሪፎርም ፍኖተ ካርታ ዙሪያ ላይና የሪፎርሙ የእስካሁኑ የስራ አፈጻጸም ...
12/06/2026

የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የክልሉን የሀረሪ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ከሪፎርሙ አብይና ቴክኒክ ኮሚቴ ጋር የሪፎርም ፍኖተ ካርታ ዙሪያ ላይና የሪፎርሙ የእስካሁኑ የስራ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄደ ።

ሰኔ 5/2018

* * * *

በፍኖተ ካርታው አገራዊና ክልላዊ ተልዕኮ በላቀ ደረጃ ለመወጣት ተቋማዊ አቅምን ማደራጀት፣ የአሠራር ፍሰትን ማሳለጥና ፍትሐዊ አገልግሎትን ማስፈን ዋነኛ አላማ አድርጎ ተዘጋጅቷል ።

በዚህም መሠረት ቢሮው የወቅቱን ተለዋዋጭ ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች፣ የዲጂታላይዜሽን ፍላጎትና የልማት አጋሮችን ተዓማኒነት ከግምት ውስጥ ያስገባ ተቋሙን ከባህላዊ አሠራር ወደ ዘመናዊ መዋቅር የሚያሸጋግር ሁለንተናዊ የሪፎርም ፍኖተ ካርታ (Reform Roadmap) በቁርጠኝነት ቢሮ አዘጋጅቷል።

እነዚህም የአደረጃጀትና አስተዳደር ሥርዓትን ማሳለጥ፣ የሠራተኞች የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥርዓት መገንባት፣ ብዝኃነትንና አካታችነትን ማፋጠን፣ ነፃና ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ ግንባታን ማረጋገጥ፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት አሰጣጥን መዘርጋት፣ የዲጂታል አስተዳደር ሥርዓትን መገንባት እንዲሁም ገቢር ነበብ አመራርና ተቋም ግንባታን ማጠናከር ናቸው።

የዚህ የሪፎርም ፍኖተ ካርታ ዋነኛ መሣሪያና ትኩረትም ተቋማዊ አሠራሮችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ (Automation) መደገፍና ወረቀት አልባ አሠራርን በየደረጃው ማስፈን ነው።

ይህ የዝግጅት ምዕራፍ ዕቅድ፤ የሪፎርሙን አስፈላጊነት፣ ሊመዘገቡ የሚገባቸውን ዋና ዋና ውጤቶችና ግቦች እንዲሁም የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ በአሁኑ ወቅት የሚገኝበትን ነባራዊ ሁኔታ (የዳሰሳ ጥናት) በዝርዝር አካቷል።

በመጨረሻም የአብይና እና የቴክኒክ ኮሚቴዎች በቀረበው አፈጻጸም ላይ በመስጠት ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኃላ የቢሮ ኃላፊው ቀጣይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል ::

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮግንቦት 30/2018 ዓ.ም*          *         *          *           * በጄኔላ ወረዳ በማህበራዊ ተጠያቂነት ፕሮግራም የተለዩ የ...
07/06/2026

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ

ግንቦት 30/2018 ዓ.ም

* * * * *



በጄኔላ ወረዳ በማህበራዊ ተጠያቂነት ፕሮግራም የተለዩ የመንገድ ልማት ፍላጎቶችን በበጀት ለማካተት የሚያስችል የቴክኒክ ግምገማና የውይይት መድረክ ተካሄደ::


በሐረሪ ክልል በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የማህበራዊ ተጠያቂነት ፕሮግራም በሚተገበርባቸው የጄኔላ ወረዳ ቀበሌዎች በማህበረሰቡ የተለዩ የመንገድ ዘርፍ ቅድሚያ ጉዳዮችን በ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የባለሙያዎች የቴክኒክ ግምገማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።


በመድረኩ መጀመሪያ ላይ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የማህበራዊ ተጠያቂነት ተጠሪ (Focal Person) የሆኑት አቶ አዲብ መሐመድ ሰፊ ገለፃ አቅርበዋል።

አቶ አዲብ በማህበራዊ ተጠያቂነት ምንነት፣ ዋና መርሆዎች (ተሳትፎ፣ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ ምላሽ ሰጪነትና አካታችነት) እና በ3ቱ ቀበሌዎች (ቀበሌ 14፣ 15 እና 16) የተካሄደውን የመስክ ጉብኝትና የገጽ-ለገጽ ውይይት ውጤት አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በዚህም ማህበረሰቡ፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና ተጋላጭ ቡድኖች የመንገድ አገልግሎትን በተመለከተ ያላቸውን ችግሮችና ቅድሚያ ፍላጎቶች በነጻነት ያቀረቡበት ሂደት መሆኑን ገልጸዋል።


