ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ኦፊስ

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ኦፊስ

ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ኦፊስ ምዕ/ጎንደር ዞን ምዕ/አርማጭሆ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

በገንዳውሃ ከተማ ቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠየትምህርት መሠረተ ልማትን ለማጠናከርና ለተማሪዎች የተሻለ የመማሪያ አካባቢ ለመፍጠር በተያዘው እቅድ መሰረ...
06/06/2026

በገንዳውሃ ከተማ ቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

የትምህርት መሠረተ ልማትን ለማጠናከርና ለተማሪዎች የተሻለ የመማሪያ አካባቢ ለመፍጠር በተያዘው እቅድ መሰረት በገንዳውሃ ከተማ ቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አዲስ የትምህርት ቤት ግንባታ የመሰረት ድንጋይ በይፋ ተቀምጧል።

በመሰረት ድንጋዩ ማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት ላይ የገንዳውሃ ከተማ ዋና ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም ሙሃመድ፣ የገንዳውሃ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ አስማረች ቆያቸው፣ የምዕራብ ጎንደር ዞን ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ይግለጥ አበባው፣የገንዳውሃ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በየነ አዳነ እንዲሁም ሌሎች የመንግስት ኃላፊዎች፣ የህብረተሰብ ተወካዮች፣ መምህራንና ወላጆች ተገኝተዋል።

በፕሮግራሙ ንግግር ያደረጉት የገንዳውሃ ከተማ ዋና ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም ሙሃመድ፣ ትምህርት የማንኛውም ማህበረሰብ እድገት መሰረት መሆኑን ገልፀው የዛሬው ፕሮጀክት የከተማዋን የትምህርት አገልግሎት ለማሳደግና በተለይም የተማሪዎችን የመማር ሁኔታ ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቅ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የገንዳውሃ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ አስማረች ቆያቸው በበኩላቸው፣ በሰው ሀብት ልማት ውስጥ ትምህርት ያለውን ወሳኝ ሚና በማንሳት የትምህርት ቤቱ ግንባታ የተማሪዎችን የመማሪያ አቅም ከማሳደግ ባለፈ ለአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ህብረተሰቡም የፕሮጀክቱን ስኬት ለማረጋገጥ በትብብር እንዲሰራ አሳስበዋል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ይግለጥ አበባው በበኩላቸው፣ ፕሮጀክቱ በዘመናዊ የግንባታ ደረጃዎች መሰረት እንደሚገነባ ገልፀው ለተማሪዎች ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የመማሪያ አካባቢ ለመፍጠር ትኩረት እንደተሰጠው ጠቁመዋል። የግንባታ ሂደቱም በቅርበት እንደሚከታተል አስረድተዋል ።

ተሳታፊዎችም የትምህርት ቤቱ ግንባታ ለከተማው እና ለተማሪዎች ትልቅ እፎይታ እንደሚያመጣ ገልጸው ፕሮጀክቱ በፍጥነትና በጥራት እንዲጠናቀቅ ያላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

የመሰረት ድንጋዩ መቀመጥ በገንዳውሃ ከተማ የትምህርት መሠረተ ልማትን ለማስፋፋት እየተደረጉ ካሉ ጥረቶች አንዱ ሲሆን ትውልድን በእውቀት ለማብቃት እና የአካባቢውን ልማት ለማፋጠን የሚያግዝ ጠቃሚ ፕሮጀክት መሆኑ ተጠቅሷል።

የገንዳውሃ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን፡፡

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ገለጉ ቀበሌ  በበጋ መስኖ  እየለማ ያለ የበቆሎ ሰብል በከፊል!!(ግንቦት፦27/2018 ዓ.ም)
04/06/2026

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ገለጉ ቀበሌ በበጋ መስኖ እየለማ ያለ የበቆሎ ሰብል በከፊል!!

