ሰሜን ጎንደር ቴክኒክና ሙያ ኢንተርፕራይዝ ልማት

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • ሰሜን ጎንደር ቴክኒክና ሙያ ኢንተርፕራይዝ ልማት

ሰሜን ጎንደር ቴክኒክና ሙያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ሰፊ የሥራ ዕድ በመፍጠር ቀጣይነት ያለው ፈጣን ልማት ማምጣት

02/12/2017

የፌዴራሊዝም ስርዓት ብዙህነትን በብቃት ለመስተናገድ በርካታ ዕድሎችን የሚከፍት የመንግስት ስርዓት በመሆኑ ባለፉት ሁለት ክፍለ ዘመናት በሁሉም የዓለም ክፍሎች የሚከተሉት ሀገራት ቁጥር እየጨመረ ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያም የፌዴራል ስርዓት በተከተለችባቸው ዓመታት በርካታ ፖለቲካዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ድሎችን አስመዝግባለች፡፡ የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ያለሙትን አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ የመገንባት ራዕይ እውን ለማድረግና ዘላቂ ሰላምና ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ለማስቻል የፌዴራሊዝም ስርዓቱ ቁልፍ መሳሪያችን ነው፡፡
ስርዓቱም መላው ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች በመቻቻል በመከባበርና በአንድነት ለመኖር ያስቻላቸው በመሆኑ ዘብ ሆነው ይጠብቁታል፡፡

