የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት

የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት በዚህ ገጵ በወረዳችን የሚሰሩ ስራወችን ለህዝብ የምናደርስበ?

በወረዳችንና በመለው አለም ለምትገኙ ህዝበ ሙስሊም አንኳን  ለ1446ኛው የኢድ-አል -አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!!                                           ...
06/06/2025

በወረዳችንና በመለው አለም ለምትገኙ ህዝበ ሙስሊም አንኳን ለ1446ኛው የኢድ-አል -አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!! የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በላይነህ አዛናው የኢድ -አል -አድሃ(አረፋ) በዓል በጎ የሚታሰብበት ፣ የተራቡ የሚጠግቡበት ፣የተነፋፈቁ የሚገናኙበት ፣ያለው የሌለውን የሚረዳበት የአንድነትና የፍቅር በዓል ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው 1446ኛው የአረፋ በዓል የሰላምና የፍቅር በዓል እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ በዓሉን ስናከብር ለሀገራችንና ለህዝባችን ሰላምና ፍቅር በማስተማር በመረዳዳት መዕድ በማጋራት እንድታከብሩ ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው አክለው አሳስበዋል:: በድጋሜ እንኳን ለ1446ኛው የኢድ -አል-አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!! EID MUBARK!!!! አቶ በላይነህ አዛናው የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ

በሁሉም አለም ለሚኖሩ ህዝበ ክርስቲያን እንኳን ለ2017ዓ.ም የፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!!!!                                      የምዕራብ በለሳ ወ...
19/04/2025

በሁሉም አለም ለሚኖሩ ህዝበ ክርስቲያን እንኳን ለ2017ዓ.ም የፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!!!! የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በላይነህ አዛናው አምላካችን መዳኒታችን እየሱስ ክርስቶስ አስቀድም ስለወደደንና ስላፈቀረን ከሌሎች ፍጥረታት በተለየ መልኩ የሚያስፈልገነን ነገር ሁሉ ከአዘጋጀ በኋላ ፈጥሮ የስነ-ፍጥረታት ዘውድ አድርጎ በገነት ቢያስቀምጠንም የቀደመ አባታችን አዳም በእንዝላልነትና በስንፍና በከይሲ ዳቪሎስ ተሳስቶ አታድርግ የተባለውን አድርጎ የሰው ልጅ የዳቪሎስ ባሪያ ቢሆንበት መዳኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ሰማያት ወርዶ ከድንግል ማሪያም ተወልዶ አርባ ሌሊትና አርባ ማልት ከዘረጋ ሳያጥፍ ፣ከቆመ ሳይቀመጥ ከፆመ ከፀለየ በኋላ በጅራፍ ተገርፎ፣በዘንግ ግንባሩን ተመትቶ ፣በችንካር ተወግቶ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ስጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ በገዛ ፍቃዱ ሞቶ ከተቀበረ በኋላ በ3ኛው ቀን ምትን ድል ነስቶ በትንሳኤው እኛን የእግዚአብሔር ልጅ አድርጎናል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የፋሲካ በዓልን ስናከብር ያለው የሌለውን ማዕድ በማጋራት የተለመደውን ኢትዮጵያዊነት ባህላችን ጠብቀን ተደጋግፈን ፣ተረዳድተን በዓሉን እንድናከብር ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው አክለው አሳስበዋል። በድጋሜ እንኳን 2017 ዓ.ም የፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!! በዓሉ የሰላም ፣የፍቅር ፣የመደጋገፍ ፣ የአንድነት በዓል እንዲሆንልን አመኛለሁ!!! የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በላይነህ አዛናው

የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት የቀበሌ ስራ አስኪያጆችን የ2015ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ!!!                                              ...
20/06/2023

የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት የቀበሌ ስራ አስኪያጆችን የ2015ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ!!! በግምገማውም፦ የጽ/ቤቱ ባለምያወች፣ቡድን መሪወች፣የቀበሌ ስራ አስኪያጆችና የሚመለከታቸው አካላቶች በተገኙበት የጽ/ቤቱ ዓመታዊ የስራ እንቅስቃሴ በጽ/ቤቱ የዕቅድና በጀት ክትትል ባለምያ በወ/ሮ ፍቅርአዲስ ሙሉአለም የቀረበ ሲሆን የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ከወረዳ እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር በተሰራው የቅንጅት ስራ ህብረተሰቡን የጤና መድን አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ፣ከቀበሌ ከበሌ ምንገዶችን በመስራት፣ክፍያ ከፍለው መታከም የማይችሉትን ሴቶችና ህፃናት ነፃ የጤና መድን ተጠቃሚ በማድረግ ፣በወረዳው የሚገኙ የአካል ጉደተኞችን በማሀበር ተደራጅተው በመስራት ተጠቃሚ በማድግ፣ ባለምያወችና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የአልማ አባል በማድረግ መዋጮ በፍቃዳቸው እንዲያወጡ በማድረግ በወረዳችን ደረጃቸውን የጠበቁ ት/ቤቶች እንዲሰሩ በማድረግ የወረዳችን ማሀበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ሲሉ የጽ/ቤቱ ዕቅድ ዝግጅትና ግምገማ ባለምያ ወ/ሮ ፍቅርአዲስ ገልፀዋል በተጨማሪም ቀበሌወችን በክላስተር ከፍለንና ሌሎች ተቋማትን በበላይነት ማስተባበር በመቻላችን የወረዳችን ህዝብ በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ ማድረግ ችለናል ያለት የጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደስታው ካሰው መዋቅራችን ከዚህ የበለጠ በማጠንከር ህዝባችን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ ማድረግ አለብን ሲሉ የጽ/ቤቱ ሀላፊ አክለው አሳስበዋል።

በምዕራብ በለሳ ወረዳ "ፈተናወችን ወደ መልካም ዕድል በመቀየር ህዝባችን እናሻግራለን" በሚል መሪ ቃል ለሁለት ተከታታይ ቀን ሲካሄድ የቆየው ኮንፈረስ ተጠናቀቀ!!!                 ...
30/05/2023

በምዕራብ በለሳ ወረዳ "ፈተናወችን ወደ መልካም ዕድል በመቀየር ህዝባችን እናሻግራለን" በሚል መሪ ቃል ለሁለት ተከታታይ ቀን ሲካሄድ የቆየው ኮንፈረስ ተጠናቀቀ!!! የለውጡ ምዕራፍ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ በሀገራችን ፣በክልላችን፣በዞናችንና በወረዳችን ብዙ ውጤታማ ድሎችን የተጎናፀፍን መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው በዚህም በወረዳችን አስተማማኝ ሰላምና ደንነት ለማምጣት ፣ በግብርና ባልተለመደ የበጋ መስኖ ስንዴ አብዮት ፣ለውጡን በተገቢው ምንገድ ማስቀጠል፣ፕሮጀክቶችን ማስጀመርና ማስጨረስ፣የደባሪ መስኖ ካናል፣የአ/ተራራ መስኖ ካናል፣የአይሰግ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ዋና ዋናወቹ ናቸው የአማራ ህዝብ የወሰንና ማንነት ጥያቄወች ከ30ዓመት በኋላ በህጋዊ መንገድ ምላሽ የሚያገኝበት ዕድል መፈጠሩና የክልላችን ህዝብ ለዘመናት ጥያቄ የሆነውን የወልቃይት፣ጠገዴ፣የማንነትና የወሰን ጥያቄ በህጋዊ ጥያቄው እንዲመለስ እየሰራ መሆኑና እንዲሁም ለውጡ እንዳይቀለበስ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል ተብሎ በኮንፈረሱ መግባባት ላይ ተደርሶ የለውጡን ጉዞ በማፋጠን ህዝባችን ወደ ላቀ ብልፅግና ለማሻገር በመረዳዳትና በቅንጅት ለመስራት ለተሳለጠ ጉዟችን እንቅፋት የሚሆኑ መሰናክሎችን ለማስወገድ ባለ5 የአቋም መግለጫ ነጥቦች አውጥቷል። 1ኛ ,በወረዳችን እየተከሰተ ያለውን የእርስ -በእርስ ግድያ ፣ጥይት ተኩስ፣ህገ ወጥ መሳሪያ ዝውውርና ስርቆትን ለማስቀረት ህዝቡን ያሳተፈ ትግል ፣የመፍትሔ አቅጣጫወች ላይ ጥልቀት ያለው ውይይት በማካሄድ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ለማፅናት ቃል እንገባለን!!! 2ኛ, በማንኛውም የሀገራችን አካባቢወች የሚስተዋሉ ግጭቶችን በሰላማዊ አማራጮች ለማድረግ ያለንን ቁርጠኝነት እየገለፅን ሌሎች ሰላም ወዳድ ሀይሎች ሁሉ በማንኛውንም አይነት ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ የመፍታት አማራጭ እንዲከተሉ ጥሪያችን እናቀርባለን!!! 3ኛ ,ፈተናወችን ዕንደ መልካም እድል በመውሰድ ህዝባችን አበክሮ የሚፈልጋቸውን እውነተኛ ሰላም ፣የዴሞክራሲና የልማት ፍላጎት እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልፅግናን ዳር እንዲደርስ መላ የምዕ/በ/ወረዳና የቀበሌ አመራሮች ሌት ተቀን ለመስራትና ሁሉንም አይነት ዋጋ ለመክፈል ቁርጠኛ መሆናችንን እናረጋግጣለን!!! 4ኛ ,ችግሮችን ይፈቱልናል፣ያስተዳድሩኛል ብሎ በምርጫ ድምፅ ለሰጠን ለወረዳችን ህዝብ እኛ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች ሙሉ አቅማችን ተጠቅመን ለህዝባችን ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ቃል እንገባለን!!!! 5ኛ ,የምዕራብ በለሳ ወረዳ ኮንፈረስ ተሳታፊወች እንደወሰነው የችግሮቻችን መውጫ መንገዶች የአመራርና አባላት አንድነት መፍጠር፣ከህዝባችን ጋር መተማመን መፍጠር ፣ሀይል የማሰባሰብና የሀገር አንድነት በመፍጠር ፅንፈኝነትን የሚታገል ስልት በመንደፍ ሰላምና ልማትን ቅድሚያ በመስጠት የመንግስትን የመፈፀም አቅም በማጎልበት ህዝባችን ለማሻገር ቃል እንገባለን!!! ግንቦት22/2015 ዓ.ም አርባያ

