ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Gunchire
  • ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት

ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት በከተማችን የሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች እናስተዋውቃለን!!

‎ሰኔ 12፣2018 ዓ.ም(ጉንችሬ)‎"ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት"!! በሚል መሪ ቃል የጉችሬ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት  7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ...
19/06/2026

‎ሰኔ 12፣2018 ዓ.ም(ጉንችሬ)
‎"ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት"!! በሚል መሪ ቃል የጉችሬ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት 7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ አፈጻጸም በተመለከተ የፐብሊክ ሰርቫንት የብልጽግና ፓርቲ ህብርት አባላት የውይይት መድርክ አካሄደ ።

‎የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ የውይይት መድረኩ በተካሄደበት ወቅት እንደገለጹት 7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በከተማው በስኬት እንዲጠናቀቅ አመራሩና አባሉ በቅንጅት መስራታቸውንና ህብረተሰቡም ጸሀይ፣ብርዱና ሰልፉ ሳይበግረው ድምፁን ዴሞክራሲን ለማፅናትና ሀገር መንግስት ለመገንባት ላሳየው የነቃ ተሳትፎ አመስግነዋል።

‎የመንግስት ሰራተኛው የብልጽግና ፓርቲ የህብረት አባላት በቅድመ ምርጫ የነበሩ ጥንካሬዎቹን በልማት ስራዎች ላይ በማስቀጠል ማህበረሰቡን በሁለንተናዊ ዘርፍ ተጠቃሚ ለማድርግ ከመቼውም ጊዜ በላይ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

‎የከተማው የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሴ ደሴ እንደተናገሩት ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ታዓማኒነት ያለው ሆኖ መጠናቀቁንና ብልጽግና ፓርቲ የበላይነቱን መያዝ የቻለበት መሆኑን አብራርተዋል።

‎ፓርቲው ማህበረሰቡን በኢኮኖሚ ፣በማህበራዊና በፓለቲካው ዘርፉ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በማከናወኑና በቀጣይ ያለው ራዕይ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት እንዲያገኝ አስችሎታል ብለዋል።

‎የውይይት ተሳታፊ የፓርቲው የህብረት አባላት በሰጡት አስተያየት በምርጫው የተገኘው ድል በልማትና በመልካም አስተዳደር ተግባራቶች ላይ በትኩረት በመስራት ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
‎‎የከተማው መንግሰት ኮሚዩኒኬሽን ነው

ሰኔ 12፣2018(ጉንችሬ)በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ።የከተማው ትምህርት ሃላፊ አቶ ሃቢብ ናስር :-የፈተና ሂደቱ...
19/06/2026

ሰኔ 12፣2018(ጉንችሬ)
በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ።

የከተማው ትምህርት ሃላፊ አቶ ሃቢብ ናስር :-የፈተና ሂደቱ በሠላም እንዲጠናቀቅ ከፍ ያለ ሚና የተወጡ የፀጥታ አካላት፣ አስፈተኝ መምህራን፣ የዞንና የክልል ደጋፊዎች፣ የከተማው ትምህርት አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁ ተማሪዎችና ሌሎች ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

#የከተማው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው!!

‎ሰኔ 12/2018ዓ.ም(ጉንችሬ) ‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ ለጉንችሬ ከተማ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ  1. 9 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት  ...
19/06/2026

‎ሰኔ 12/2018ዓ.ም(ጉንችሬ)
‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ ለጉንችሬ ከተማ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ 1. 9 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የጋርመንት ቴክኖሎጂ የስልጠና ማሽነሪዎች ድጋፍ ማድርጉ ተገለጸ።

‎ብቁና ተወዳዳሪ ዘመኑ የሚፈልገው የሰለጠነ የሰው ሀይል ለማፍራት የሚደርገውን ተግባር ለማሳካት የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ተጠቁሟል።

‎የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አ/ቋድር ሂጅራ ድጋፉን በተመለከቱበት ወቅት እንደገለጹት በተለያዩ የስልጠና ዘርፎች ብቁና የሰለጠነ የሰው ሀይል ለማፍራት ኮሌጁ እያደረገ ያለውን ስራ አጠናክሮ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ገልጸዋል።

‎ክልሉ ያደረገው ድጋፍ በጋርመንት ዘርፉ ለሰልጣኞች ተግባር ተኮር ትምህርት ለማስተማር ብቁና ተወዳዳሪ ዘመኑ የሚፈልገው የሰለጠነ የሰው ሀይል ለማፍራት የሚደርገውን ተግባር ለማሳካት የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ገለጸው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎የጉንችሬ ከተማ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ሙባረክ ሰፋ በበኩላቸው ተቋሙ የተለያዩ የአካባቢወን ማህበረሰብ ችግር የሚቀርፉ ቴክኖሎጂዎች በመፍጠር ለኢንተርፕራይዞች በማሸጋገር ዉጤታማ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

