22/05/2026
በአዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ወንዶች ብቻ የተሳተፉበት የሻይ ቡና ውይይት እና የማኑፌስቶ ትውውቅ መርሐግብር ተካሄደ።
ጠንካራ ሀገር መንግስት ለመገንባት የመሪዎች ሚና ወሳኝ በመሆኑ ህዝቡ ሀገርን ወደ የተሻለ ደረጃ ለማሻገር ለሀገራዊ ምርጫ ዕጩነት ለቀረቡት አባላት ትኩረት በመስጠት ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ትኩረት መስጠት እንዳለበት ተገልጿል።
ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገርነት ለማሸጋገር በሚደረገው ጉዞ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ ምርጫ ማካሄድ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ምርጫው ቅቡልነት ፍትሐዊና አካታች እንዲሆን ሁሉም ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚገባው ተመላክቷል።
በሻይ ቡና ውይይቱ የብልፅግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ያዘጋጀውን ማኑፌስቶ እና የስንዴ ነዶ የምርጫ ምልክት ይፋ የማድረግ መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን ምርጫችን ሀገርን አፅንቶ የሚያስቀጥል መሆኑን በመርሐግብሩ ተጠቁሟል።
!!
!!
!!