ጎንደር ማራኪ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን - Gondar Maraki Sub City Communication Office

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • ጎንደር ማራኪ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን - Gondar Maraki Sub City Communication Office

ጎንደር ማራኪ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን - Gondar Maraki Sub City Communication Office የዚህ ፌስ ቡክ ገጽ ዓላማ የክፍለ ከተማውን መልካም ገፅታ ማን?
(1)

በጎንደር ከተማ አስተዳደር የማራኪ ክፍለ ከተማ ማኅበራዊ ዘርፍ ጽ/ቤት በግማሽ በጀት ዓመት ተግባር አፈጻጸም 1ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነ።በግማሽ በጀት ዓመቱ በመናበብ እና በቅንጅት በመሰራቱ ...
25/01/2026

በጎንደር ከተማ አስተዳደር የማራኪ ክፍለ ከተማ ማኅበራዊ ዘርፍ ጽ/ቤት በግማሽ በጀት ዓመት ተግባር አፈጻጸም 1ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነ።

በግማሽ በጀት ዓመቱ በመናበብ እና በቅንጅት በመሰራቱ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን የጎንደር ከተማ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ አስታውቋል።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የ6ወር እቅድ አፈፃፀም በዛሬው ዕለት የገመገመ ሲሆን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉቀን ጌታሁን እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ተቀራርቦ እና በመቀናጀት በመሰራቱ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል ።

የችግር ተጋላጭ የሆኑ አካል ጉዳተኞች በማህበራዊ በኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው የሴቶች የወጣቶች፣ የአረጋውያን፣ የአካል ጉዳተኞች እና የህጻናት አደረጃጀት እሰከ ታችኛው እርከን ድርስ ውጤት በሚያመጣ መልኩ መደገፍ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።

ተቋማት አካቶ ትግበራ ላይ የሚፈለገውን ውጤት እንዲያመጡ ተገቢውን ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ የገለጹት ኃላፊዋ ሴቶች የወጣቶች የአረጋዉያን የአካል ጉዳተኞች በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚና በፖለቲካዊ ተሳታፊነት ለማሳደግ መሰራት ይገባል ብለዋል።

የተቋሙን የመፈጸም አቅም ማሳደግ እንደሚገባ በመጠቆም ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ በመስራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የሴቶች አደረጃጀቶች ለሴቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊዋ ቀበሌዎች ብቁና ተቀራራቢ ውጤት እንዲኖራቸው ክፍለ ከተሞች አስፈላጊውን ድጋፍ በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው አመላክተዋል።

የሴቶችን ጥቃት ለመከላከል ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ፈጠራ ላይ መስራት እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን በገቢ ማስገኛ ሴቶች እና ወጣቶች በማሰማራት በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ በቀጣይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ወይዘሮ ሙሉቀን አሳስበዋል ።

የጎንደር ከተማ ምክር ቤት የሴቶችና ወጣቶች ቋሚ ኮሜቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ልኪቱ አሰፋ በበኩላቸው የችግር ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል ።

የሴቶች አደረጃጀት ውጤታማ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ ጠቅሰው የአካቶ ትግበራ ሥራ ከባለፈው ዓመት በተሻለ መንገድ መከናወኑን አብራርተዋል ።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ እስካለው ተባባል ደግሞ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባር ሁሉም ክፍለ ከተሞች አበረታች ሥራ መስራታቸውን ገልጸዋል ።

የሴቶች የልማት ህብረት አደረጃጀት የክትትል እና ድጋፍ ሥራ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አመላክተዋል ።

በበጀት ዓመቱ ማራኪ ክፍለ ከተማ ማኅበራዊ ዘርፍ ጽ/ቤት የተሻለ ውጤት በማስመዝገቡ የእውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል።

ክፍለ ከተማው በ2018 በጀት ዓመት በ1ኛ ሩብ ዓመትም ከሌሎች ክፍለ ከተሞች በአፈጻጸም 1ኛ በመውጣት ዕውቅና የተሰጠው ሲሆን በሁለተኛው ሩብ ዓመትም የተሻለ ሥራ በመሥራት የዕውቅና ደረጃውን አስጠብቆ ቀጥሏል።