‎ዘመኑ ያፈራቸው ማሽኖችን በመጠቀም ብቁ የሆነ ስራ ፈጣሪ ዜጋ ለማፍራት አስፈላጊ መሆኑንና የተደረገው ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን 1. 9 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ለጋርመንት አገልግሎት የሚውሉ ማሽኖች መሆናቸውንና ለዚህም ምስጋናቸውን ገልጸው በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።

‎ዘገባው የከተማው መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው

https://youtu.be/amw_vMPaJ2I?si=JZqn-oaq-0_FPqoN #ሊንኩን በመጫን ሙሉ መረጃውን ይመልከቱ።
18/06/2026

https://youtu.be/amw_vMPaJ2I?si=JZqn-oaq-0_FPqoN

#ሊንኩን በመጫን ሙሉ መረጃውን ይመልከቱ።

ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለረጅም ዘመናት የህብረተሰቡ የልማት ጥያቄ የነበሩት በመመለስ...

‎በቀሩት ጥቂት የመኸር ጊዜያት ፈተናዎችን በመቋቋም ፍጥነትና ፈጠራን በማከል በግብርና ዘርፉ ውጤታማ ስራ መስራት ይጠበቅብናል፦አቶ አበራ ወንድሙ‎‎ሰኔ 11/2018(ጉንችሬ)‎‎የጉራጌ ዞን ም...
18/06/2026

‎በቀሩት ጥቂት የመኸር ጊዜያት ፈተናዎችን በመቋቋም ፍጥነትና ፈጠራን በማከል በግብርና ዘርፉ ውጤታማ ስራ መስራት ይጠበቅብናል፦አቶ አበራ ወንድሙ

‎ሰኔ 11/2018(ጉንችሬ)

‎የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በጉራጌ ዞን ቸሀ ወረዳ የመኸር ወቅት የግብርና ልማት ስራዎች ያሉበት ሁኔታ ተዟዙረው ተመልክተዋል።

‎ኃላፊ እንደገለፁት ግብርና ዋነኛው ከድህነት መውጫ መንገዳችን በመሆኑ በልዩ ትጋትና ቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

‎በዘንድሮ የመኸር ወቅት 177 ሺ 806 ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች ለመሸፍን ታቅዷል ያሉት አቶ አበራ እስካሁን በተሰሩ ስራዎች 135ሺ ሄክታር መሬት ማረስ መቻሉ አስታውቋል።

‎የአየር ሁኔታው እና የነዳጅ እጥረት በግብርና ስራው ላይ ተጽእኖ የፈጠሩ ቢሆንም እነዚህ ችግሮችን በመቋቋም ግብርናውን በስኬት እንዲጠናቀቅ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

‎በዞኑ ሁሉም አማራጮችን በመጠቀም የመኸር ስራው ሜካናይዝድ በሆነ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መደረጉንም አቶ አበራ ገልጸዋል።

‎የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቡና ፣በአትክልትና ፍራፍሬ፣በመኖ፣በእንስሳትና አሳ፣ በአረንጓዴ አሻራ ፣በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዘርፎች በተቀናጀ መልኩ የበለጠ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‎አቶ አበራ አክለውም በግብርና ዘርፉ የተያዙ 6ቱ የግብርና ምሶሶዎችን በአግባቡ በመተግበር የዞኑ የግብርና አቅምና ጸጋ አጉልተን ማውጣት ይጠበቃል ሲሉ ተናግረዋል።

‎የግብርና ዘርፉ የምግብ ዋስትናችንን ከማረጋገጥ ባሻገር ለዜጎች የስራ እድል የምንፈጥርበት ስለሆነ ግብርና ላይ ለአፍታም መዘናጋት አይገባም ብለዋል አቶ አበራ።

‎ድህነትን ያሸነፈና የቤተሰብ ብልጽግናን በተጨባጭ ያረጋገጠ ማህበረሰብ ለመፍጠር ግብርናን የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል ነው ያሉት።

‎በመሆኑም ያሉን የሰው ሀይል ጉልበት፣የደቦ፣የጌዝ እና የትራክተር አማራጮቻችንን አሟጠን መጠቀም ይገባል ብለዋል።

‎በተያዘው አመት 12 ሺ ሄክታር ያልታረሱ መሬቶች ማረስ ቢቻልም የበለጠ ግን መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል ።