(ግንቦት፦27/2018 ዓ.ም)

የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ  የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ተግባራት አፈፃፀምን  ገመገመ። በምዕሬብ ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በማስመልከት የማጠቃለያ ግ...
04/06/2026

የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ተግባራት አፈፃፀምን ገመገመ።

በምዕሬብ ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በማስመልከት የማጠቃለያ ግምገማ እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከጠቅላለላ አመራሩ ጋር ውይይት ውይይት ተካሂዷል።

በግምገማው በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ወቅት እና በድህረ ምርጫ ወቅት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት የነበሩ ጠንካራ ጎኖች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም የተወሰዱ መፍትሔዎች ዙሪያ ግምገማ ተደርጓል።

የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ እሸቱ ስመኘው በክልሉ ብሎም በወረዳችን ምርጫ እንዳይካሄድ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠረት እና ህዝቡ ይመራኛል ብሎ የሚያምንበትን መንግስት እንዳይመርጥ ብሎም ሀገር ሰላም እንድትሆን የማይፈልጉ ፀረ ሰላም ሀይሎች ያደረጉት ጥረት የከሸፈበት የህዝብ አስተዋይነት የታየበት ምርጫ ነበር ብለዋል።

ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ምርጫው ዕለት ድረስ ምርጫው ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ላደረጉ የጸጥታ ኃይሎች እና በየደረጃው ለሚገኙ አስፈፃሚ አካላት ዋና አስተዳዳሪው ምስጋና አቅርበዋል።

የወረዳው ማህበረሰብ በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ ድምፅ በመስጠት ምርጫው ፍትሀዊ እና አሳታፊ መሆኑን ያሳየበት ተግባር መሆኑን የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ታከለ አውደው ገልፀዋል።

ህዝቡ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የህዝቡን ጥያቄና ችግር ለመፍታት በቀጣይ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የልማት ስራዎችን ለማስቀጠል እጅ እና ጓንት ሁነን መስራት ከሁላችን የሚጠበቅ ህዝብ የጣለብን አደራ ነው ሲሉ አቶ ታከለ ገልፀዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጋሻው ስዩም እንደገለፁት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደቱ ምንም ዓይነት የጸጥታ ችግር ሳይገጥመን በሰላም መጠናቀቅ የቻለው በህዝቡ ንቁ ተሳትፎ እና በጸጥታ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር መሆኑን አብራርተው በተለይም ማህበረሰቡ የምርጫውን ሂደት በባለቤትነት ስሜት በመጠበቅና ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ላሳየው ብስለት ምስጋና አቅርበዋል።

በቅደመ ምርጫ ወቅት ህዝቡ በቀጣይ አምስት አመት ይመረኛል ያስተዳድረኛል የሚለውን መንግስት እንዲመርጥ በአደረጃጀት የተሰራው የግንዛቤ ፈጠራ ስራ ምርጫው ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጉን ገልፀዋል።

ህዝቡ ያለምንም መንገላታት እና ችግር በሰላማዊ መንገድ እንዲመርጥና እንዲጠናቀቅ ላደረጉ የምርጫ አስፈፃሚዎች፣ ታዛቢዎች እና የፀጥታ መዋቅሩ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።

ህዝቡ ምርጫው በሰላም እንጠናቀቅ ያሳየውን እርብርብ አጠናክሮ በማስቀጠል ወደልማት ተግባራችን መግባት አለብን ሲሉ የመድረኩ ተሳታፊዎች አብራርተዋል።

የተገኘውን ሰላምና መረጋጋት ዘላቂ ለማድረግና በቀጣይ የልማትና የሰላም ስራዎችን ለመስራት እና ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

አብርሃጅራ:- ግንቦት 27/2018 የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: https://www.facebook.com/share/1CsG1K8GAR/
Telegrams :https://t.me/+xuUwI1oZM-I2M2U8
youtube:https://youtube.com/?si=9zUtvoNNNSOblOik

በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ በሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም የ10 ወር የፈፃሚ ተቋማት የስራ አፈፃፀም እና የቴክኒክ እና አብይ ኮሚቴ የመስክ ምልከታ ግምገማ አካሄደ። አብርሃጅራ :- ግንቦት 27/2...
04/06/2026

በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ በሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም የ10 ወር የፈፃሚ ተቋማት የስራ አፈፃፀም እና የቴክኒክ እና አብይ ኮሚቴ የመስክ ምልከታ ግምገማ አካሄደ።

አብርሃጅራ :- ግንቦት 27/2018 ዓ.ም በምዕራብ ጎንደር ዞን የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የ10 ወር የፈፃሚ ተቋማት የስራ አፈፃፀም አብይ ኮሚቴው እና የቴክኒክ ኮሚቴው በተገኘበት በምግብ እና ስርዓተ ምግብ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን ገምግሟል።