24/01/2026
24/01/2026
ጎንደር ጥምቀትን ለማክበር የሚመጡ እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጁ ሆናለች፡- የከተማዋ ከንቲባ ቻላቸው ዳኘውጎንደር ጥምቀትን ለማክበር የሚመጡ ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጁ...
14/01/2026

ጎንደር ጥምቀትን ለማክበር የሚመጡ እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጁ ሆናለች፡- የከተማዋ ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው

ጎንደር ጥምቀትን ለማክበር የሚመጡ ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጁ ሆናለች ሲሉ የከተማዋ ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው ገለጹ።

ወርሃ ጥር ጎንደር የምትሞሸርበት ወቅት ነው ያሉት ከንቲባው፤ ጥምቀት የሕዝባችን ባህል፣ ሃይማኖት እና የአብሮነት እሴቶች ጎልተው የሚወጡበት በዓል ነው ሲሉ የበዓሉን ዝግጅት አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

የጋራ ታሪካችን የሆነው የአፄ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት ከ400 ዓመታት በኋላ በመደመር መንግሥት በተሰጠው ልዩ ትኩረት እድሳት በተደረገለት ማግስት በአዲስ ገፅታ ለመጎብኘት ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡

ከንቲባው አክለውም ቤተ-መንግሥቱ ወደ መጀመሪያ ዘመኑ ተመልሶ ብርሃን በማግኘቱ በምሽት ሁሉ እንዲጎበኝ ሆኗል ነው ያሉት።

ለጥምቀት በዓል ወደ ጎንደር ለሚጓዙ የበዓሉ ተሳታፊዎች የትራንስፖርት አማራጮች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፤ ተጨማሪ የበረራ አገልግሎቶች እንዲኖሩ መደረጉንም አክለዋል።

ሆቴሎች እንግዶችን በተገቢው መልኩ ለመቀበል ዝግጅት አድርገዋል ያሉት ከንቲባ ቻላቸው፤ በነዋሪዎች ዘንድ ላለፉት 3 ዓመታት ባህል ሆኖ የመጣውን 'አንድ እንግዳ ለአንድ አባወራ' ፕሮግራም ዘንድሮም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

አያይዘውም የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ ማራዘም የሚያስችሉ የተለያዩ ዝግጅቶች ስለመጠናቀቃቸውም በመግለጫቸው አስታውቀዋል።

ጎብኝዎች አይረሴ ትውስታን ይዘው የሚመለሱበት ዝግጅት ተጠናቋል ያሉት ከንቲባው፤ ነገ የሚከበረው የአፄ ቴዎድሮስ የልደት በዓል አንዱ ነው ብለዋል። የፊታችን አርብ የኪን ኢትዮጵያ ድግስ፣ የባህል ፌስቲቫል እና ሌሎች ኩነቶችም ይካሄዳሉ ሲሉም ጠቅሰዋል።

የሀገር ቤት እና ባሕር ማዶ እንግዶችም ከጥምቀት በዓል ተሳትፏችሁ ጎን ለጎን እድሳት የተደረገለትን የአፄ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት እና በኮሪደር ልማት የለማውን የጎንደርን አዲስ መልክ እየጎበኛችሁ፣ የአባቶቻችሁን ታሪክ እወቁ ሲሉ ከንቲው መልዕክት አስተላልፈዋል።

የአፄ ቴዎድሮስ 207ኛ የልደት ቀን በጎንደር ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።መይሳው ካሳ መነጣጠል ሱስ በሆነባቸው መሳፍንቶች መካከል መደመርን ትርጉም ሰጥተው በጋራ ለትልቅ ሀገር ...
14/01/2026

የአፄ ቴዎድሮስ 207ኛ የልደት ቀን በጎንደር ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።

መይሳው ካሳ መነጣጠል ሱስ በሆነባቸው መሳፍንቶች መካከል መደመርን ትርጉም ሰጥተው በጋራ ለትልቅ ሀገር የተዋደቁ መሆኑን በዓሉ ላይ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ገልፀዋል፡፡

መይሳው ካሳ ትልቅ ሀገር የመፍጠር ህልም ነበራቸው ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ለኢትዮጵያ አንድነት በከፈሉት ዋጋ ስማቸው አሁንም ከፍ ብሎ እተጠራ ነው ብለዋል፡፡