በመቀጠልም በባለሙያዎች የተደረገውን የቴክኒክ ግምገማና የውሳኔ ሃሳብ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፣ በ3ቱ ቀበሌዎች የተለዩ የ8 ማህበረሰብ ተኮር የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር በግምት ብር 89 ሚሊዮን በጀት እንደሚያስፈልግና የበጀት አስተያየቱ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።


በመድረኩ ላይ የተገኙት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ም/ቢሮ ሃላፊ አቶ ያህያ አብዱረሂም በሰጡት አስተያየት፤ ይህ ፕሮግራም አገልግሎት ሰጪውን እና አገልግሎት ተቀባዩን ማህበረሰብ በቅርበት የሚያቀራርብ፣ በመካከላቸው የጽኑ እምነት ድልድይ በመሆን ሀገርን የሚያሳድግ ታላቅ እምርታ መሆኑን አረጋግጠዋል።

አክለውም ለወረዳው አስፈላጊው ሙያዊ ድጋፍ ሁሉ እንደሚደረግ ገልጸው፣ ወረዳው የገቢ ምንጩን ከህብረተሰቡና ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር በማስተባበር የንቅናቄ ስራ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።


በትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በኩል የተገኙት የቢሮው ም/ኃላፊም በባለሙያዎች የቀረበውን የቴክኒክ አስተያየትና ጥናት ሙሉ በሙሉ በመቀበል፣ በቀጣይ የአቅማቸውን ያህል አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን በቁርጠኝነት ገልጸዋል።


በዚህ ከፍተኛ የውይይት መድረክ ላይ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ እንዲሁም የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አመራሮች ተሳትፈዋል።

በተጨማሪም የጄኔላ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ፣ የወረዳው ማህበራዊ ተጠያቂነት አስተባባሪና ሰብሳቢ (አፈ-ጉባኤ) የሦስቱ ቀበሌዎች መድረክ ሰብሳቢዎችና ጸሐፊዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በጋራ ተገኝተዋል።

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮግንባት 29/2018*          *         *          *           *የማህበራዊ ተጠያቂነት ፕሮግራም የ9 ወራት አፈፃፀም ግምገማ መድ...
06/06/2026

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ

ግንባት 29/2018

* * * * *

የማህበራዊ ተጠያቂነት ፕሮግራም የ9 ወራት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተካሄደ ::

በሐረሪ ክልል የማህበራዊ ተጠያቂነት ፕሮግራም በሚተገበርባቸው ጄኔላ፣ አቦከር፣ አሚር-ኑር እና ሶፊ ወረዳዎች የ2018 ዓ.ም የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ።

ከገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የማህበራዊ ተጠያቂነት ተጠሪ የሆኑት አቶ አዲብ መሐመድ ሰፊ ገለፃ አቅርበዋል።

አቶ አዲብ በገለፃቸው የማህበራዊ ተጠያቂነት ምንነትን፣ አሰራሩ ለማህበረሰቡ መሰረታዊ አገልግሎቶች ጥራት መሻሻል ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዲሁም ወረዳዎችና የአካባቢው አመራሮች ፕሮግራሙን በባለቤትነት በመምራት ረገድ ሊጫወቱት ስለሚገባው ስልታዊ ሚና በዝርዝር አስገንዝበዋል።

በመቀጠልም አራቱ ወረዳዎች (ጄኔላ፣ አቦከር፣ አሚር-ኑር እና ሶፊ) ባለፉት 9 ወራት ውስጥ ያከናወኗቸውን የማህበራዊ ተጠያቂነት ተግባራት፣ የተመዘገቡ ውጤቶችን፣ ያጋጠሟቸውን የአሰራር ተግዳሮቶች እና የነገ አቅጣጫዎቻቸውን በዝርዝር አቅረበው የጋራ ግምገማ ተደርጓል።

በቀረቡት ሪፖርቶችና በተደረገው ሰፊ ውይይት መሰረት በአራቱም ወረዳዎች የማህበራዊ ተጠያቂነት ፕሮግራም በጥሩ ጅምርና በተስፋ ሰጭ ደረጃ ላይ እየተተገበረ መሆኑ ተገልጿል።

ፕሮግራሙ በጥሩ ደረጃ ላይ ቢገኝም በአንዳንድ ዘርፎች ላይ የታዩ ክፍተቶች፣ ማሻሻያ እና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች በግልጽ ተለይተዋል።