‎በቀሩት ጠቂት የመኸር ወቅቶች ፈተናዎችን በመቋቋምና ፍጥነትና ፈጠራን በማከል በግብርና ዘርፉ ውጤታማ ስራ መስራት ይጠበቅብናል

‎ቸሀ ወረዳ በግብርና ዘርፉ ላይ በአፋጣኝ ወደ ስራ ተገብቶ የተሰሩ ስራዎች አበረታች መሆናቸው የተናገሩት አቶ አበራ በቀጣይም ማሳዎችን በኩታ ገጠም እና በሜካናይዜሽን የማረሱ ተግባር ይበልጥ እንዲጠናከር አሳስበዋል።

‎የቸሀ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጠቅልል አባድየ እንደገለፁት የመኸር እርሻ የተሳካ ለማድረግ እቅድ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን በመግለጽ ሜካናይዝድ በሆነ መልኩ በትራክተር፣ በበሬ እና በሰዉ ሀይል እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል።

‎የተለያዩ ሰብሎች በክላስተር ለማምረት 17ሺ 58 ሄ/ር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነ አመላክተዉ እስካሁን 11ሺ 715 ሄክታር መሬት መታረሱን እና ተግባሩ እየቀጠለ ይገኛል ብለዋል።

‎በወረዳዉ ምንም ዓይነት መሬት ሳይታረስ እንዳይቀር የወረዳ አስተዳደር ጨምሮ ተግባሩ የተሳካ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ ርብርብ እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት አቶ ጠቅልል።

‎በተለያዩ ቀበሌዎች በዛሬ ዕለት ከ24 በላይ ትራክተሮች እያረሱ እንደሚገኙ ጠቁመዉ የነዳጅ እጥረት እንዳይገጥማቸዉ እና አስፈላጊ ግብአቶች አሟልቶ ለማቅረብ ከዞን ግብርና መምሪያና ገበያ ልማት ከወረዳዉ ከሚመለከታቸዉ አካላት በቅንጅት እየተሰራ ነዉ ብለዋል።

‎በቸሃ ወረዳ የሚኖሩት አርሶ አደር መሀመድ አህመዲን እና አርሶ አደር አብድል ወሀብ ሳኒ ጤፍ፣ ገብስ፣ በቆሎ፣ ስንዴና ሌሎች ሰብሎችን በኩታ ገጠም በማምረት ለሌሎች አርሶ አደሮች ተምሳሌት ሆነዋል።

‎አርሶ አደሮቹ ከድህነት ለመውጣት ግብርናን አማራጭ የሌለው ሥራ በማድረግ ዘመናዊ የእርሻ አሰራሮችን በመተግበር ከፍተኛ ምርት እያገኙ መሆኑ ጠቅሰዋል።

‎ አክለውም በግብርናው ከቤተሰብ ፍጆታ ባለፈ ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ በማግኘት ኑሯቸውን እያሻሻሉ መሆኑን ገልጸዋል።

‎ለዚህ ስኬት የቸሃ ወረዳ መንግስት በግብርና ግብዓት አቅርቦት፣ በሙያ ድጋፍና በቅርብ ክትትል የሚያደርገው ድጋፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸው አርሶ አደሮቹም በቀጣይ የምርት መጠናቸውን የበለጠ ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
‎ዘገባው የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

‎የጉራጌ ማህበረሰብ ከጥንት ጀምሮ ለአረንጓዴ አሻራ ልማት ያለው ንቁ ተሳትፎ በማጠናከር የዞኑ የደን ሽፋን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት መም...
18/06/2026

‎የጉራጌ ማህበረሰብ ከጥንት ጀምሮ ለአረንጓዴ አሻራ ልማት ያለው ንቁ ተሳትፎ በማጠናከር የዞኑ የደን ሽፋን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት መምሪያ ገለፀ።

‎ሰኔ 11/2018(ጉንችሬ )

‎መምሪያው የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በተመለከተ ለሚዲያ መግለጫ ሰጥቷዋል።

‎በጉራጌ ዞን በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም 55 ነጥብ 5 ሚሊየን የደን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት መድረጉ ታውቋል።

‎ደን የሕይወት መሠረት ሲሆን አካባቢን፣ ኢኮኖሚንና የሰው ጤናን በብዙ መንገድ ይጠቅማል።

‎የጉራጌ ዞን ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ እንዳለ ስጦታው እንዳሉት ደን ለመዝናኛ ፣ለቱሪዝም ፣የአፈር መሸርሸርን በመከላከል፣ የአየር ንብረትን በማስተካከል እና በሌሎችም ዘርፎች ብዙ ጥቅም አለው።