"ፈተናወችን ወደ መልካም ዕድል በመቀየር ህዝባችን እናሻግርአለን"በሚል መሪ ቃል በምዕራብ በለሳ ወረዳ ከግንቦት 21-22/2015ዓ.ም የሚያካሂደውን ኮንፈረስ ጀመረ!!!!             ...
29/05/2023

"ፈተናወችን ወደ መልካም ዕድል በመቀየር ህዝባችን እናሻግርአለን"በሚል መሪ ቃል በምዕራብ በለሳ ወረዳ ከግንቦት 21-22/2015ዓ.ም የሚያካሂደውን ኮንፈረስ ጀመረ!!!! በኮንፈረሱ ማስጀመሪያ ፕሮግራም የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የውሃና ኢነርጅ መምሪያ ሀላፊ አቶ በርሀኑ ይመርና የዞኑ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ኑረዲን ሰዒድ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የበለሳ ህዝብና መሪ በህልውና ዘመቻው ጠላትን ድባቅ በመምታት ኢትዮጵያ እንድትጠና ህዝቦቿም በነፃነት እንዲኖሩ ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ወንድምና እህቶቹ ጋር ያደረገው ትግል እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው ያሉት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የውሃና ኢነርጅ መምሪያ ሀላፊ አቶ ብርሀኑ ይመር ጀግና ህዝብ ጀግና መሪ መፍጠርን ያውቅበታልና በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ህዝብና መንግስትን አስተባብሮ መስራት በሄ/ር 34 ኩንታል ስንዴ እንዲመረት በማድረግ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ገበሬወች ለልጆቻቸው ዳቦ ለከብቶቻቸው መኖ ማብላት እንዲችሉ ያደረገ፣ከ8 በላይ በፀሀይ ሀይል የሚሰሩ የውሃ ቧንቡ ውሃ በማሰራት የገጠሩ ማሀበረሰብ የንፁህ ውሃ መጠጥ ተጠቃሚ ያደረገ፣ የበለሳ ህዝብ ልማት እንዲፋጠኑ መሰረት የሚጥል ድልድይ ያሰሩ፣ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ቀበሌወችን በውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ በአበይታራ ቀበሌ 33 ሚሊየን ብር የተበጀተለት የውሃ ፕሮጀክት ያስጀመሩ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ኑረዲን ሰዒድን ጀግና መሪ መፍጠር የቻለ ጀግና ህዝብ ከዚህ የበለጠ ህዝብና መንግስትን አስተማምኖ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር አጥንቶ ህዝቦቿን የልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ አመራር እንደምትፈጥሩ እርግጠኛ ነኝ ሲሉ ሀላፊው አክለው ተናግረዋል።