የወረዳው የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ሞገስ መላክ የሁሉንም የፈፃሚ ተቋማት በምግብና ስርዓተ ምግብ ማሻሻል በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የተከናወኑ የአስር ወራት የተግባራትን አፈፃፀም ሪፖርት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

ፕሮግራሙ በነፍሰጡር እናቶች እና ከ2 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትን በስርዓተ ምግብ እጥረት ሊከሰት የሚችሉትን ችግሮች ለመቅረፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።

በግምገማው ፕሮግራሙ በልጆች እና በእናቶች የአመጋገብ ስርዓት ላይ ትኩረቱን አድርጎ እንደሚሰራ የገለፁት አቶ ሞገስ ህፃናትን ከመቀንጨር እና መቀጨጭ ለመከላከል በጤና፣ በግብርና፣ በትምህርት እንዲሁም የንፁህ መጠጥ ዉሃን ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን በመስራት የነገ ሀገር ተረካቢ በአካላዊ እና አዕምሮው የዳበረ ትውልድ ለመቅረፅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመቀናጀት ትኩረት ሰጥተዉ መስራት እንዳለባቸዉ ገልፀዋል ።

ሌላው በግምገማው የተገኙት የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የወረዳው ንግድ ገበያ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አሰማርቶ አላምረው እንደገለፁት የበለፀጉ ምግቦችን በስፋት በማምረት እና በማልማት በስርዓተ ምግብ እጥረት የሚፈጠሩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ተጨባጭ ለውጥ በማሳየት በወረዳው ንቁ እና ቀልጣፍ ዜጋ ለማፍራት በፕሮግራሙ የታቀፉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል።

አቶ አሰማርቶ አክለውም በፕሮግራሙ የታዩ ለውጦችን በማጠናከር የህፃናት የምግብ እጥረትን ለመቀነስ የተመረጡ ጽ/ቤቶችና ኮሚቴዎች በቅንጅት ወደታችኛው መዋቅር በመውረድ በወረዳችን የህፃናትን መቀጨጭ እና መቀንጨርን ዜሮ ለማድረግ በተመረጡ ቀበሌዎች ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ሁሉም ተቋማት ባለፉት ወራት የታዩ ጥንካሬዎችን ይበልጥ በማጠናከር ድክመቶችን ደግሞ በማሻሻል ቀሪ ተግባራትን በጊዜ የለኝም መንፈስ በመስራት የህፃናትን እና የእናቶችን ተጠቃሚነት ልናረጋግጥ ይገባል ብለዋል።

ፕሮግራሙ የማህበረሰቡን የምግብና ስርዓተ ምግብ አጠቃቀም በማሻሻል የህፃናትን አካላዊና አዕምሮዓዊ መቀንጨር በመቀነስ ብሎም በማጥፋት የተሻለ አምራች ዜጋ ለመፍጠር ትኩረት ሠጥቶ እየተሠራ መሆኑን የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ስጦታው አዱኛ ገልፀዋል።

ጤናማ እና አምራች ትዉልድ መገንባት የሚቻለዉ ስርዓተ ምግብ ላይ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ሲቻል ነው ያሉት አቶ ስጦታው በቀጣይ ሁሉም የሚመለከታቸው ተቋማትና ባለሙያዎች እኔ ይመለከተኛል የሚል ስሜት በመሰነቅ የትውልድ ግንባታ ላይ መስራት አለብን ብለዋል።

መቀንጨርና መቀጨጭ በህፃናት አዕምሮ እና አካል ሊያስከትል የሚችለዉን ችግር ለመቅረፍ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የገለፁት አቶ ስጦታው ተግባራትን ተቀናጅቶ በመፈፀም መቀንጨር በህብረተሰቡ ዘንድ ሊያስከትል የሚችለዉን ችግር ለመቅረፍ መሰራት አለበት ብለዋል።

በመጨረሻም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ግምገማው ተጠናቋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: https://www.facebook.com/share/1CsG1K8GAR/
Telegrams :https://t.me/+xuUwI1oZM-I2M2U8
youtube:https://youtube.com/?si=9zUtvoNNNSOblOik