‎በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም 55 ነጥብ 5 ሚሊየን የደን ችግኞች ለመትከል ዝግጅት መድረጉ ተናግረዋል።

‎የችግኝ ተከላ ስራው ውጤታማ ለመሆን ከግብርና መምሪያ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው በደን ልማትና በአግሮ ፎረስተሪ በአጠቃላይ ከ123 ሚሊየን በላይ የሚሆኑት ችግኞች እንደሚተከሉ አብራርተዋል።

‎እስካሁን 70 ነጥብ ነጥብ 5 ፐርሰንት የጉድጓድ ዝግጅት ተደርጓል ሲሉ አቶ እንዳለ አመላክቷል።

‎የሚተከሉ ችግኞች የአፈርና ውሃ ጥበቃ በሚያስጠብቅ መልኩ እና አግሮ ኢኮሎጂው በጠበቀ መልኩ እንደሚተከሉ አስገንዝበዋል።

‎ከዚህ በፊት የሚተከሉ ችግኞች በአግባቡ በመንከባከብ እና በመጠበቅ የዞኑ የደን ሽፋን አሁን ላይ 26 ነጥብ 6 ፐርሰንት ማሳደግ መቻሉ ተናግሯል አቶ እንዳለ።

‎የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሩ የተፈጥሮ ሃብትን ከመጠበቅ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያለመ መኾኑም ሃላፊው ጠቁመዋል።

‎በዞኑ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ባለፉት ዓመታት በየአመቱ 55 ነጥብ 5 ሚሊየን ችግኞች መተከላቸውንና ከዚህም ውስጥ 93 በመቶው መጽደቁን አቶ እንዳለ አስታውሰዋል።

‎ለችግኝ ተከላ ዝግጅት 2መቶ 28 ችግኝ ጣቢያዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልፀው፤ በዚህም ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ጠቁመዋል።

‎እጽዋቶቹ ከብዝሃ ሕይወት ሀብትነታቸው ባለፈ ለመድኃኒትነትና ለተለያዩ ግልጋሎቶች የሚውሉ መሆናቸውንና ካላቸው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አንጻር የጥበቃ ስራው ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል።

‎በዞኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በደን ዘርፍ ብቻ ከ16 ሺ 787 ሄክታር መሬት በላይ መሬት ተዘጋጅቷል ያሉት አቶ እንዳለ በዘንድሮ አመት በአንድ ጀንበር 245 ሄክታር መሬት በደን ይሸፈናል ብለዋል።

‎ለዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የደን፣የቀርከሃ፣የውበት ዛፎች፣የፍራፍሬ የቡናና ሌሎችም ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መዘጋጀታቸው የገለፁት ኃላፊው የተከላ ቦታዎችንና ተሳታፊዎች መለየቱንም አብራርተዋል።

‎በዚህም ማህበረሰቡ ወጣቶች የመንግስት ሰራተኞች የአካባቢው ተወላጆች፣የሀገር ሽማግሌዎች እና ምሁራን እንደሚሳተፉ አስታውቀዋል።

‎በየ አመቱ ከጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመላክተው በዚህም በተሰሩ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራዎች የተጎዱ መሬቶችን በማገገም አመርቂ ውጤቶች ተመዝግቧል ሲሉ ተናግረዋል።

‎የጉራጌ ማህበረሰብ ከጥንት ጀምሮ ለችግኝ ተከላ ያለው ንቁ ተሳትፎ እና እሴት በዞኑ በርካታ ደኖች እንዲፈጠሩ ማስቻላቸው አመላክተው ይህንን ለትውልድ ለማሸጋገር ሁሉም በችግኝ ተከላ ስራ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ አቶ እንዳለ ጥሪ አስተላልፏል።
‎ዘገባው የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው

‎ሰኔ 11/2018 ዓ.ም (ጉንችሬ) ‎ከጉንችሬ ከተማ  አስተዳደር ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት የተላለፈ መልእክት‎‎በዋናው በውኃው መስመር ብልሽት ምክንያት በከተማው ከቀን 12/2018 ጀምሮ ለተ...
18/06/2026

‎ሰኔ 11/2018 ዓ.ም (ጉንችሬ)
‎ከጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት የተላለፈ መልእክት

‎በዋናው በውኃው መስመር ብልሽት ምክንያት በከተማው ከቀን 12/2018 ጀምሮ ለተከታታይ 4ቀናት የውኃ አገልግሎት የሚቋረጥ ሲሆን የውኃ ደንበኞች ከወዲሁ አስፋላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አስታውቋል።

‎ችግሩ በመቅረፍ ባጠር ጊዜ አግልግሎት እንዲሰጥ የከተማ አስተዳደሩ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት በትኩረት እንደሚሰራና የውኃ አገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በሙሉ በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልእክቱን አስተላልፏል።

ሰኔ 11፣2018(ጉንችሬ)በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር 2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መስጠት ተጀመረ!!ፈተናው የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ እ...
18/06/2026

ሰኔ 11፣2018(ጉንችሬ)
በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር 2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መስጠት ተጀመረ!!