የብልፅግና ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የአማራ ብልፅግና ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ በነበሩት በአቶ ግርማ የሽጥላ ግድያን ተከትሎ እየታየ ያለውን የተዛባ አመለካኩት የሚያወግዝ በምዕራብ በለሳ ወረዳ በ...
17/05/2023

የብልፅግና ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የአማራ ብልፅግና ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ በነበሩት በአቶ ግርማ የሽጥላ ግድያን ተከትሎ እየታየ ያለውን የተዛባ አመለካኩት የሚያወግዝ በምዕራብ በለሳ ወረዳ በአርባያ ከተማ ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ተካሄደ!!!! በህዝባዊ ሰልፉም፦ሴቶች፣ህፃናት፣ወጣቶች፣የመንግስት ሰራተኛው ፣ነጋዴውና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍል የተሳተፈበት ህዝባዊ ሰልፍ ሲሆን "ለአማራ ህዝብ የሚበጀው ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት ለህዝቡ ዘላቂ ልማት እና ሰላም በጋራ መቆም ሲቻል ነው", ለአማራ ህዝብ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን የማይፈልጉ ሀይሎች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል",ወንጀለኞችን በህግ በመጠየቅ የህግ የበላይነት መከበር አለበት"የሚሉ ድምፆች በህዝባዊ ሰልፉ ተስተጋብተዋል። ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት ነው!!!! የምዕራብ በለሳ ወረዳ ህዝብ

ለሁሉም የክርስና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2015ዓ.ም የፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!!!                                      ፈጣሪ በክፉወች ተንገላቶ በመስቀል...
15/04/2023

ለሁሉም የክርስና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2015ዓ.ም የፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!!! ፈጣሪ በክፉወች ተንገላቶ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ በሚስማር ተቸንክሮ የሰውን ልጅ ከዳቪሎስ ባርነት አላቆ የሚገባውን ክብርና ነፃነት አጎናጥፎ ለዓለም ህዝብ ትህትና ፣ፍቅር አንዱ ለአንዱ መኖር እስከ ምት ድረስ መሆን እንዳለበት ፈጣሪ በክፉወች ባየው መከራና ስቃይ ተምረን ዛሬም የክፉ ምሳሌ የሚሆኑ ስለማጠፉ ሀሳባቸውን ባለመሸከም እርስ በራሳችን መልካም ግንኙነት በመፍጠርና በመረዳዳት ወልደን የምናሳድግባት፣አርሰን ነግደን በየ ስራ ዘርፉ ሰርተን የምንጠቀምባት ለህዝቦቿ ምቹ የሆነች ኢትዮጵያን ፈጥረን ለሚቀጥለው ትውልድ ለማስተላለፍ እያንዳዳችን የሚጠበቅብነን ሀላፊነት እንወጣ እያልኩ በዓሉ የሰላም የፍቅር ፣ አንዱ ለአንዱ ማዕድ በማጋራት ከፈጣሪ በረከት የምታገኙበት በዓል እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴ ነው!!!! በድጋሜ እንኳን ለ2015ዓ.ም የፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!! የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑረዲን ሰዒድ

መጋቢት 11/2015ዓ.ም                                             አርባያ                                                        ...
20/03/2023

መጋቢት 11/2015ዓ.ም አርባያ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የምዕራብ በለሳ ወረዳ የመስኖ ስንዴ ልማት የመስክ ጉብኝት ተካሄደ!!!! በጉብኝቱም፦የአማራ ክልል ም/ዕርሰ መስተዳደር ዶክተር ጌታቸው ጀበር፣የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ሀ/ማሪያም ከፍያለው፣የማዕከላዊ ጎንደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ፈንታሁን ስጦተውና ሌሎች የክልል፣የዞንና የወረዳ አመራሮች በጉብኝቱ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የበጋ መስኖ ስንዴ ለኢትዮጵያ ብልፅግና የሚያመጣውን ፈይዳ ጥናት በማድረግ ከዚህ በፊት የበጋ መስኖ ስንዴ አልምተው በማያውቁ ወረዳወች ለአርሶ አደሩ ስልጠና በመስጠትና እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ሆኔታ ተስማሚ የሆነ የስንዴ ዘር በመዝራት ህዝባችን ከተቀቀለ ስንዴ ልመና ማውጣት የሚችል የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት አልምተናል ያሉት የክልል፣የዞንና የወረዳ አመራሮች ኢኮኖሚያችን እየጠነከረ በመጣ ቁጥር በችግሮቻችን ስበብ ሉዓላዊነታችን በመጋፋት የሀገራችን አንድነት የሚሸረሽሩ ሀይሎችን በማሳፈር ተቀናጅተን በመስራት የሀገራችን ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲፋጠን በማድረግ የሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ሀላፋነት በመሆኑ ተባብረን ሀገር መገንባቱ ላይ እንረባረብ ሲሉ የክልሉ፣የዞኑና የወረዳ አመራሮቹ አክለው አሳስበዋል።