መይሳው ካሳ ታላቅ አገር መገንባት ብቻ ሳይሆን ሀገሪቱን በቴክኖሎጅና በእውቀት የማበልፀግ ህልምም እንደነበራቸው ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ በመደመርና በእንድነት የምንቆምበት ወቅት ላይ እንገኛለን ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው እንደ መንግስት የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የአፄ ቴዎድሮስን ሃውልት በከተማዋ በትልቁ በመገንባት ለቱሪስት መስህብነት ከማዋል ባሻገር ወጣቱ ትውልድ የእርሳቸውን ታላቅ ሀገር የመገንባት ህልም እውን ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋየ ደግሞ አፄ ቴዎድሮስ የኢትዮጵያ የለውጥ ሃዋሪያ ሆነው ሀገሪቱን የመሩ መሆናቸውን ገልጸዋል ።

በዘመነ መሳፍንት የነበረው ሰራዊት በአንድ እንዲሆን በማድረግ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰራዊቱ ደምወዝ ኑሮት እንደ ሀገር እንዲቀጥል ያደረጉ ንጉሥ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

አፄ ቴዎድሮስ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ትልቅ አብዮት ያመጡ ንጉሥ መሆናቸውን ጠቅሰው እኛ የአፄ ቴዎድሮስ ልጆች ነን ስንል አፄ ቴዎድሮስ የጀመሩትን ኢትዮጵያዊነት መንገድ ተከትለን ኢትዮጵያዊነት በማፅናት ህብረ ብሔራዊ ያላትን ኢትዮጵያ ወደ ፊት ከፍ ማድረግ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህም ሁላችንም ርብርብ ማድረግ ይገባል ሲሉ ቢሮ ኃላፊው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ማሪያሟ ካሳሁን ደግሞ የአፄ ቴዎድሮስ ሲወለዱ ሀገር በመሳፍንቶች ተከፋፍላ አንድ የሚያደርጋት ሀቀኛ ያጣችበት ዘመን እንደነበር ገልፀዋል ።

ይህን ኃላቀር የጦርነትና ከባድ ስርዓት ባህልና አስተሳሰብ በመቀልበስ የችግረኞች አባት በመሆን ህዝባቸውንና ጦራቸውን አስተሳስረው አንዲት ኢትዮጵያ መፍጠር የቻሉ ታላቅ መሪ መሆናቸው ተናግረዋል ።

የንጉሡን ልደት ስናከብር በእሳቸው የተጀመረውን ዘመዊነት ኢትዮጵያ በህብረ ብሔራዊ አንድነት መንፈስ በማስቀጠል ዓለም ከደረሰችበት የብልጽግና ማማ በማድረስ ህልማቸውን እውን እንዲሆን ርብርብ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በበዓሉ የፖሊስ ማርሽ ባንድ ፣ ግጥም ፣ መነባንብ እንዲሁም በፋሲለደስ የባህል ቡድን መዚቃ ቀርቧል።

የአበባ ጉንጉን በአፄ ቴዎድሮስ ሀውልት ላይ የማስቀመጥ ስነ ስርዓትም ተካሂዷል ።

14/01/2026
 !የጥምቀት በዓል በአገራችን በአደባባይ ከሚከበሩ ታላለቅ በዓላት መካከል አንዱ ሲሆን በተለይም በጎንደር ከተማ በየዓመቱ ጥር 11 ቀን ከአበው ሲርድ ሲዋረድ የመጣውን ሃይማኖታዊና ባህላዊ ት...
14/01/2026

!