ፈተናው የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ እና የትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊው አቶ ሃቢብ ናስር እንዲሁ የክልልና የዞን ደጋፊ ባለሙያዎች ተገኝተው አስጀምረውታል።

#የጉንችሬ ከተማ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው!!

‎ሰኔ 10፣2018 ዓ.ም(ጉንችሬ)‎‎በቅድመ ምርጫ ወቅት በተሰሩ ስራዎች በምርጫው አመርቂ ወጤት ለማምጣት የጎላ ሚና እንደነበራቸውና በቀጣይም የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ...
17/06/2026

‎ሰኔ 10፣2018 ዓ.ም(ጉንችሬ)
‎‎በቅድመ ምርጫ ወቅት በተሰሩ ስራዎች በምርጫው አመርቂ ወጤት ለማምጣት የጎላ ሚና እንደነበራቸውና በቀጣይም የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራትን በትኩረት መሰራት እንደሚገባ ተገለፀ።

‎ይህ የተገለጸው ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት!! በሚል መሪ ቃል የጉችሬ ከተማ አስተዳደር አመራሮች የ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ አፈጻጸምና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በተመለከተ የውይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው።

‎የጉራጌ ዞን የመልካም አስተዳደርና አካባቢያዊ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ታሪኩ ንዳ ውይይቱ በተካሄደበት ወቅት እንደገለጹት የዞኑ ህብረተሰብ ሲጠይቃቸው የነበሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዳገኙና በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

‎ምርጫው ስኬታማና ውጤታማ እንዲሆን አመራሩና ማህበረሰቡ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነና ይህን ተግባር በልማት ስራዎች ላይ መድገም እንደሚገባ ገልፀዋል።


‎በቀጣይም በተቀናጁ የከተማ ግብርና ስራዎች ፣በፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ፣ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና፣በገቢ፣በስራ እድል ፈጠራ፣ በገበያ ማረጋጋት፣ የኮሪደር ልማትና ሌሎችም የተጀመሩ ስራዎችን በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

‎የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ በበኩላቸው ማህበረሰቡ የሰጠን ከፍተኛ የሆነ ኃላፊነት በቅንነትና በታማኝነት በመስራት የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ህብረተሰቡንም በማሳተፍ ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

‎ከምርጫ ማግስት የተጀመሩ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው አመራሩ በቅድመ ምርጫ ወቅት ሲያደርገው የነበረውን ተግባር ቀልጣፋ የሆነ አገልግሎት በመስጠትና በልማት ስራዎች ላይ ማሳየት እንዳለበት ገልጸዋል።

‎ሚዲያው ህዝብና መንግስት በማገናኘት የህብረተሰቡን ሰላም አንድነት የሚያጎለብቱ ስራዎችና መስራት እንደሚገባና የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎችን ማጋለጥ ያስፈልጋል ብለዋል

‎በመድረኩም የከተማው የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሴ ደሴን ጨምሮ ሌሎችም የከተማው አመራሮች ተሳትፈዋል።

ሴኔ 10፣2018(ጉንችሬ)በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈተኞች ኦሮንቴሽን ተሰጠ።ተፈታኞች በፈተና ስነስርዓትና ደንብ፣ በመረጃ አሞላል፣በሰአት አጠቃቀምና በስነል...
17/06/2026

ሴኔ 10፣2018(ጉንችሬ)
በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈተኞች ኦሮንቴሽን ተሰጠ።

ተፈታኞች በፈተና ስነስርዓትና ደንብ፣ በመረጃ አሞላል፣በሰአት አጠቃቀምና በስነልቦና ረገድ በቂ ዝግጅት እንዲኖራቸው፣ ቅድመ ፈተና ገለጻ ተደርጎላቸዋል።

ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በሚጀምረው ፈተና በጉንችሬ ሃይስኩል እና ቆጭራ አንደኛ ትምህርት ቤት የሚሰጥ ይሆናል።
በዘንድሮ ከ8ኛ ክፍል ወንድ 103 እና 154 ሴት በጠቅላላው 257 ተፈታኞች ክልል አቀፍ ፈተናውን የሚወስዱ ይሆናል።

#የከተማው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው!!

Address

Gunchire

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share