የወረዳ አመራሩ፣የስራ ሂደቶችና ባለምያወች በተገኙበት በጨው አይደቁስና በማርዝባ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጉብኝት ተካሄደ!!!                                   ...
10/03/2023

የወረዳ አመራሩ፣የስራ ሂደቶችና ባለምያወች በተገኙበት በጨው አይደቁስና በማርዝባ ክላስተር የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ጉብኝት ተካሄደ!!! ከጉብኝቱ መጨረሻ ላይ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ዋሲሁን ከፍያለው አጭር ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን የበጋ መስኖ ስንዴ በማልማት የህዝባችን ህይወት ለመቀየር ሰፊ እቅድ ይዘን ተነስተን በ15 ቀበሌወች በስፋት በሌሎች ቀበሌወች በተበታተነ ሁኔታ በስፋት በማልማት ይህን የመሰለ የበጋ መስኖ አልምተናል ያሉት ሀላፊው የበጋ መስኖ ልማቱ ከዚህ ደረጃ ለማድረስ አመራሩና ባለምያው ከአርሶ አደሩ ጋር አገዳ አጭዶ ተሸክሞ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱ ሀገራችን የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ መሰረት እንዲጥል አድርጋል ሲሉ ሀላፊው አክለው ገልፀዋል በተጨማሪም የስራ ሂደቶችና ባለምያወች አስተያየት የሰጡ ሲሆን በወረዳችን የለማው የበጋ መስኖ ስንዴ ለሌሎች አካባቢወች ምሳሌ ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ በማበልፀግ የህዝባችን ህይወት እቀይራለሁ ብሎ የገባውን ቃል እየተወጣ ነው ያሉት አስተያየት ሰጭወቹ የዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ለኢኮኖሚዊ ብልፅግናችን መሰረት በመሆኑ ቀጣይነት እንዲኖረው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ለልማቱ ትኩረት በመስጠት አንድነቱን አጠናክሮ መስራት አለበት ሲሉ አክለው አስተያየት ሰተዋል።

በዘንድሮው ዓመት በወረዳችን የለማው የበጋ መስኖ ስንዴ ህዝባችን ከተረጅነት ስሜት በማላቀቅ አልምቶ መበልፀግ እንደሚቻል አስተምሯል!!!!!                                 ...
10/03/2023

በዘንድሮው ዓመት በወረዳችን የለማው የበጋ መስኖ ስንዴ ህዝባችን ከተረጅነት ስሜት በማላቀቅ አልምቶ መበልፀግ እንደሚቻል አስተምሯል!!!!! የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑረዲን ሰዒድ በወረዳችን የበጋ መስኖ ስንዴ በለማባቸው ቀበሌወች ገበሬወች የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ በማድረግ አርሶ አደሩን የበጋ መስኖ ስንዴ በማልማትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በመሸጥ ስንዴን ከራስ አትርፎ ለውጭ ገቢያ ማቅረብ እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ተግባር ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በዚህ ዓመት የበጋ መስኖ ስንዴን በማልት ህዝባችን እንዲጠቀም በዙ ወተን ወርደን በሰራነው ስራ ህዝባችን የተረጅነት ስሜትን እንዲሰብር ማድረጋችን በቀጣይ ከዚህ የበለጠ በማልማት የብልፅግናችን ጉዞ ያማረ የሰመረ ያደርገዋል ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው አክለው ገልፀዋል።

የካቲት23/2015ዓ.ም                                            አርባያ                                                          ...
02/03/2023

