30/12/2025
የአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ በነጋዴ ባህር ቀበሌ በንብ ሃብት ልማት ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ እንስሳትና አሳ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ገለፀ።
🤝ታህሳስ 21/2018.ዓ.ም🤝
በ አዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ የማር ምርትና ምርታማነት ለማሻሻል የተጀመረው ዘመናዊ የንብ ቀፎ ሽግግር ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በነጋዴ ባህር ቀበሌ አርሶ አደሮችን ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለሚደረገው ሽግግር የኬንያ ሽግግር ቀፎ ለተጠቃሚ አ/አደሮች በመስራት እና ልምድ ልውውጥ በማሳደግ በማር ምርት ውጤታማ ስራዎችን እየሰሩ እንደሚገኙ ጽ/ቤቱ ገልፆልናል ።
የወረዳው የንብና ሃር ልማት ባለሙያ የሆነው አቶ ፀሃይነህ ባረከ በዚህ የኬንያ ሽግግር ቀፎ ስራ ለ 35 አ/አደሮች፣ ለ 3 የቀበሌ ባለሙያዎችና ለ 3 የወረዳ ባለሙያዎች በተግባር የተደገፈ ልምድ ስለ ተቀናጀ የንብ ሃብት ልማት ማሻሻያ ዘዴዎችና አያያዝ፣ እንዲሁም አ/አደሩ በአካባቢ በቀላሉ በሚያገኛቸዉ ቁሳቁሶች ስለ ሽግግር ቀፎ አሰራር ለተከታታይ 2 ቀን የአሰራር ልምድ ልውውጥ ተሰጥቷል፡፡
ታህሳስ 21/2018.ዓ.ም
ምንጭ- (የአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ እንስሳትና አሳ ሃብት ልማት ጽ/ቤት )