እነዚህም በቀጣይ ጊዜያት በፍጥነት እንዲታረሙ ግልጽ አቅጣጫ ተቀምጧል በተለይም ማህበረሰቡን በቀጥታ በማሳተፍ የተለዩ የልማት ፍላጎቶችና ቅድሚያ የሚሰጣቸው ችግሮች በጋራ የማሻሻያ ዕቅድ ውስጥ ተካተዋል ::

ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች እና ከየወረዳዎቻቸው ጋር በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ የውል ስምምነት (ፊርማ) እንዲፈራረሙ እና ስምምነቱ እንደተጠናቀቀ በቀጥታ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲገቡ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

በዚህ ወሳኝ የገመገማ መድረክ ላይ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የወረዳ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች፣ የመድረክ አባላት፣ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎቹም የአሰራር ሂደቱን ይበልጥ ሊያሳድጉ የሚችሉ ገንቢ አስተያየቶችና ምክረ ሀሳቦችን በነጻነት አንስተዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ በተደጋጋሚ እንደተነሳው፡ ማህበራዊ ተጠያቂነት በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለውን ትብብርና እምነት በማጠናከር የዜጎችን ቀጥተኛ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ጥራት ለማሻሻል የሚያገለግል ወሳኝ የጋራ አሰራር ነው የሚለው ቁልፍ መልዕክት በመድረኩ ተላልፎ ተጠናቋል።


Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮግንባት 15/2018*          *         *          *           *የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለኤረር ወረዳና ለዲሬ-ጠያ...
23/05/2026

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ

ግንባት 15/2018

* * * * *

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለኤረር ወረዳና ለዲሬ-ጠያራ ወረዳ ትምህርተ ቤቶች መምህራን በትምህርተ ጥራት ፕሮግራም (ኢቶል)አተገባበር ግምገማ አከሄደ እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ::

ስልጠናው የትምህርት ቤቶች የድጎማ በጀት መመሪያ ላይ ለወረዳ ኦዲተሮች፣ለሱፐር ቫይዘሮች፣ለትምህርት አስተባባሪዎች፣ለፋይናንስ አስተባባሪዎች እንዲሁም ለርዕሰ ማስተዳደሮች ስልጠና ሰጠ::

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮግንባት 8/2018*          *         *          *           *የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለሰራተኞች ስለ ኤች.አይ.ቪ...
16/05/2026

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ

ግንባት 8/2018

* * * * *

የሀረሪ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለሰራተኞች ስለ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ::

* * * *

የሀረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ለሰራተኞች ስለ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከያ መንገዶችና ተያያዥ ጉዳዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።

የስልጠናው ዋና ዓላማ ሰራተኞች ስለ በሽታው ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እንዲጠብቁ፣ እንዲሁም በስራ ገበታቸው ላይ በሽታው ያለባቸውን ተገልጋዮችም ሆነ የስራ ባልደረቦቻቸውን ያለ ምንም መድልዎና መገለል እንዲያገለግሉ ለማስቻል ነው።

በመጨረሻም ሰራተኞቹ ይህ ግንዛቤና ስልጠናዎች መሰጠታቸው ለጤናቸው ጥንቃቄ እንዲያደርጉና በበሽታው ዙሪያ ያሉ የተሳሳቱ አመለካከቶችን ለማረም እንደሚረዳቸው ገልጸዋል።

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረሪ ሕዝብ ክልላዊ መንግስት ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮግንባት 3/2018 *          *        *          *        የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ በጄ...
11/05/2026

የሀረሪ ሕዝብ ክልላዊ መንግስት ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ

ግንባት 3/2018

* * * *


የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ በጄኔላ በሶፊ፣ በአሚር ኑርና በአቦከር ወረዳዎች ከሚገኙ የማብረተሰብ ተወካዮች፥ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አመራሮችና ጋር በማኅበራዊ ተጠያቂነት ዙሪያ የገፅ-ለገፅ የወይይት መድረክ አካሄደ።


በውይይቶቹ ላይ በጤና፣ በትምህርት፣ በመንገድ እና በውሃ አገልግሎት ዙሪያ የተለዩ ችግሮች ተነስተው የተወያዩ ሲሆን፥ በመድረኩም የተገኙት የሚመለከታቸው አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ ከወረዳና ከቀበሌ የማህበራዊ ተጠያቂነት መድረክ ሰብሳቢዎችና ፀሃፊዎች፣ ከማህበረሰብ ተወካዮች እና ከተቆጣጣሪ አካላት ጋር ገንቢ ውይይት ተካሂዷል።