"በዞኑ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መከናወኑ፤ በቀጣዩ ምዕራፍ ሙሉ በሙሉ ወደ ሰላምና ልማት በማተኮር፣ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በማጠናከር የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ላይ ያተኩራል።"...
03/06/2026

"በዞኑ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መከናወኑ፤ በቀጣዩ ምዕራፍ ሙሉ በሙሉ ወደ ሰላምና ልማት በማተኮር፣ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በማጠናከር የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ላይ ያተኩራል።" የዞኑ አስተዳደር

​ገንዳ ውኃ፣ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም ​የክልልና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በማስመልከት የማጠቃለያ ግምገማና በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

በዚሁ የግምገማ መድረክ ላይ በቅድመ-ምርጫ፣ በምርጫ ወቅት እና በድህረ-ምርጫ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በጥልቀት ተገምግመዋል።

​በማጠቃለያ ግምገማው ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የአስተዳደር ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጥላሁን መኳንንት፤ በክልልም ሆነ እንደ ሀገርና ዞን ለሚለማው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ዕውን መሆን በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ ድምፅ ለሰጡ ዜጎች ምስጋና ሰጥተዋል።

በየደረጃው ያለው የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ሕዝቡ ድምፅ ከመስጠት ባለፈ የምርጫ ቁሶችን ደኅንነት በባለቤትነት በማስጠበቅ ድጋፍ በማድረግ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው አስተዋጽኦ ጭምር ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ ባስተላለፊት መልዕክት፤ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በዞኑ ያለምንም የጸጥታ ችግር፣ በሰላማዊ እና በዴሞክራሲያዊ መንገድ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላበረከቱት ባለድረሻ አካላት የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በዞኑ 6 ተፎካካሪ ፓርቲዎች መሳተፋቸውን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው፤ ሕዝቡ ለሚፈልገው ፓርቲ ድምፁን በሰላማዊ መንገድ መስጠቱን ገልጸዋል።

ይህም ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ትልቅ አሳታፊ ተግባር መሆኑን አስገንዝበዋል።

በቀጣዩ ምዕራፍ በዞኑ ሙሉ በሙሉ ወደ ሰላምና ልማት በማተኮር፣ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በማጠናከር የህዝቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሰላማን ለማፅናት ትልቅ አደራ አለብን ብለዋል።

በዞኑ የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የሞት ሽረት ርብርብ በማድረግ፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንዳለው ማሩ፤ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ምርጫው ዕለት ድረስ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሥራ ኃላፊዎች፣ ለፀጥታ አካላትና ለመላው የዞኑ ሕዝብ ምስጋና አቅርበዋል።

በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የታየውን ሕዝባዊ አንድነት በድህረ ምርጫውም ሂደት ላይ በሚከናወኑ ጉዳዮችና በቀጣይ በማስቀጠል፣ሰላምና ልማትን ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።

ተሳታፊ የሥራ ኃላፊዎችና አመራሮች በበኩላቸው፤ ይህ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ውስብስብ የዴሞክራሲ ሂደቶችን በሰላም መምራት እንደምትችል ለዓለም ያሳየችበት ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን ገልፀዋል።

በቀጣይ ወደ ሰላምና መሰረተ ልማት ግንባታዎች በማዞር የሕዝባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተጋት እንሰራለን።

በ​መድረኩ የተከናወኑ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በዝርዝር ቀርበው የተገመገሙ ሲሆን፣በቀጣይ መከናወን በሚገባቸው አበይት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ግልጽ የስራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በስኬት ተጠናቋል።

በመድረኩ ላይ የክልል እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

​"የአካባቢው ሰላምና ልማት በቅንጅታዊ አመራር ይረጋገጣል!"

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ  ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ...
03/06/2026

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ክልልም ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው የክልላችን ሕዝብ ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል፤ በአማራ ክልል ምርጫ ማካሄድ ድምጽ ከመስጠት ባሻገር ነው" ብለዋል።

በክልላችን ምርጫ እንዳይካሄድ፤ ዜጎች መብታቸውን እንዳይጠቀሙ፤ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠርት፣ ክልሉ ሁልጊዜ በድህነት እና በግጭት ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጉ የውይይት እና የሰላም ተቃራኒ ኃይሎች ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል። "ይሁን እንጂ በሕዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ኃይላችን ጀግንነት እነርሱ የፈለጉት ሳይኾን ሕዝብ የፈለገው ኾኗል" ነው ያሉት።