የካቲት23/2015ዓ.ም አርባያ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ምክር ቤት ጽ/ቤት ለቀበሌወች ዋና አፈ-ጉባኤወች፣ ዋና አስተዳዳሪወችና ስራ አስኪያጆች ስልጠና ሰጠ!!! በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑረዲን ሰዒድ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የዛሬው ስልጠና አባቶቻችንና እናቶቻችን የጣሊያን ወራሪ ሀይል ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት በአንድነትና በመተባበር ወራሪ ሀይሉን ተዋግተው በማሸነፍ ለኢትዮጵያና በአጠቃላይ የጥቁር ህዝቦች ነፃነትን እንዲያገኙ ያደረጉበት ቀን በመሆኑ ስልጠናው በዚሁ ታሪካዊ ቀን መሰጠቱ የእናቶቻችንና የአባቶቻችን ሀገራዊ ወኔ ሰንቀን በመስራት ሀገራችን ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ በማፋጠን ድህነትን ታሪክ በማድረግ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን እንደምናስረክብ አልጠራጠርም ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል። ስልጠናውን የሰጡት የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ አቻሽ ክፍሌ ሲሆኑ ለቀበሌወች ምክር ቤት ስልጠና በመስጠት የቀበሌ መዋቅሩ የሚሰራቸው ስራወችን በየወቅቱ እየገመገመ የህዝባችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተዘጋጀ ስልጠና ነው ያሉት ክብርት አፈ-ጉባኤዋ ከስልጠናው ያገኛችሁትን እውቀት በመጠቀም በየቀበሌው ያላችሁ የምክር ቤት አባላት የቀበሌውን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርግ ሰነድና መመሪያ እያወጣችሁና የሚሰሩ ልማቶችን በየወቅቱ እየገመገማችሁ የወከላችሁን ህዝብ እንዲጠቀም እንድታደርጉ ሲሉ ክብርት አፈ-ጉባኤዋ አክለው አሳስበዋል።

በምዕራብ በለሳ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የ2015ዓ.ም የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ የንቅናቄ መድረክ አካሄደ!!!                      በንቅናቄ መድረኩ፦የቀበሌ መዋቅሩ ፣የወረዳ አ...
25/01/2023

በምዕራብ በለሳ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የ2015ዓ.ም የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ የንቅናቄ መድረክ አካሄደ!!! በንቅናቄ መድረኩ፦የቀበሌ መዋቅሩ ፣የወረዳ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት የተገኙ ሲሆን የምዕራብ በለሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑረዲን ሰዒድ የተፈጥሮ ሀብቱን በማልማትና በመጠበቅ በአግባቡ የሚጠቀም ማሀበረሰብ በመገንባት የተፈጥሮ ሀብታችን ለብልፅግና ጉዟችን የራሱን አሻራ እንዲያስቀምጥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገናል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የተራቆቱ መሬቶችን በማልማት በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሸፈኑ በማድረግ ለወጣቱ ቋሚ የስራ እድል በመፍጠር የህዝባችን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከወረዳ እስከ ቀበሌ ያለው መዋቅር ህዝቡን አነቃንቆ የ2015ዓ.ም የተፈጥሮ ሀብት ልማታችንና ጥበቃችን ውጤታማ እንድናደርግ ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው በመክፈቻ ንግግራቸው አክለው አሳስበዋል።በተጨማሪም የምዕራብ በለሳ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ም/ሀላፊ አቶ አብርሀም ደሴ የ2015ዓ.ም የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ የማስፈፀሚያ ዕቅድ ያቀረቡ ሲሆን የዘንድሮው የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ በእውቀትና በሞያ ተደግፎ ህዝባችን እንዲጠቀም ለማድረግ በወረዳ ደረጃ 11 እና በቀበሌወች 134 የሰው ሀይል ስለተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ስልጠና ሰተናል ያሉት ሀላፊው ይህ ደግም በተፈጥሮ ሀብት ልማቱ ለህብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ተክል እንደ ዋንዛ እንዲሁም አፈር የማቀብ ተፈጥሮዊ አቅም ያላቸውን ተክሎች እንደ ጋቫ ያሉ ተክሎችን በመትከልና የተፈጥሮ ሀብት ልማታችን ሳይንሳዊ በመሆን የታለመለትን ግብ እንዲመታ ያግዘናል ሲሉ ሀላፊው አክለው ገልፀዋል።

Address

Gondar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የምዕራብ በለሳ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት:

Share