የጥምቀት በዓል በአገራችን በአደባባይ ከሚከበሩ ታላለቅ በዓላት መካከል አንዱ ሲሆን በተለይም በጎንደር ከተማ በየዓመቱ ጥር 11 ቀን ከአበው ሲርድ ሲዋረድ የመጣውን ሃይማኖታዊና ባህላዊ ትውፊት ጠብቆ በደማቅ ሁኔታ የሚከበር ዓቢይ በዓል ነው፡፡
በዓሉ የሚከበርበት ዋነ ምክንያትም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅን ይፈጽም ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ የተጠመቀበትን ዕለት ለማስታወስ እንደሆነ የዘርፉ ምሁራን ይናገራሉ፤ የጥምቀት ባዓል በአገራችን ከማይዳሰሱ ቅርሶች መካከል አንዱ በመሆኑ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በርካታ ቱሪስቶች ከአገር ውስጥና ከባሕር ማዶ ወደ መዲናችን በብዛት ይጎርፋሉ፤ ስለሆንም በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓና ከመንፈሳዊ እሴቱ በተጨማሪ ለከተማችን ዕድገትና ለሕዝዝባችን ጠቀሜታ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውም የጎላ ነው፡፡
ይህ ታሪካዊ በዓል በተባበሩት መንግሥታ የኢኮኖሚ የትምህርትና የባህል ድርጅት (UNESCO - United Nations Education Science and Culture Organization) የተመዘገበ በመሆኑ የማይዳሰስ ቅርስ ለጎንደር ከተማ ሕዝብ ትልቅቀ ጥቅም የሚሰጥ ከመሆኑም ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ይበልጥ እውቅና እንዲያገኝና የቱሪስቶች ዓይን ወደ ኢትዮጵያ እንዲያማትር የሚያደርግ መልካም አጋጣሚ ነውና እንጠቀምበት፡፡
ይህ በዓል ባለቤትነቱ የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ከርስቲያን ቢሆንም ከኢኮኑሚ አንፃር ግን ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ስለሚያደርግ በዓሉ የሁሉም ነው ማለት ይቻላል፤ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በርካታ ቱሪስቶች ወደ ከተማችን ስለሚመጡ ከሊስትሮ ጀምሮ ሆቴሎች ምግብ ቤቶች ፔንሲዮኖች የባህል ምሽት ቤቶች ባህላዊ አልባሳት መሸጫ ሱቆች የትርንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎችን በሙሉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ለማንም ግልጽ ነው፡፡
ይህ በዓል በሰላም እንዳይከበርና ሕዝቡ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዳይሆን ለማድረግ የጎንደርን ኢኮኖሚ ለማንኮታኮት የጥፋት አጀንዳ ቀርጸው ሌሊትና ቀን የሚሠሩ አፍራሽ ኃሎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ለአፍታም ቢሆን መዘንጋት የለብንም ሕዝቡ ግን ከተባበረ ከሕዝብ የሚደበቅ ወንጀልና ወንጀለኛ ስለማይኖር የሕዝብን ሰላም የሚያውክን ግለሰብም ሆነ ቡድን ለጸጥታ አካላት እና ሰላም አስከባሪ ኃይሎች አጋልጦ በመሥጠት ማኅበረሰቡ በተለይም የሰላም ዘብ የሆነው ወጣቱ ተቀናጅቶ አካባቢውን መጠበቅ ይገባዋል፡፡
የጥምቀትን በዓል ለማክበር ሁለንተናዊ ርብርብ በማድረግ ማኅበረሰቡ በተለይም ወጣቱ ትውልድ የአንበሳውን ድርሻ (The lion share) መውሰድ አለበት፤ በሌላ በኩል ሕዝቡ አካባቢውን በማጽዳትና የሰላምን በሮች በመክፈት ዓመት በዓልን ጠብቆ በምግብ ቤቶችና በሱቆች ላይ የዋጋ ጭማሪ ባላማድረግ እንግዳ ተቀባይ መሆናችንን ከዘፈን ባለፈ በተግባርም ማሳየት ያስፈልጋል፡፡
ይህንን ታሪካዊ በዓል በሰላምና በስኬት ለማክበር ሰላም አስከባሪ ኃይሉ ፀጥታውን በማስከበር ሕዝቡ አካባቢውን በማጽዳትና ውብ በማድረግ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ተገቢውን አገልግሎት በመሥጠትና ዓመት በዓልን ጠብቆ የዋጋ ጭማሪ ባለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በመወጣት በዓሉ በሰላምና በስኬት እንዲከበር ማድረግ ከእያንዳንዳችን የሚጠበቅ የዜግነት ግዴታችን ነውና ኃላፊነታችንን በአግባቡ እንወጣ መልእክታችን ነው!!!

Address

Gondar City
Gondar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጎንደር ማራኪ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን - Gondar Maraki Sub City Communication Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share