የመድረኩ ዋና ዓላማ ማህበረሰቡን በውሳኔ ሂደት ውስጥ በንቃት ማሳተፍ፣ በመንግስታዊ አገልግሎቶች ውስጥ ግልፅነትና ተጠያቂነትን ማጠናከር፣ እንዲሁም ተቋማትና ማህበረሰቡ በጋራ ለችግሮች ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው።


በቀጣይም በውይይቶቹ የተለዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ችግሮች በጋራ የተግባር እቅድ (Joint Action Plan) ውስጥ ተካተው እንዲፈፀሙ ክትትልና ግምገማ ይካሄዳል።

በተጨማሪም ከህብረተሰቡ ጋር ተከታታይ የውይይት መድረኮችን በማካሄድ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና የህዝብ እምነትን ለማጠናከር በትኩረት ይሰራል።


Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮሚያዝያ 29/2018*        *         *          *የማህበራዊ ተጠያቂነት (SA) የመስክ ጉብኝት በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ! በኢትዮጵያ...
07/05/2026

የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ

ሚያዝያ 29/2018

* * * *

የማህበራዊ ተጠያቂነት (SA) የመስክ ጉብኝት በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ!


በኢትዮጵያ የማህበራዊ ተጠያቂነት (SA) ፕሮግራም ማዕቀፍ ውስጥ የማህበራዊ ተጠያቂነት አፈጻጸምን ለማጠናከር እና የምክር ቤት አባላት የቁጥጥር ሚናን ለማበረታታት በተዘጋጀ ቼክ ሊስት መሰረት፣ በወረዳ ደረጃ የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል።


የጉብኝቱ ዋና ትኩረት በወረዳዎችና በስሩ ላሉት ት/ቤቶች የማህበራዊ ተጠያቂነት ስራዎች አፈጻጸምን በተግባር መመልከት፣ ያሉ ችግሮችን መለየት እና ለቀጣይ ማሻሻያ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ላይ ነበር።


🎯 የጉብኝቱ ዋና ዓላማዎች:-

> የSA ተግባራት በወረዳ ደረጃ እንዴት
እየተፈጸሙ እንደሆነ ማረጋገጥ
> የምክር ቤት አባላት የቁጥጥር ሚናን
ማጠናከር
> ችግሮችን መለየት እና ተገቢ መፍትሄዎችን
ማቅረብ

👥 በጉብኝቱ የተሳተፉ አካላት

የበጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢና የማህበራዊ ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ እንዲሁም ከገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ናቸው ።


ጉብኝቱም የተካሄደው የመስክ ጉብኝት የማህበራዊ ተጠያቂነት ስርዓትን ለማጠናከር፣ ግልፅነትና ተጠያቂነትን ለማሳደግ እንዲሁም የህዝብ ተሳትፎን ለማበረታታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በመግለፅ በቀጣይም ሩብ አመት ጉብኝቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሰታቀውቀዋል።

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

03/05/2026
29/04/2026

*[በመካከለኛው ምስራቅ በተፈጠረው ቀውስ ምክንያት የዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት መቆራረጥ ጉዳዩ እስኪሰክን ዜጎች ምን ማድረግ ይችላሉ?]*

- ትክክለኛ የመረጃ ምንጮችን በመለየት፣ ሁኔታውን መረዳትና መንግስት ከጎናችሁ መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው።
- ከሀሰተኛ ወሬዎች እና ከተሳሳቱ መረጃዎች ራስዎን ይጠብቁ
- አጋጣሚውን በመጠቀም ለማትረፍ የሚሞክሩትን ያጋልጡ
- አሁን ያለውን የዓለም ተጨባጭ ሁኔታ በመገንዘብ በትዕግስት እና በጥንካሬ ለማለፍ ይሞክሩ
- አላስፈላጊ ጉዞዎችን በመቀነስ ነዳጅንና ሌሎች ውስን ሀብቶችን በጥንቃቄ ይጠቀሙ።

ምንም እንኳን ትልልቅ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች ቢኖሩብንም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የነዳጅ አቅርቦት እንዳይቋረጥና ዜጎችን ከእንግልት ለመከላከል አተኩሮ እየሰራ ነው።

በትብብር እና በትዕግስት ይህንን አስቸጋሪና ተለዋዋጭ የዓለም አቀፍ ሁኔታ፤ በጋራ ማለፍ እንችላለን!

🇪🇹

Address

Jinella
Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Finance & Economic Cooperation Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Harari Finance & Economic Cooperation Bureau:

Share