02/11/2017

የተፋጠነ ልማትን ለማረጋገጥ፤ ፍትህና መልካም አስረዳደርን ለማስፈን ለህብረተሰቡ የቅርብ አመራር መስጠት እንደሚያስፈልግ ይታወቃል፡፡ በዚህ መሰረት ሰፊ የቆዳ ስፋት የነበረውና የህዝብ ቁጥሩም በዛው ልክ ከፍተኛ የሆነው የሰሜን ጎንደር ዞን በአንድ የአስተዳደር ማዕከል የሚሰጠው አመራር የሚጠበቀውን ፈጣን ልማት ማረጋገጥና ህዝቡ በየአካባቢው ለሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እንቅፋት በመሆኑ ሰሜን፤ ምዕራብና ማዕከላዊ በሚባሉ ስያሜዎች በቅርቡ ከሶስት ተከፍሏል፡፡
የኪራይ ሰብሳቢ ሀይሎችና የአካባቢውን ልማትና ጸጥታ የማይወዱ ወገኖች ይህን ለተሻለ ልማትና ዕድገት ተብሎ የተፈጠረውን አዲስ የዞን አደረጃጀት በራሳቸው የጥፋት መነጽር በማየት ህዝቡን ለማደናገር እየተንቀቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ በመሰረቱ በየትኛውም ሀገር የአካባቢ አስተዳደር መስፋትና መጥበብ ያለና ሊኖር የሚችል ጉዳይ ነው፡፡ መንግስት የመረጠውን ህዝብ ለማገልገልና የልማት ፍላጎቱን ለማሳካት የሚያስችሉትን ልዩ ልዩ የአካባቢ አስተዳደሮች በህዝቡ እውቅና እና ፈቃደኝነት ተመስርቶ ይፈጥራል፡፡ ከየአካባው ተጨባጭ ሁኔታ አኳያ እነዚህ የመጥበብ የመስፋት፤ የመከፈልና የመዋሃድ ጉዳዮች ተፈጥሯዊ ናቸው፡፡ ምንም አዲስ ነገር የለውም፡፡ በኛ ዞን ነባራዊ ሁኔታም የቀበሌዎችና የወረዳዎች ውህደትና ከፈሎ በየትኛውም አካባቢ ከየወቅቱ የልማት አጀንዳ አኳያ እየተመዘነ ሲካሄድ የነበረ ነው፡፡ ምናልባት አዲስ ነገር ሚሆነው አሁን የተካሄደው የዞን ከፈሎ መሆኑ ብቻ ነው፡፡ ይህ አዲስ የዞን አደረጃጀትም የየአካባውን የልማት ጸጋ እና እንቅፋቶች መሰረት አድርጎ የተካሄደ ነው፡፡ ለምሳሌ የምዕራቡ አካባቢ ማለትም መተማ ቋራና አርማጭሆ በውስጣቸው የሚካተቱ የከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በሰሊጥና በጥጥ እንዲሁም በእጣን ምርት የታወቁ፤ ከፍተኛ የንግድና አገልግሎቶች እንቅስቃሲዎች የሚካሄድባቸው አካባቢዎች ናቸው፡፡ ይህ እንደ አንድ የልማት ኮሪደር የሚወሰድ አካባቢ ሲሆን በተለይ የግብርና ምርችቶን የሚያቀነባብሩ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በስፋት እንዲመሰረቱ በማድረግ የግብርናውንና የኢንዱስርቲውን ዕድገት ለማፋጠን የሚያስችል ከመሆኑም በተጨማሪ ሰፊ የሥራ ዕድል ሊፈጠርባቸው የሚችል አካባቢ ነው፡፡ እነዚህን ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተከትለው ሰፋፊ የንግድና አገልግሎት መስጫ ተቋማትም እየተስፋፉ ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ትላልቅ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዲስትሪዎች የሚገኙ ሲሆን በዋነኛነት ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርች ይመረቱባቸውል፡፡ ታዲያ ይህን ያህል ትልቅ የመልማት ዕድል ያለውን አካባቢ በቅርበት የሚከታተል ፤ ችግሮቹን እየለየ የሚፈታና፤ የካባቢውን ልማት የሚያፋጥን የቅርብ አስተዳደር መፈጠሩ ሃጢያቱ ምን ይሆን?
አሁንም አዲሱ የዞን አደረጃጀት በየአካባቢው ያለውን የልማት የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመለየት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ገብቷል፡፡ ልማትን በማፋጠን አካባቢው በመሰረተ ልማት እንዲተሳሰር፤ ማህበራዊ ልማት እንዲስፋፋ ሰፊ ስራ ለመስራት በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ ይህ ጥረት ተጠናክሮ ሲቀጥልና አካባቢያችን በልማት ዕድገት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሲደርስ ኢኮኖሚያዊ ትስስሩ ይበልጥ ይጎለብታል፡፡ በኢኮኖሚያዊ የተሳሰረ ህዝብ ደግሞ ይበልጥ አንድነቱ ይጠናከራል፡፡ አንድነትን የሚያላው ድህነት ብቻ ነው፡፡ ልማቱ ሲፋጠንና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ ይበልጥ ሲረጋገጥ ከዚህ የበለጠ ትስስር የትም አይገኝም፡፡
በመሆኑም ጸረ ህዝብ ኃይሎች የተምታታ አጀንዳቸውን ዋጋ አልባ ለማድረግ አሁንም የልማት ስራችን ላይ ማተኮር አለብን፡፡ ህዝባችን ልማት ወዳድ ነው፡፡ በጥፋተኞች አጀንዳ ሳይዘናጋ አካባቢውን በንቃት ማልማት ይኖርበታል፡፡ ለዚህ ደግሞ ይበልጥ ወደ ህዝቡ ቅርብ ሆነው የተደራጁ ዞናዊ መዋቅሮች ለህዝቡ ሙያዊ ምክርና አገልግሎት መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከድህነት የከፋ ጠላት የለንምና ሌት ተቀን ተረባርበን ድህነትን ማስወገድ ይጠበቅብናል፡፡ ያኔ ጎንደር በልማት ወደ ኃላ ቀረች እያሉ ሲያላዝኑ የነበሩት አሁን ደግሞ ልማቱን ይበልጥ ለማፋጠን አዲስ አደረጃጀት ሲፈጠር በልማት ወደ ኋላ ቀረ የሚለውን አጀንዳቸውን ቀይረው ጎንደር ተከፋፈለች ወደሚል ሟርት ፊታቸውን አዙረዋል፡፡ እነሱ ከልማት ምንም የሚጠብቁት ትርፍ የለም፡፡ ትርቸፋውን የሚያገኙት ከጥፋትና ብጥብጥ ነው፡፡ እኛ ህዝባቸንን በተፋጠነ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ሩጫ ላይ ነን፡፡ እነሱን የሚሰማ ጆሮ የለንም፡፡ ውሾቹ ይጮሃሉ ግመሉ ግን ጉዞውን ቀጥሏል፡፡

