19/06/2026
ሰኔ 12፣2018 ዓ.ም(ጉንችሬ)
"ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት"!! በሚል መሪ ቃል የጉችሬ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት 7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ አፈጻጸም በተመለከተ የፐብሊክ ሰርቫንት የብልጽግና ፓርቲ ህብርት አባላት የውይይት መድርክ አካሄደ ።
የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ የውይይት መድረኩ በተካሄደበት ወቅት እንደገለጹት 7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በከተማው በስኬት እንዲጠናቀቅ አመራሩና አባሉ በቅንጅት መስራታቸውንና ህብረተሰቡም ጸሀይ፣ብርዱና ሰልፉ ሳይበግረው ድምፁን ዴሞክራሲን ለማፅናትና ሀገር መንግስት ለመገንባት ላሳየው የነቃ ተሳትፎ አመስግነዋል።
የመንግስት ሰራተኛው የብልጽግና ፓርቲ የህብረት አባላት በቅድመ ምርጫ የነበሩ ጥንካሬዎቹን በልማት ስራዎች ላይ በማስቀጠል ማህበረሰቡን በሁለንተናዊ ዘርፍ ተጠቃሚ ለማድርግ ከመቼውም ጊዜ በላይ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የከተማው የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሴ ደሴ እንደተናገሩት ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ታዓማኒነት ያለው ሆኖ መጠናቀቁንና ብልጽግና ፓርቲ የበላይነቱን መያዝ የቻለበት መሆኑን አብራርተዋል።
ፓርቲው ማህበረሰቡን በኢኮኖሚ ፣በማህበራዊና በፓለቲካው ዘርፉ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በማከናወኑና በቀጣይ ያለው ራዕይ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት እንዲያገኝ አስችሎታል ብለዋል።
የውይይት ተሳታፊ የፓርቲው የህብረት አባላት በሰጡት አስተያየት በምርጫው የተገኘው ድል በልማትና በመልካም አስተዳደር ተግባራቶች ላይ በትኩረት በመስራት ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
የከተማው መንግሰት ኮሚዩኒኬሽን ነው