የክልሉ ሕዝብ ትናንት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያሳየው ተሳትፎ፣ ጽናት እና ትዕግሥት የብልሃት እና የጥበብ ምንጭ መኾኑን ያሰመሰከረበት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ምርጫው ሕዝቡ ለፈተና የማይበገር፤ በዛቻ እና በማስፈራሪያ የማይሰበር፣ ለሰላም እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የትኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል ያሳየበት እንደሆነ አስታውቀዋል። "የክልላችን ሕዝብ በትናንትናው ምርጫ የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በሕዝብ ድምጽ እንጂ በኃይል አለመኾኑን ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ነው" ብለዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ ሰላም ወዳድነቱን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈላጊነቱን፤ በሕግና በሕዝብ ይሁንታ ለሚጸና መንግሥት ቀናዒነቱን በግልጽ እንዳሳየም አብራርተዋል። ለዚህ ደግሞ የከበረ ምስጋናዬን ከጥልቅ አክብሮት ጋር ማቅረብ እወዳለሁ ነው ያሉት።

"ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምርጫው በክልላችን በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ለሀገር መከለካያ ሠራዊት፣ ለክልላችን የጸጥታ ኃይል፣ በየደረጃው ለሚገኙ የክልላችን አመራሮች እና ለመላው የክልላችንን ሕዝብ በራሴ እና በአማራ ክልል መንግሥት ስም የላቀ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ለሀገር እና ለሕዝብ በአንድነት መሥራት ምን አይነት ስኬታማ ውጤት እንደሚያስገኝ ምርጫው ሕያው ምስክር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በምርጫው ጫፍ ረገጥ አስተሳሰቦች እስከ አደረጃጀቶቻቸው በሕዝብ ደምጽ ከሽፈዋል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት።

02/06/2026

በወሊድ ጊዜ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመከላከል በጤና ጣቢያ መውለድ ጠቃሚ መሆኑን በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ በአብርሃጅራ ጤና ጣቢያ የወሊድ ክትትል ሲያደርጉ ያገኘናቸው እናቶች ተናገሩ።

በጤና ጣቢያው የሚገኙ ባለሙያዎችም አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል እንደሚያደርጉላቸውም ተናግረዋል።

አብርሃጅራ:- ግንቦት 25/2018 የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: https://www.facebook.com/share/1CsG1K8GAR/
Telegrams :https://t.me/+xuUwI1oZM-I2M2U8
youtube:https://youtube.com/?si=9zUtvoNNNSOblOik

01/06/2026
ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሀገራችን ታሪካዊ ቀን ነው!!ለቀጣይ 5 ዓመታት ታላቂቷን ኢትዮጵያ የሚመራውን ፓርቲ ዛሬ በድምፃቸው እየመረጡ ነዉ።በአፍሪካ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ ከፍተ...
01/06/2026

ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሀገራችን ታሪካዊ ቀን ነው!!

ለቀጣይ 5 ዓመታት ታላቂቷን ኢትዮጵያ የሚመራውን ፓርቲ ዛሬ በድምፃቸው እየመረጡ ነዉ።

በአፍሪካ የዴሞክራሲ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛው የመራጮች ቁጥር በተመዘገበበት የዘንድሮው ምርጫ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በድምፃቸው ያረጋግጣሉ።

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ድምፅ በአንድነት ሲሰባሰብ የማይበገር ሀገራዊ አቅም እና ጠንካራ መንግስታዊ መሰረት ይፈጥራል።

ዛሬ ኢትዮጵያውያን ሉአላዊነታቸውን በድምፃቸው ያረጋግጣሉ!!

‎በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ምርጫ ክልል የወዲ-አንበሶ ቀበሌ ነዋሪዎች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኗሪዎች ድምጻቸውን  እየሰጡ ይገኛሉ ። #‎ኢትዮጵያ_እየመረጠች_ነው!
01/06/2026

‎በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ምርጫ ክልል የወዲ-አንበሶ ቀበሌ ነዋሪዎች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኗሪዎች ድምጻቸውን እየሰጡ ይገኛሉ ።

#‎ኢትዮጵያ_እየመረጠች_ነው!

Address

Gondar

Telephone

+251970887823

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ኦፊስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share