17/10/2017

የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በገበያ ተወዳሪ መሆን የሚችሉት ጥራት ያለው ምርት ማምረት ሲችሉና ምርታማ ሲሆኑ ነው፡፡ ምርታማነትም ሆነ የምርት ጥራት የሚረጋገጠው በቂ ክህሎትና የቴክኖሎጅ አጠቃቀም አቅም ሲዳብር ብቻ ነው፡፡ የኢንተርፕራይዞቻችን አንቀሳቃሾች በተሰማሩበት ስራ የተሟላ ክህሎት ስለሚጎድላቸው የምርት ጥራታቸው አሳሳቢ ደረጃ ለይ ይገኛል፡፡ ገበያን በአግባብ የመቆጣጠር ችግርም አለባቸው፡፡ በስራው የሚሰማሩ ወጣቶችም ዘርፉን የመቆያ እንጅ የዘላቂ ለውጥ መነሻ አድርገው አይወስዱትም፡፡፡ክህሎታቸውን ለማሳደግ የሚሰጡት ትኩረት በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡
እነዚህና ሌሎች መሰል ችግሮች የሚቀረፉት ለኢንተርፕራይዞቻችን ተከታታይ የኢንዱስትሪ አገልግሎት በመስጠት ነው፡፡ በመሰረቱ የኢንዱስትሪ አገልግሎት ዋነኛው ዓላማ ኢንተርፕራይዞቻችን በሚያመርቱት የምርት ጥራና በዋጋ በገበያ ተወዳዳሪና አትራፊ እንዲሆኑ ማስቻል ነው፡፡ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አራት የድጋፍ ማዕቀፎች ያሉት ሲሆን የሂሳብ መዝገብ አያያዝ፤ የቴክካል ክህሎት አቅም ግንባታ፤ የካይዘን ( የምርታማነት ስራ አመራር) እንዲሁም የቴክኖሎጅ አቅርቦት ናቸው፡፡ የተጠቀሱትን የድጋፍ ማዕቀፎች በዕድገት ተኮር የሥራ መስኮች ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች በመስጠት ኢንተርፕራይዞቹ ወደ ቀጣዩ የእድገት ደረጃቸው የሚያደርትን በማሳካት ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ለሚደረገው መዋቅራዊ ሽግግር ያላቸውን የማይተካ ሚና እንዲወጡ ማድረግ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው፡፡
በሰሜን ጎንደር ዞን በ2009 በጀት ዓመት ያለባቸውን ክፍተትና የዕድገት ደረጃ መሰረት በማድረግ ለ4419 ነባር ኢንተርፕርይዞች የተሟላ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ለመስጠታ ታቅዶ ለ 4085 ያህሉ(92.4%) ያህል የሟላ ድጋፍ በመስጠት በገበያ ተወዳሪና ትርማ እንዲሆኑ ለማድረግ ሰፊ እንቅስቃሴ ተደርጓል፡፡ በያዝነው በጀት ዓመትም ይህ ስራ በልዩ ትኩረት ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን በሞዴል ኢንተርፕራይዞች አማካኝነት ለሁሉም በዕድገት ተኮር መስክ ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞቻችን ጥራት ያለው፤ የተቀናጀ እና ሁለንተናዊ የኢንዳስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመስጠት የዞናችንን እድገት ለማፋጠን ጠንክረን እንሰራለን፡፡

07/10/2017

Address

Gondar
Gondar
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰሜን ጎንደር ቴክኒክና ሙያ ኢንተርፕራይዝ ልማት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share